ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
አካሄድ

የስንፍናን ጡዘት
ካንሸዋረሩበት
ከአካሄዱ ጀርባ
ሀፍረትን ቢመርጡም
ወደው ለሄዱበት
ነፃነት አይቀሙም
...
ግና................
ተዘክረው ቢመጡም
እንደአካሄዳቸው
ምህረትን ፍለጋ
ዳር ዳር ቅኝታቸው...
ልዝቡን ሹክሹክታ
ሽቅብ ቢያደምጡም
ባልኖሩት ንሰሃ
ፍቅርን አያቀልሙም።

           By ኢያሱ ከበደ
           መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም
            @josheyasuu

@getem
@getem
@getem
👍1311🔥4
የኔ ዓለም!
(ሚካኤል አስጨናቂ)

እንዳንቺ 'ሚጣፍጥ - አንጀት የሚያረካ
ጣፋጭ የለም ለካ!
ጥዑም ናቸው ያሉኝ ማርና ቸኮሌት
ካንቺ ሲነፃፀር ፣ መረሩኝ እንደ ሬት።
.
ማርያምን !
.
ከድምፀትሽ ልቆ - 'ሚሰማ ሙዚቃ
ከአንባሰል ከባቲ ከብሉዝ ትዝታ
ወድያም ከብሉዙ ፡ ደግሞም ከአፍሪቃ
አንድም የለም በቃ!
.
ማርያምን!
.
እንደውም ፣ እንደውም
ካንቺ ጋራ ስሆን ሀዘን ጭንቄን ሽሮ
የደስታ ወሰኔን ፣ አለቅጥ አንሮ
የሚገርመኝ የለም ከዓለሟ ተፈጥሮ።
.
እውነት አይገርመኝም !!
ይኸው ለምሳሌ...
ያቺ የሰማይ ሳህን
ምንድናት ጨረቃ?
እንዲያ ስትሞገስ
ተስላ ፣ ተፅፋ
በሁሉ ተደንቃ...
አንቺን ያየሁ ጊዜ
ዓይኔ ውስጥ ከሰመች
ተዋርዳ ፣ ተንቃ።
.
ማርያምን...
የቱ ኮሜዲ ነው የትኛው ቀልደኛ
እኔን የሚያደርገኝ የወሬው ምርኮኛ?
ደግሞ ካንቺ በላይ
እኔን ለማሳሳቅ ማነው የሚደፍረው ?
ባንቺ ጨዋታ ነው
የተደበቀውን.. . ጥርሴን የምገልጠው።
.
ማርያምን !
እንደውም ባጭሩ.. .
አሁን ይሄ ግጥም
የቃላት ጥርቅም
እጅግ መሳጭ ሆኖ አንባቢው ቢያደንቅም
ካንቺ ግን አይበልጥም።
.
ማርያምን።

@getem
@getem
@getem
👍7232😁8🤩5🔥2🎉1
የመዳፌን መሃል
ነክቶኝ መሃል ጣቷ
አሰፈረችብኝ~'ማይነቀል ቆሌ
ከአያት ቅድም አያቷ
(ክ...ፋ...ቷ!)
አልል ጥፍሯ ወጋኝ
ተቆርጧል ባጭሩ
ምን ብትቋጥርበት
ጣቷ መናዘሩ
ሀጥያት ማስዘርዘሩ...
ነፍስ ማስገበሩ...
የእንጨት አፍሮ አይገቤ
የመቅደስ ስር እጣን
ጩህ ጩህ እንደሚለው
ትዕቢተኛ ሰይጣን
እሪ ልል ስነሳ
ለአፍታ በነካችኝ
ጉሮሮ እንዲከዳኝ
ከንፈር ደገመችኝ

(ጉድ እሷ!)

መቼስ በሀገር ታሪክ
እኛ በምናውቀው
እንጂ ነጭ ሲወር
ምድሩን ሲያስጨንቀው
መዳፉን ተስሞ
እስኪጠፋው አለም
ለጠላቱም ቢሆን
እጅ ያልሰጠ የለም

(እንኪ እጅ ጀብኣ በይ!)

ዘማርቆስ
@wogegnit

@getem
@getem
@paappii
👍5821🤩7🔥5
የወራት ዘመኑ ቀኑ ተቆረጠ
የማህፀኗን እቅፍ በጊዜ አሳቦ
ሆዷን ረገጠ

በ 18 ምሽት
ለ 19 አጥቢያ ቀኑ ከረፈደ
ማርያም
ማርያም..... ሲባል ዮኒ ተወለደ
🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳
🥳@getem
🥳@getem
🥳@getem
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳

12:35 PM

🎂@yonatoz🎂
ዮኒ
ኣታን
🎉14450👍41🔥5🤩4👎2
ገጣሚው
ማንም ያላየውን
ማንም ያልፃፈውን
በፊት ያልነበረ …
ስንኝ ለማዋቀር
መወጠን ጀመረ ።
ሆኖም ግን አንድ አጣ
ያልተፃፈ በሰው
ሁሉን ቢያሰላስል
ቢያወጣ ፣ ቢያወርደው
አንድም አልነበረ
ሌላው ያልጀመረው ።
አሰበ ገጣሚው
አወረደ ፣ አወጣ
አዲስ ነገር ልፃፍ
ብሎ የጀመረ
ገጣሚ ግን አጣ።
እናም ይሄን ጊዜ
የሱን ክታብ ሲቃኝ
ቀለሙን ሲያዋድድ
ከዝርጉ ወረቀት
'አዲስ ነገር ልፃፍ'
የሚል ነበረበት ።
ስንኙ አበቃ
ብዕር ተሰለበች
ታጠፈች ወረቀት
ግጥም ቀን ወጣላት ፤
አዲስ ነገር ፃፈ
አዲስ ነገር ልፃፍ
ብሎ በመነሳት ።

(ሚካኤል አ )

@getem
@getem
@getem
👍5317🔥10😱3😁1
የቢላልን ታናሽ
ተከትላው ሄዳ
እሱም  እሷን ወዶ
እሷም እሱን ወዳ
"ወላሂ" እንደሚላት
ስትለው "ማርያምን"
ተቻችለን ሲሉኝ
ሰምቼ እንዳላምን
ለነሱ እኔ ጨንቆኝ
መሃል ስብሰለሰል
ዘገየች ልጅቱ
ሊያስቀራት ሊያስቀራት
ሊያስቀራት ነው መሰል

ዘማርቆስ
@wogegnit

@getem
@getem
@paappii
👍4026😁9🔥5👎2😢2😱1
የቀናልህ
የሞላልህ
ባለ ካባ
ባለ ሞገስ
ስምህ ዘመን አልፎ
ምዕተ ዓመት የሚዳረስ
አዋቂ
ታዋቂ
ያደረጀህ ነዋይ
በራሪ በሰማይ
ደስታህ የሚተመን ፣ ሆኖልህ አለቀጥ
በከፍታ እርካብ ፣ ክብርህ የሚያስቀምጥ ፤
ውብ እና ሸበላ
ዓይነ ውብ ከብላላ
ዘርህን ያበዛህ ፣ በብዙ መሰጠት
መናዋን የበላህ ፣ የምድርን በረከት ፤
ሁሉህ ሙሉ
እጅህ ያለ ፣ የዓለም ውሉ …
መሆንህን አይቼ
የማልገረመው
“ከዛስ ?” ብዬ ሳስብ
ትርጉም ቢያጣብኝ ነው ።
እሺ ከዛስ ?
አንተ አላፊ !🤔

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
👍36😁43😢2🔥1
ኧረ በቃኝ ይሄስ ዓለም
ቀኔ ጎድሏል ሙሉ አይደለም።
ልሂድ ልግዛ ፣ አንዲት ገመድ
ልጓዝ ልብረር ፣ በሙት መንገድ።
ያስከፋኛል አገዛዙ ፣
ዙሪያው ገባው አያያዙ
የሰው ክፋት ጉድ ፣ መዘዙ
አላፈራም … ከምዘራው
እንባዬን ነው የማዘራው።
:
ልሂድ በቃ ልሰናበት…
ዘመኔ ላይ ልፍረድበት …
አንዲት ገመድ ላንዲት አንገት
በሽንቁሯ ልለፍበት ፤
ብዬ ጀመርኩ የሙት ጉዞ
ልቤ ቀልቤ ተመርዞ … ።
:
ግና ከንቱ…
ምን ዋጋ አለው?
:
አገኘኋት ስረማመድ
ያቺን ሸጋ ልጃገረድ
ገለጠችው ያንን ከንፈር
ይኸው ሳቀች ለክፋቱ
ልኑር በቃ ምናባቱ!

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
78👍51😁18🎉5👎3🔥3🤩2
‘ጥፍራም ነህ ‘ ስላለኝ
ተቆረጥኩት ጥፍሬን
‘አርጅቶ ነው ‘ ሲለኝ
ጣልኳት ከዘራዬን ።
ያኔ ተናነቀኝ …
ጥፍሮቹን ሞርዶ ፣
በትር ይዞ ዱላ…
ምኔን ይዤ ልትረፍ?
ከታለልሁኝ ኋላ!

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
54👍23😁8🔥5🎉2😱1
አንዳንዱ በመሀል ገብቶ ይሄስ ነዉር ይለኛል
ተምራ ብለዉ ያሙኛል
እኔ ምን ይጨንቀኛል?

ብቻ………………..

ያገባ ባል ፈልጉልኝ🤗

በነገር ሲጠበስ ኖሮ ትዕግስት የተሸለመ
የት ገባህ የት ወጣህ መሮት ከሶፋ የተሰየመ

ያገባ ባል ፈልጉልኝ😒

አማቱ በአሽሙር ቄንጧ መፈጠር ያስረገመችዉ
የአከራዪ ልጅ በግልምጫ የጨረሰችዉ።

ያገባ ባል ፈልጉልኝ😌

ጏረቤት ዉለድ እያሉት በምክር የጠነከረ
በኑሮ ብዙ የተማረ
ያለእድሜዉ የተሰበረ

ከኔ በአምስት የፙበልጥ
ባይኖረዉ በኔ የሚያጌጥ

በጭራሽ ግን ከምሽቱም ያልፈታ
የሚያከብረኝ አዳማጩን ይስጠኝ ጌታ።

በኔ ቢካስ
ይሁን ብሎ…………..


ላግባዉ
ላኑረዉ
ላቆየዉ ከቢሮዬ
ማማከር ነዉ ስራዬ😇

ትምጣ እሷም
ላግባት
ላቆያት በቢሮዬ
ማስማማት ነዉ አላማዬ😇

በትዝታ ወልዴ ✍🏽


@Tizita21
@getem
@getem
👍4628😁17🔥5
ወይኑ ጐምርቶ ባናይ
ምን በለሷ ባታፈራ
የዘራነዉ ጭንጫ ቢቀር
ህልማችን ቢወርድ መቃብር
ምድር ፍሬ ከልክላ
ብናጣም ጥጋት ከለላ

ተመስገን!
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::


💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)

@getem
@getem
42👍30🔥7🤩1
መጣለሁ
  በናፍቆት አክናፍ ስከንፍ
ያስለመድሽኝን .. , ውብ አይንሽን
ዳግም ላተኩር  ልተክዝበት
ህይወት ውጥንቅጡን
ዳግም ላዘግም ልዘብትበት

መጣለሁ

ከሳቅ  ነው ? 'ሳሳቅሽ ?
ገላሽ ነው ጠረንሽ  ?

ይህነው በማልልሽ
ይሄ ነው በምልሽ
በሂ አፈጣጠርሽ



መጣሁ
መጣሁማ

ሀሴት ላደርግበት

ቅኔ  ልቀኝበት

አኮኬት
አኮቴት አኮቴት ልልበት ።




መሳት ሳያስትሽ
መጠርጠር  ሳያይሽ
መርሳት ትዝ ሳይል
መልመድ ሳይሰውርሽ
ጥቂት ጥቂት
ብቻ





ግን ግን
እንድያው የድንገት
እኔን ስጠብቂ
ቢመስልሽ  የምቀር
ይህንን አስቢ

ሌት ለሺህ ሰከንዶች
ታብዮ ቢጨልም
ምድር አይኗን መግለጧ
ፀሀይ መፍለቅለቋ
መንጋቱ እንደው
አይቀርም።


ስትሰጊ  ቢከፋሽ
መጠበቅ ቢደብት
ተስፋ ቢያሳጣሽም
ጥበቃ መቆርፈድ
እድሜን ማንደድ
መክሰም
ሆኖ ቢታይሽም


ደሞም
ደሞም

ልትተይኝ ብትይ,
ብትረሽኝም ደሞ
ሌላ ልትለምጅ።

ቃሌን 'ዳትዘነጊ
መጣለሁ
መጣለሁ
እምነትሽን አትጭ ።

By ሚክያስ አለምሰገድ

@getem
@getem
@paappii
28👍24👎3🔥1
ያ ስንት  ያልንበት
ስንት  ያልነት
ጊዜም
ለጥቆ ነጎደ


ወዳጅም ባይሰምርለት
ላንድኛው
በሞት መራቁን ወደደ

ልብም ማስታመም ባይችል
መዘንጋት
መርሳትን ለመደ ።

አቤቱ


ጊዜ ስልቱ
ተዘነጋኝ
ያለፈው ካለው
ተማታኝ
ወደ ፊት አልመስልህ
አለኝ ጨነቀኝ
ወደ አንተ ቀና ከማለት
አስጨከነኝ ።

ዛሬን ማረኝ አልልህም
ትናንት ያልሆነልኝን ?
ስታውቀኝ ?

ይልቅ


እስኪ እባክህ
ተለመነኝ
አንድ ጊዜ ለማለፍ
አስር አትፈትነኝ
ዛሬን ተዋትና
ሌላ ነገ ስጠኝ።


....................

ሚክያስ አለም ሰገድ

@getem
@getem
@paappii
👍3113🎉2
እናንተ የምወድዳችኹ ፤
ስነ-ፅሁፍን የምትወድዱ ፤
የግጥም ነፍስ ያላችኹ ፤
ወንድሞቼ ፤ እህቶቼ ፤ ወዳጆቼ ፤ ታላላቆቼ እና በደስታዬ ደስ የሚላችኹ የዘመን ተጋሪዎቼ ኹሉ ፤ ይቺን የመጀመሪያ ስራዬን ቅድሚያ ገዝታችሁ ፤ ከጓዳ ወደ አደባባይ እንድትሸኙልኝ ስል ፤ የተወደደ የወዳጅነት ግብዣዬን እጋብዛችዃለሁ ።

ከወዲኹ ...
እጅግ እጅግ አመሰግናችዃለሁኝ
ኑሩልኝ !
ቴዎድሮስ ካሳ

____

የመፅሐፍ ቅድመ ሽያጭ ማስታወቂያ
Reserve yours now—it's on pre-order!

ርዕስ /Title - የዱር አበባ / Wild Flower
ዘርፍ / Genres - ስነ-ግጥም /Poetry
ዋጋ/ price - 300 ብር/ birr

የባንክ ቁጥር / Bank Accounts :
ቴዎድሮስ ካሳው አስረሴ
Tewodros Kassaw Asresse
ንግድ ባንክ / CBE - 1000360039847 ወይም 1000292025185 (ናትናኤል እሸቱ)
አዋሽ ባንክ /Awash Bank - 01320885596200
ሲቢኢ ብር / CBE Birr - 0972338625
ቴሌብር/ Tellebirr - 0972338625

[ ማሳሰብያ : ዃላ ለማስታወሻ ይረዳኝ ዘንድ Screenshot አንስታችሁ በውስጥ በሜሴንጀሬ አልያም በቴሌግራም አድራሻዬ @Poet_tedi መላኩን እንዳትረሱት ይሁን ።]
👍23🔥65
34👍12🔥3
# ይድረስ ለጨረቃ #
እንዴት ነሽ ጨረቃ
እንዴትነሽ በሰማይ
ምን ይታይሻል
ምን አለ ምድር ላይ… ?
በየጉራንጉሩ ሰው ነውሩን ደብቆ
የሚሰራው ስራ ህሌናውን ሰርቆ
ይታይሽ ከሆነ ሴራ ሲጎነጎን
የመከራ ጎጆ ሲሰራ ሲጠግን
የክፋት እንጀራ ሲቦካ ሲጋገር
የልቦና ቁስል ሲማገር ሲታጠር
ንገሪኝ በሞቴ ይገለጥ ጉዱ
የሰውልጅ ዶሴ የበደል ሰነዱ
እኔም ልናገር ልመስክር ለፍርዱ ።

@topazionnn
@getem
@getem
42👍29🔥8😁1
እኔ ያንቺ አለም
ደብዘዝ የምል ደማቅ ቀለም
የምተጋ ነገን ማልም
ለኔም ላንቺም የምሆን ህልም
ተዛምደናል ኪዳን መተን
መሃላችን ለቃል ሰተን
ነበርሽ የኔ ብርቱ ወገን
ጥንካሬሽ አንድ ያረገን

ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
የሄድሽበት ከኔ ይርቃል
ረስተሻል መሃላ ቃል
የኔ ገላ ያልታደለ
አንቺን ልኮ ባዶ አደረ
ደህና አድሯል ወይ ያንቺ ገላ
ባሉን ትቶ የተዳራ
ሽሎሽ ነው ወይ ከኔ እሱን
ቃል ማሃላን ማፋረሱን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
አንድን ይዞ ሳይራቡ
ምን ይሉታል መደረቡ

ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍5311😢3🔥2😱2🎉1
እልፍ ስትል እልፍ አበሳ ሄድ ስትል ጉድ ጭካኔ በመንገድህ ለሚነጉደው
ምን ለማትረፍ ምን ለማግኘት እርምጃህን 'ምትቀጥለው
ወዴት ይሆን ህይወቴ ሆይ የምትሄደው
የብቻነት የስቃይ ቤት ምን ይሆን ‘ምትፈልገው
እዚህ የእንባ ጎርፍ ውስጥ አለምን ከሰራት
ብትሰምጥ ብትሞት እርሷን እንደው ይቸግራት?
ደስታ ፍለጋ ‘ምትባዝን ህይወቴ ሆይ
ከንቱነት ነው አንተን ‘ሚቆይ
አንተ አበባው በሜዳህ ላይ የምትስቀው
አንቺም ወፏ ከዛፍሽ ስር ተደብቀሽ 'ምታለቅሺው
ፍፃሜያቹ ለካ አንድ ነው
ለማይዘገን ጥቂት ደስታ ዞሮ እንደ ጉም ለሚበነው
በስለቱ በጫፉ ላይ አየዘለልክ 'ምትጨፍረው
.....አንተ እኮ ነህ የምትደንቀው


Translated from "hymen of death " the movie

By yodan

@getem
@getem
@getem
👍339🔥1😢1
ተራራ የሆነብንን የዳህንበትን አቀበት
እየናጠጡ እየፈረጠጡ ተንደረደሩበት

መስከኛ  ያለውን    ለም መሬት
ፎሮሹ   ፈጩበት
ወቁ ሰለቁበት


አደራ  አማን ብለን ሳለ
አልተዘገረ
አልተመተረ
ከተባለ
አኑር ጠብቀን   ብለን ሳለ
ከሆነ የሞት ሹም
አይሳሉ ስለት   ለሞታችን የተሳለ

ተመርቆለትም ከኪሎው ካለየ
ወደ ተመዛኙ ካላዘነበለ 

አይጠረጥርም ወይ
ምንም ያልጠየቀ   ?

ክሳት ገፅ የለውም 
አጥንት ካልገለጠ ?


ነገር  ነገሩን ቢለይም
ምኑን ከምኑ
ውል ያልያዘ ሰው
ቢመሽበትም  አይነጋለትም

ዘንድሮም ዘንድሮ ተባለ
ሹም ሽረቱ ፍርዱም ተሻረ
ውሸቱ ሲፍም  እውነት ከሰመ

ጊዜ ለሁሉ መልስ ቢያኖርም    
ምኑን ከምኑ
ውል የተሳተው
ቢመሽበትም   አይነጋለትም

By mik

@getem
@getem
@paappii
👍329🔥1
ስምን መሄድ ጥሎ
ከታሪክ ተካፍሎ
አሸብርቆ መኖር
በወርቅ ተጠቅልሎ ፤
ዘርን በመተካት …
ወዳጅን በማፍራት
የምድር መናዋን
ብዙውን በመብላት
ሸጋውን በመልበስ
ፋሽን በመጫማት
ማርሴዲስ መኺና
ሸምቶ በመንዳት
ነው እያልን ስንኖር
መለኪያ ፣ ሚዛኑ
ሁሌ በየቀኑ…
ከልብ መሳቅ ኖሯል
የስኬት ተመኑ !

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
27👍20🔥6🤩2
ጭጋጉ ሲያከትም በክረምቱ ማብቂያ፤
ፀሐይ ስትፈነጥቅ በመሬት መድረቂያ፤
የፀደይ አበባ ማበብ ስትጀምር ፤
አደይዋ ለሰዎች ተስፋን ስታበስር፤
በወርሐ ጥቅምት በመጀመሪያው ቀን፤
ዛሬን ነዉ የወጣሁ ከእናቴ ማኅፀን።

ያቺ እናቴ በጭንቋ ቀን ምጧ ደርሶ፤
እያነባች ላብ አጥምቋት ፊቷ ርሶ፤
ማርያም ማርያም እያለች፤
ምጧ ቀለለላት ስሟን እየጠራች።

በልደቷ ቀን መታሰቢያ.........
ሰምታ ጸሎት ስዕለቷን፤
ማርያም ማረቻት እናቴን።
በዚያች ሴኮንድ በዚያች ቅፅበት........
ከልቤ ታትሞ ማርያም የሚለው ስም፤
ለዛሬ ደረስኩኝ በፍቅሯ ስሸለም።

የእቅፏን መዓዛ እየመገበችኝ፤
የትህትናን ዋጋ እያስተማረችኝ፤
የልጇን ጌትነት በልቤ ሰሌዳ፤
የእርሷን ትሁትነት በፍቅር አዋድዳ፤
የንስሐ እድሜን ፈጥና አሰጠችኝ፤
አዲስ ቀንን እንዳይ ድንግል ባረከችኝ።
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎊🎊🎊🎊
ዔደን_ታደሰ @ediwub
ጥቅምት ፩/፳፻፲፯
መልካም ልደት ለእኔ🎂🎂🎊🎊🎊
@getem
@getem
@getem
70🎉27👍24🤩4