ግጥም ብቻ 📘
64.2K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
የተቀነጨበ

ጨዋታ ከሳቅሽ
ከለዛ አንደበትሽ ተደማምሮ ሳለ
ከተፈጥሮሽ እንጂ ከልብሽ ምን አለ?
.
.
.
እንጃልን እኛማ
ላወጋልን ሁሉ
ለሳቀልን ሁሉ ሞትን ካልንማ።

ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
30👍22😢5🔥1
ሲኖር የሚገርመኝ
አይደለም እንደ ሟች
ይሄ ሁሉ ተጓዥ ፣ ይሄ ሁሉ ዘማች ፤
ሁሉም ጥሬ አሳሽ ፣ ስብስብ ነው የዶሮ
አነር ያድነዋል ፣ እንደ ዱር መንጥሮ።
ከስብስቡ መኃል ፣ ባለቀን ሲነጠቅ
ሌላው ዶሮ ይጮኃል ፣ ፈርቶ በመሳቀቅ።
ሲሞላ ግን አፍታ
እየው አበክረህ
ወንድሙን የሸኘ
ያን አልቃሻ ዶሮ
ጥሬ ይናጠቃል
ዛሬም እንደ ዱሮ።
አይገርምም ?
አይደንቅም?
የሞት ማግስት ወጉ
አነርን ይረሳል የዶሮ ዝንጉ።
🐓

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
33👍28🔥7🎉1
በሰዉ ዘንድ መገፋት፤
ደግ ፊት መነሳት፤
እስከ ጥግ አዉቃለሁ.....
ክፉ ደግ ያሳለፍን፤
ጎረቤቶቼ እንኳን፤
ያለፍኩ እንደሆነ ድንገት በበራቸዉ፤
እንደዚህ ይሉኛል ቃል እያጠራቸዉ፤
ምኑን ቢያቀምሷት፤
በምን ቢመርዟት፤
አልባሷን ቀዳዳ ጎዳና የወጣች፤
ከሰዉ ተነጥላ ብቻዋን ያወራች፤
እርሷ እኮ እንዲህ ነች እያሉ፤
ምኑንም ሳያዉቁ ፍርድ ይበይናሉ፤
ፍፁም ሰላምና ጤንነትን ሽቼ፤
ራሴን አገኘሁ ከገዳም ሰንብቼ፤
እናም አካላቴ እዉነት ናፍቀኸኛል፤
በክንድህ መሸሸግ እቅፍህ ያሻኛል፤
ትዝ ይልሃል አይደል......
የኔ ልብ ካንተ ያንተም ልብ ከኔ፤
በፍፁም ተጋምዶ በፍቅራችን ቅኔ፤
ለሰርጋችን ድምቀት እቅድ ስናወጣ፤
ነጠላ አጣፍተን ተሳልመን ስንመጣ፤
ትዝ ይልሃል አይደል......
ለዚህ ያደረሰኝ ቤተሰብ ጓዳዬ፤
ስንት የደከምኩበት ፍቅርና አላማዬ፤
ትናንት በጉያዬ በእጄ የነበረ፤
ተስፋ ያደረኩት መና ሆኖ ቀረ።
ማነዉ ተጠያቂ ልቤ ለመድማቱ
እዉነተኛ ደስታ ከእኔ ለመጥፋቱ
ማነዉ ተጠያቂ?????
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
😢23👍206🤩1
እንደ ተበዳይ አታልቅሺ
ለበደል ነበር አመጣጥሽ
ፀባይ አመልሽን ማጣፈጥሽ
እስስት ውስጥሽን መለወጥሽ

እንደ ንፁህ ሰው "እሪ" አትበይ
ባገር በሰፈር አታሳጂኝ
የሳልሽው ብረት በላሽ እንጂ
እቅድሽ ነበር ልትጎጂኝ

የዋህ አልነበርሽም እንዳሰብኩሽ
ጅል አልነበርኩም እንዳሰብሺኝ
አባዝተሽ ከኔ ለመውሰድ ነው
ሽሙንሙን ፍቅር የሰጠሺኝ

ፍቅርሽን ይዤ ዝም ብልሽ
ከእብድ አየሺኝ ከወንበዴ
ክፉ ሰው ሆንኩኝ ልትሄጂ ስል
ቀድሜሽ እኔ በመሄዴ

እሰይ ደግ አረኩ
የኔ አስመሳይ
ብትቀበሪም ፡  አላምንሽም
እምባሽ ላይ ሳቅሽ ይታየኛል
ውሸት አትፈሪም እየማልሽም
ድራማሽ ይብቃ ተነቃቃን
ከበቀል ጠጪ ከእልሁም
መለየት መርሳት እችላለው
እንደ ወንዶችሽ አይደለሁም!

እንዲያ ነው ብለሽ አውጂልኝ
ይሄ ጥቅስ አለ ከኔ ዘንዳ
"ደግ ነው በዳይ የሚያስለቅስ
  ብፁዕ ነው ክፉ  የሚጎዳ!"

እሰይ ..
እንኳን ጎዳሁሽ
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
48👍19🔥9
👍4420🔥4😱2
ሲሸሹኝ ስጎትት ሲርቁኝ ስጣራ፤
ሲሄዱ ስከተል ሲዘጉኝ ሳወራ።

አሁንስ ዝም አልኩኝ ልቤን ደካከመው፤
ሁለት እየሆነ አንድ ነው ያልኩት ሰው።

ብቻ በመንገዴ፥

ከነሳቸው ሠላም ከነሳቸው ጤና እኔ መከተሌ፤
ለበደለኝ ሁሉ ለበደልኩት ሁሉ ይቅርታ ነው ቃሌ።

ሄጃለሁ ከእንግዲህ በቃ ለልከተል🚶‍♀‍➡️🚶‍♀‍➡️🚶‍♀‍➡️🚶‍♀‍➡️🚶‍♀‍➡️

ጦቢያ

@getem
@getem
@getem
👍6021🤩2
የቱ ጋር መሰለህ…
(ሚካኤል አ)

መባቻ ጅምርህ
የነፍስህ ድባቴ
ውድቀት እንግልትህ
ያኔ …
ባሽትሪ መያዣ ፣ በሲጋራ ብናኝ
በርጋፊ ቅጠል ፣ ድባቧ የሚቃኝ
በዛች ጠባብ ክፍል
ምጥን መሰብሰቢያ
ዙሪያህን ሰው ሞልቶህ
ቀንህን ማጣፊያ
ለአፕላይ ግብዣ የተዘረጋች ጣት
በሚግተለተል ጢስ ፣ ሰንቃልህ እሳት
እሷን ለመቀበል ስትፈግግ ባ’ክብሮት
የሰበብ አስባብ ጢስ
ቀረ ቤትህን ወርሶት።
የቱ ጋር መሰለህ?
በቀይ መብራት ፍካት
በቅልቅል ሽቶ አዲስ አይነት ክርፋት
በጭላጭ ብርጭቆ ተላኮበት ድራፍት
ከስፒከር ማህፀን ሙዚቃ ተለቆ
ጭፈራ እና ዳንሱ አንድ ላይ ተዛንቆ
የቀይ ሴት ታፋ ዓይንህ በስስ ሰርቆ
በምራቅህ ድርቀት ጉሮሮህ ተጨንቆ
ጠቅሰህ ስትጠራት
ያቺን የሞት ብልቃጥ
ከባቷ ፈልቅቀህ ዕፅዋን ስትቀምሳት
በገላህ ፍሰሀ መቅደስህን ናድካት ።
የቱ ጋር መሰለህ?
የልጅነት ልምድህ
ከሰንበት ቤት ገዳም
ምልልስ ብርታትህ
በሀይኪንግ ሲቀየር
የያሬዱ ወረብ
በእስክስታ ሲዛወር
ሳትቆም ለፀሎት
ሳይንስ ከእምነት ልቆት
ኒቼ ቦታ ሲወርስ የየኔታን መንበር
የነፍስህ ቁዘማ መንደርደሪያ ነበር።
ትዝ አለህ?
ዘር መራጭ ስትሆን
የደም ሴል መንጣሪ
ጆሮህ ዳባ ሲለብስ
ለፍጥረት እንግልት
ለህፃናት ጥሪ…
መንገድህ ሲሳለጥ
በ V 8 መኪና
ዝርግ አስፓልት ሲመስልህ
ጉርብጥብጥ ጎዳና ፤
ስቆልኛል ስትል ጥርሱን የነከሰ
እንባው አንሸራሽሮህ ጌታ ዘንድ ደረሰ።
ምላሹስ የከፋው መቼ ላይ ሆነና?
ጥሬ እየቆረጥክ ሆድህ ሲመረመር
እስቲም ሳውና ገብተህ ፊትህ ሲጭበረበር
በድሎትህ መኃል
ገላን የሚያኮስስ የእሾህ ስንጥር ነበር።
ትዝ አለህ?
መኝታህ በምቾት ተሞልቶ በአጀብ
እንቅልፍህ ሲናጠብ?
ትዝ አለህ?
በውድ ቀለም ቤቶች ልጆችህ ሲማሩ
ከግብረገብ ታዛ ተናንሰው ሲቀሩ?
ትዝ አለህ?
የጉያህ መልካም ሴት
የአጥንትህ ፍላጭ
አሁን ከምን ጊዜው
ሆነችብኝ ምላጭ?
ብለህ ስትቆዝም …
እንዲያ ነው አይዋ
ግፍ ፅዋው ሲሞላ
በትሩን አይመርጥም።
ትዝ አለህ?
ታወሰህ?
የቱ ጋር መሰለህ?
የተፈታው ውሉ
የጎደልክ ከሙሉ
ኧረ ስከን ሲሉ
ከዕድሜ የተማሩ
የጋሽ ውቤን ምክር
የእመት ጉሌን ዝክር
ረግጠህ ስትበር…
ስትሻገር ፣ ስጥስ
የምስኪናን ድንበር
የዛሬ ውድቀትህ ፣ በግጥም ሊነገር
ክንፍህ የተመታው ይሄን ጊዜ ነበር።
ትዝ አለህ?

አዎን እሱ ጋር ነው!

@getem
@getem
@getem
30👍20
በቅንድቧ ባይኗ በኩል
አልተቀባም አንዳችም ኩል
አልደረበች ማዳመቂያ አልፈጠራት በጎደሎ
ያኖረልን በግሩምታ ንፁህ ልቧን አስመስሎ
የሰው ሰራሽ ቅርፀ ብዙ
         አሎዞራትም በአካሏ
በክፋት የማትኖር
          ትሁት መልሰ ቃሏ

ያቹት......እርሷ!


ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
45👍15🔥1
👍23😁16🤩166🔥1
ቤትህ…
በመኃልይ ልባስ
መልኩን የደበቀ
መልከኛ እዬዬ ገባ ተሸሽጎ
ለደጅህ የላኩት
እንዳማረ በቃ ላደባባይ ሸንጎ።

በተመስገን መዳፍ
በቡራኬ ከንፈር
ወደሰማይ ያልኩት ተቀላቅሎ ካ’ፈር
ለጓዳዬ አይበቃም እንኳንስ ለጠፈር።
አንተው በጣቶችህ
ጣራ ስር ከቀረ ዋይታዬ ስር አንሳኝ
ወይም ጸሎት ንሳኝ።

ዘመን ቢተራመስ እድሜ ቢቀናጣ
እንባዬ ቢጋለጥ ደስታዬ ቢሰጣ
አደባባይ መውጫ ግጥም ብቻ አልጣ።

@getem
@getem
@paappii

By Yadel Tizazu
👍3710🔥5😱3🤩1
አካሄድ

የስንፍናን ጡዘት
ካንሸዋረሩበት
ከአካሄዱ ጀርባ
ሀፍረትን ቢመርጡም
ወደው ለሄዱበት
ነፃነት አይቀሙም
...
ግና................
ተዘክረው ቢመጡም
እንደአካሄዳቸው
ምህረትን ፍለጋ
ዳር ዳር ቅኝታቸው...
ልዝቡን ሹክሹክታ
ሽቅብ ቢያደምጡም
ባልኖሩት ንሰሃ
ፍቅርን አያቀልሙም።

           By ኢያሱ ከበደ
           መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም
            @josheyasuu

@getem
@getem
@getem
👍1311🔥4
የኔ ዓለም!
(ሚካኤል አስጨናቂ)

እንዳንቺ 'ሚጣፍጥ - አንጀት የሚያረካ
ጣፋጭ የለም ለካ!
ጥዑም ናቸው ያሉኝ ማርና ቸኮሌት
ካንቺ ሲነፃፀር ፣ መረሩኝ እንደ ሬት።
.
ማርያምን !
.
ከድምፀትሽ ልቆ - 'ሚሰማ ሙዚቃ
ከአንባሰል ከባቲ ከብሉዝ ትዝታ
ወድያም ከብሉዙ ፡ ደግሞም ከአፍሪቃ
አንድም የለም በቃ!
.
ማርያምን!
.
እንደውም ፣ እንደውም
ካንቺ ጋራ ስሆን ሀዘን ጭንቄን ሽሮ
የደስታ ወሰኔን ፣ አለቅጥ አንሮ
የሚገርመኝ የለም ከዓለሟ ተፈጥሮ።
.
እውነት አይገርመኝም !!
ይኸው ለምሳሌ...
ያቺ የሰማይ ሳህን
ምንድናት ጨረቃ?
እንዲያ ስትሞገስ
ተስላ ፣ ተፅፋ
በሁሉ ተደንቃ...
አንቺን ያየሁ ጊዜ
ዓይኔ ውስጥ ከሰመች
ተዋርዳ ፣ ተንቃ።
.
ማርያምን...
የቱ ኮሜዲ ነው የትኛው ቀልደኛ
እኔን የሚያደርገኝ የወሬው ምርኮኛ?
ደግሞ ካንቺ በላይ
እኔን ለማሳሳቅ ማነው የሚደፍረው ?
ባንቺ ጨዋታ ነው
የተደበቀውን.. . ጥርሴን የምገልጠው።
.
ማርያምን !
እንደውም ባጭሩ.. .
አሁን ይሄ ግጥም
የቃላት ጥርቅም
እጅግ መሳጭ ሆኖ አንባቢው ቢያደንቅም
ካንቺ ግን አይበልጥም።
.
ማርያምን።

@getem
@getem
@getem
👍7232😁8🤩5🔥2🎉1
የመዳፌን መሃል
ነክቶኝ መሃል ጣቷ
አሰፈረችብኝ~'ማይነቀል ቆሌ
ከአያት ቅድም አያቷ
(ክ...ፋ...ቷ!)
አልል ጥፍሯ ወጋኝ
ተቆርጧል ባጭሩ
ምን ብትቋጥርበት
ጣቷ መናዘሩ
ሀጥያት ማስዘርዘሩ...
ነፍስ ማስገበሩ...
የእንጨት አፍሮ አይገቤ
የመቅደስ ስር እጣን
ጩህ ጩህ እንደሚለው
ትዕቢተኛ ሰይጣን
እሪ ልል ስነሳ
ለአፍታ በነካችኝ
ጉሮሮ እንዲከዳኝ
ከንፈር ደገመችኝ

(ጉድ እሷ!)

መቼስ በሀገር ታሪክ
እኛ በምናውቀው
እንጂ ነጭ ሲወር
ምድሩን ሲያስጨንቀው
መዳፉን ተስሞ
እስኪጠፋው አለም
ለጠላቱም ቢሆን
እጅ ያልሰጠ የለም

(እንኪ እጅ ጀብኣ በይ!)

ዘማርቆስ
@wogegnit

@getem
@getem
@paappii
👍5821🤩7🔥5
የወራት ዘመኑ ቀኑ ተቆረጠ
የማህፀኗን እቅፍ በጊዜ አሳቦ
ሆዷን ረገጠ

በ 18 ምሽት
ለ 19 አጥቢያ ቀኑ ከረፈደ
ማርያም
ማርያም..... ሲባል ዮኒ ተወለደ
🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂🎂
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳
🥳@getem
🥳@getem
🥳@getem
🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳

12:35 PM

🎂@yonatoz🎂
ዮኒ
ኣታን
🎉14450👍41🔥5🤩4👎2
ገጣሚው
ማንም ያላየውን
ማንም ያልፃፈውን
በፊት ያልነበረ …
ስንኝ ለማዋቀር
መወጠን ጀመረ ።
ሆኖም ግን አንድ አጣ
ያልተፃፈ በሰው
ሁሉን ቢያሰላስል
ቢያወጣ ፣ ቢያወርደው
አንድም አልነበረ
ሌላው ያልጀመረው ።
አሰበ ገጣሚው
አወረደ ፣ አወጣ
አዲስ ነገር ልፃፍ
ብሎ የጀመረ
ገጣሚ ግን አጣ።
እናም ይሄን ጊዜ
የሱን ክታብ ሲቃኝ
ቀለሙን ሲያዋድድ
ከዝርጉ ወረቀት
'አዲስ ነገር ልፃፍ'
የሚል ነበረበት ።
ስንኙ አበቃ
ብዕር ተሰለበች
ታጠፈች ወረቀት
ግጥም ቀን ወጣላት ፤
አዲስ ነገር ፃፈ
አዲስ ነገር ልፃፍ
ብሎ በመነሳት ።

(ሚካኤል አ )

@getem
@getem
@getem
👍5317🔥10😱3😁1
የቢላልን ታናሽ
ተከትላው ሄዳ
እሱም  እሷን ወዶ
እሷም እሱን ወዳ
"ወላሂ" እንደሚላት
ስትለው "ማርያምን"
ተቻችለን ሲሉኝ
ሰምቼ እንዳላምን
ለነሱ እኔ ጨንቆኝ
መሃል ስብሰለሰል
ዘገየች ልጅቱ
ሊያስቀራት ሊያስቀራት
ሊያስቀራት ነው መሰል

ዘማርቆስ
@wogegnit

@getem
@getem
@paappii
👍4026😁9🔥5👎2😢2😱1
የቀናልህ
የሞላልህ
ባለ ካባ
ባለ ሞገስ
ስምህ ዘመን አልፎ
ምዕተ ዓመት የሚዳረስ
አዋቂ
ታዋቂ
ያደረጀህ ነዋይ
በራሪ በሰማይ
ደስታህ የሚተመን ፣ ሆኖልህ አለቀጥ
በከፍታ እርካብ ፣ ክብርህ የሚያስቀምጥ ፤
ውብ እና ሸበላ
ዓይነ ውብ ከብላላ
ዘርህን ያበዛህ ፣ በብዙ መሰጠት
መናዋን የበላህ ፣ የምድርን በረከት ፤
ሁሉህ ሙሉ
እጅህ ያለ ፣ የዓለም ውሉ …
መሆንህን አይቼ
የማልገረመው
“ከዛስ ?” ብዬ ሳስብ
ትርጉም ቢያጣብኝ ነው ።
እሺ ከዛስ ?
አንተ አላፊ !🤔

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
👍36😁43😢2🔥1
ኧረ በቃኝ ይሄስ ዓለም
ቀኔ ጎድሏል ሙሉ አይደለም።
ልሂድ ልግዛ ፣ አንዲት ገመድ
ልጓዝ ልብረር ፣ በሙት መንገድ።
ያስከፋኛል አገዛዙ ፣
ዙሪያው ገባው አያያዙ
የሰው ክፋት ጉድ ፣ መዘዙ
አላፈራም … ከምዘራው
እንባዬን ነው የማዘራው።
:
ልሂድ በቃ ልሰናበት…
ዘመኔ ላይ ልፍረድበት …
አንዲት ገመድ ላንዲት አንገት
በሽንቁሯ ልለፍበት ፤
ብዬ ጀመርኩ የሙት ጉዞ
ልቤ ቀልቤ ተመርዞ … ።
:
ግና ከንቱ…
ምን ዋጋ አለው?
:
አገኘኋት ስረማመድ
ያቺን ሸጋ ልጃገረድ
ገለጠችው ያንን ከንፈር
ይኸው ሳቀች ለክፋቱ
ልኑር በቃ ምናባቱ!

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
78👍51😁18🎉5👎3🔥3🤩2
‘ጥፍራም ነህ ‘ ስላለኝ
ተቆረጥኩት ጥፍሬን
‘አርጅቶ ነው ‘ ሲለኝ
ጣልኳት ከዘራዬን ።
ያኔ ተናነቀኝ …
ጥፍሮቹን ሞርዶ ፣
በትር ይዞ ዱላ…
ምኔን ይዤ ልትረፍ?
ከታለልሁኝ ኋላ!

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
54👍23😁8🔥5🎉2😱1
አንዳንዱ በመሀል ገብቶ ይሄስ ነዉር ይለኛል
ተምራ ብለዉ ያሙኛል
እኔ ምን ይጨንቀኛል?

ብቻ………………..

ያገባ ባል ፈልጉልኝ🤗

በነገር ሲጠበስ ኖሮ ትዕግስት የተሸለመ
የት ገባህ የት ወጣህ መሮት ከሶፋ የተሰየመ

ያገባ ባል ፈልጉልኝ😒

አማቱ በአሽሙር ቄንጧ መፈጠር ያስረገመችዉ
የአከራዪ ልጅ በግልምጫ የጨረሰችዉ።

ያገባ ባል ፈልጉልኝ😌

ጏረቤት ዉለድ እያሉት በምክር የጠነከረ
በኑሮ ብዙ የተማረ
ያለእድሜዉ የተሰበረ

ከኔ በአምስት የፙበልጥ
ባይኖረዉ በኔ የሚያጌጥ

በጭራሽ ግን ከምሽቱም ያልፈታ
የሚያከብረኝ አዳማጩን ይስጠኝ ጌታ።

በኔ ቢካስ
ይሁን ብሎ…………..


ላግባዉ
ላኑረዉ
ላቆየዉ ከቢሮዬ
ማማከር ነዉ ስራዬ😇

ትምጣ እሷም
ላግባት
ላቆያት በቢሮዬ
ማስማማት ነዉ አላማዬ😇

በትዝታ ወልዴ ✍🏽


@Tizita21
@getem
@getem
👍4628😁17🔥5
ወይኑ ጐምርቶ ባናይ
ምን በለሷ ባታፈራ
የዘራነዉ ጭንጫ ቢቀር
ህልማችን ቢወርድ መቃብር
ምድር ፍሬ ከልክላ
ብናጣም ጥጋት ከለላ

ተመስገን!
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::


💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)

@getem
@getem
42👍30🔥7🤩1