ለእርሱ Multimedia
965 subscribers
45 photos
4 videos
8 links
Download Telegram
Kingdom Sound 9th Batch Registration has started.

The main purpose is to give spiritual and technical training for singers and musicians.

- We will inform you by telegram when the training will start.

- You can use the telegram link @KingdomSoundBot to register

- You can scan the QR code on the poster too

For more information please call

+251939592385
Forwarded from Mulu Multimedia
John 15:13
Greater love hath no man than this, that a man lay down his life for his friends.

የዮሐንስ ወንጌል 15:13
ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።
👍7
Forwarded from Kingdom Sound Public
ድንቅ ስጦታ

የአምልኮ ምሽት
📌ቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን
      Ketena Hulet Full Gospel church

Date : Sunday, Dec 22 2024
          እሁድ ታህሳስ 13 2017

‼️🕔ከ10:00 ጀምሮ

ኑ!  እግዚአብሔርን አብረን በዝማሬ እናምልክ
1
መልካም ሰኞ
4🙏2🫡1
Forwarded from Mulu Multimedia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Please share this video for others.
ይህን ምስል ለወዳጅዎ በማጋራት አብረውን ይሁኑ።

ለጥያቄና እና ለሀሳብዎ
011 439 27 66
ተባረኩ!
ምን ያህል መሄድ እንችል ይሆን??

ትዝ ይላችኋል ወዳጆቼ የነብዩ ሆሴዕ ህይወት የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ደግሞም ለህዝቡ የጌታን ድምፅ የሚያስተላልፍ  ነው።
በቅድስና የሚገለግለው ሆሴዕ ጋ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል  ጋለሞታዋን ጎሜርን ያገባ ዘንድ ነው !

እጅግ አስደንጋጭ ድምፅ ነው😳 እንኳን በሆሴዕ የትዳር ቀርቶ  የጓደኝነት መስፈርት ውስጥ የማትካተተዋን ጎሜር ጌታ ሂድ አግባት ይለዋል ይህ ብቻ  ደግሞ አይደለም 

ይህንን የመሰለ ሰው በደሏን ሸፍኖ  የወደዳትን መልሳ ከድታ ሌላ ጋ ትሄዳለች ግን ያም ሆኖ ጌታ ሄደህ አምጣት ይለዋል

ሆሴም ሄዶ በውድ ዋጋ የከዳችውን ሌላ ወዳ እሱን ትታ የሄደችውን ሚስቱን ያመጣታል በቃ ሙሉ ታሪኩ ይህ ነው ስትሄድ ሆሴዕ ምሮ ሲያመጣት ያሳየናል።

ጌታም እንዲህ ነው

ከፍጥረታችን በደለኛ ለሆነው ከመጣን በኋላም  ሌላ ወደን አይናችን ለሚንከራተት ለእኛ በውድ ዋጋ ገዛን፣ አቀፈን ፣አፈቀረን ፣ደጋግም በፍቅር ሳበን፣ ትዕግስቱን አበዛልን

ከዛ የዳነውም ጥሪያችን ይሄ ነው!

እንዲህ መዘርጋት ፣ጌታን መግለጥ ያንን ለመለወጥ አስቸጋሪ የሚመስለውን ሰው አብዝቶ መውደድ ፣
ለጓደኝነት መስፈርታችን ውስጥ የማናስበውን ያንን ሰው ማቀፍ  እስኪለወጥ መታገስ ፣አሳልፎ አለመስጠት፣ ገመናውን መደበቅ፣ የጌታን ምህረት ማሳየት ነው ።
ይህ ነው ጥሪያችን
እናስ እኛስ እንደ ሆሴዕ መሄድ እና መዘርጋት እንችል ይሆን??
ጌታ ይርዳን!
2
Forwarded from Kalllll
ለተገፉ ዋና ተሟጋች

ትዝ ይላችኋል ወዳጆቼ የዳዊት ህይወት
በዓመቱ መለወጫ ነገስታት ወደ ሰልፍ በሚወጡበት ጊዜ ዳዊት ኢዮአብን  ከእርሱም ጋር ባሪያዎቹን እስራኤልንም ሁሉ በሰደደ ወቅት ኦርዮን የሚባል ሰውም ወደዚህ ሰልፍ ሄዷል
ያኔ ነው እንግዲህ ወደ ማታ  ጊዜ ዳዊት ከምንጣፋ ተነስቶ  ዘወር ዘወር  ሲል ነው የኦርዮንን ሚስት ገላዋን ስትታጠብ ያያት ዳዊትም ስለማንነቷ ካጣራ በኋላ ወደ እርሱ አስመጣት ከእርሷም ጋ ተኛ ከዛ እሷ ወደ ቤቷ ተመለሰች
ነገር ግን ነገራቸው በዚህ አልተቋረጠም ቤርሳቤህ አረገዘች ወደ ዳዊትም ይህንን መልዕክት ላከችለት   ዳዊት ይህን ጊዜ  ኤልያብን ኦርዮንን ስደድልኝ አለው።
እንዳለውም ኦርዮን መጣ ዳዊትም  ትንሽ ካነጋገረው በኋላ ወደ ቤቱ ሄዶ እረፍት እንዲያደርግ ነገረው
ኦርዮን ግን በንጉስ ደጅ ተኛ ።

ዳዊት ይህንን ሲሰማ ኦርዮንን ለምን ወደ ቤት አልሄድክም ብሎ ጠየቀው ኦርዮን ግን የእግዚአብሔር ታቦት በውጪ ሆኖ እንዴት ብዬ አለ ።
በቀጣይ ጊዜ ዳዊት አጥጥቶ ወደ ሚስቱ እንዲሄድ ሊያደርግ ቢሞክርም ኦርዮን ወይ ፍንክች አለ  ።

ይሄን ጊዜ ነው  እንግዲህ ዳዊት የሞቱን ደብዳቤ  አስይዞ ወደ ኦርዮን  ሰልፍ የላከው ኢዮአብም ንጉሱም እንዳዘዘው ሰልፉ ሲፋፋም ኦርዮን ከፊት አሰልፎ ያለ ደጋፊ አስገደለው ።

ቤርሳቤህም ይህንን በሰማች ጊዜ ለባሏ አለቀሰች ይህ ነገር ሲያልቅ ዳዊት ልኮ አስመጣት

ይህ ነገር ሁሉ ግን በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሆነ
ይሄን ጊዜ  ለዛ በግፍ ለተገደለው ጠበቃ ለሌለው እግዚአብሔር ሊሞገት ተነሳ ነብዪ ናታንንም ወደ ዳዊት ላከው ናታንም ወደ እርሱም መጥቶ አለውበአንድ ከተማ አንዱ ባለጠጋ አንዱም ድሀ የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ።
ባለጠጋውም እጅግ ብዙ በግና ላም ነበረው።
ለድሀው ግን ከገዛት አንዲት ታናሽ በግ በቀር አንዳች አልነበረውም አሳደጋትም ከልጆቹም ጋር በእርሱ ዘንድ አደገች እንጀራውንም ትበላ ከዋንጫውም ትጠጣ በብብቱም ትተኛ ነበር እንደ ልጁም ነበረች።
ወደ ባለጠጋውም እንግዳ በመጣ ጊዜ ከበጉና ከላሙ ወስዶ ለዚያ ወደ እርሱ ለመጣው እንግዳ ያዘጋጅለት ዘንድ ሳሳ የዚያንም የድሀውን ሰው በግ ወስዶ ለዚያ ለመጣው ሰው አዘጋጀ።
ዳዊትም በዚያ ሰው ላይ እጅግ ተቈጥቶ ናታንን፦ ሕያው እግዚአብሔርን! ይህን ያደረገ ሰው የሞት ልጅ ነው።
ይህን አድርጎአልና፥ አላዘነምና ስለ አንዲቱ በግ አራት ይመልስ አለው።
ናታንም ዳዊትን አለው፦ ያ ሰው አንተ ነህ። የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በእስራኤል ላይ ንጉሥ ልትሆን ቀባሁህ፥ ከሳኦልም እጅ አዳንሁህ፤
የጌታህንም ቤት ሰጠሁህ፥ የጌታህንም ሚስቶች በብብትህ ጣልሁልህ፤ የእስራኤልንና የይሁዳን ቤት ሰጠሁህ፤ ይህም አንሶ ቢሆን ኖሮ ከዚህ የበለጠ እጨምርልህ ነበር።
አሁንስ በፊቱ ክፉ ትሠራ ዘንድ የእግዚአብሔርን ነገር ለምን አቃለልህ? ኬጢያዊውን ኦርዮን በሰይፍ መትተሃል፥ ሚስቱንም ለአንተ ሚስት ትሆን ዘንድ ወስደሃል፤ እርሱንም በአሞን ልጆች ሰይፍ ገድለሃል።
ስለዚህም አቃልለኸኛልና፥ የኬጢያዊውንም የኦርዮን ሚስት ለአንተ ሚስት ትሆን ዘንድ ወስደሃልና ለዘላለም ከቤትህ ሰይፍ አይርቅም።
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ ከቤትህ ክፉ ነገር አስነሣብሃለሁ፤ ሚስቶችህንም በዓይንህ ፊት እወስዳለሁ፥ ለዘመድህም እሰጣቸዋለሁ፥ በዚህችም ፀሐይ ዓይን ፊት ከሚስቶችህ ጋር ይተኛል።
አንተ ይህን በስውር አድርገኸዋል፤ እኔ ግን ይህን በእስራኤል ሁሉ ፊትና በፀሐይ ፊት አደርገዋለሁ።


ለሞተው ለዛ ለራሱ መቆም፣ መማገት ለማይችለው ምስኪን ፃዲቁ  እግዚአብሔር ስለ እሱ ተሟገተለት ፤  የተረሳ ማንም ያያ ለማይመስል  ለዛ ንፁህ ሰው ፈራጁ ከሰማይ ሁሉን ተመልክቶ በፅድቅ ፈርዷል!

ዛሬም ወዳጆቼ ለእናንተ የሚቆም በሌለበት ፤ንፁህ በሆናችሁበት ነገር ግን በግፍ በተገፋችሁበት፤ እናንተም በቀበራችሁበት ዋና ጉዳያችሁ  ላይ
ስለ እናንተ የሚቆም ተሟጋች የእናንተ ሁኔታ የሚመለከተው ጠበቃ አላችሁና
ቀና በደንብ ቀና በሉ !
ተባረኩ
5
Forwarded from Kalllll
እርቃን ሸፋኝ ሁኑ

ትዝ ይላችኋል ወዳጆቼ
ዘፍ 9 ላይ ያለው የ ኖህ 👨‍🦳ታሪክ

ከጥፋት ውሀ በኋላ ኖህ ገበሬ ሆነ
ወይንም 🍇 ተከለ
ከወይኑ ጠጅም ጠጣና 🍷ሰከረ በድንኳኑም ውስጥ ራቁቱ ተኛ
በዚህ ጊዜ ነው  ካም የአባቱን ዕራቁትነት የተመለከተው ነገር ግን  ካም የአባቱን ዕራቁትነት ከመሸሸግ እና ካማልበስ ይልቅ ለወንድሞቹ ሮጦ 🏃‍♂‍➡️ሄዶ
የአባቱን ራቁትነት መናገር 🗣የመረጠው
ወንድሞቹ ሴም እና ያፌት👬 ግን እንደካም አልነበሩምና  ካም በነገራቸው ጊዜ ዞረው እንኳን የአባታቸውን ዕራቁትነት ማየት አልፈለጉም
የኋሊት ሄደው የአባታቸውን ዕርቃን አለበሱ

አባታቸውም በነቃ ጊዜ በነ ሴም ተደሰተ መረቃቸውም

እኛስ ዛሬ
የስንት ወንድሞቻችን እርቃን  ይሆን ከመሸፈን ይልቅ ለአደባባይ ማወጅ የቀለለን?😔

እንጃ ብቻ 🤷‍♀

እግዚአብሔር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያካፈለን ህይወት አንዳችን ለሌላችን እርቃችንን፣ ድካማችንን ምንሸፋፈንበት እንጂ የምንሳለቅበት እና አገልጠን የምንሰጥበት  አይደለም
እንከን የሌለበት ንፁሁ ጌታ እግዚአብሔር ራሱ የእነ አዳምን እርቃን ሸፍኖል

እኛም  የደከመውን በፍቅር ልናበረታው፣ የሳተውን ልንመልሰው እና የወደቀውን ልንደግፍ ለዚህ ተጠርተናል እናም   ይህንን ህይወት እንኑር

🎼የአዳምን እርቃን ደርሶ ከሸፈነው
የአባትነት ፍቅሩ አጋልጦ ካልሰጠው
ይህ ህይወት በኛ አለ ከተጠቀምንበት
ከራስ የሚያልፍ ፍቅር የተረፈ ህይወት
ማገገሙ አዬቀርም ምህረቱ አክሞት
ወደ ፀጋው ዙፋን እንግፋው በፀሎት
የሌላውን እርቃን ተባብረን ስንሸፍን
ሞገስ አለ ከላይ የሚለቀቅልን በመያያዛችን🎼
ድምፅ ብቻ እንሁን!

ትዝ ይላችኋል ወዳጆችዬ የመጥምቁ ዮሀንስ ህይወት
ገና ሳይወለድ ከዘመናት በፊት ነብዪ ኢሳያስ የተነበየት ትንቢቱ እንደዚህ  ከምቾት፣  ራስን ከማስደት ፈፅሞ የራቀ  ኑሮ ምድረበዳ ምግቡ አንበጣ ይልቅ የሰማይን ፍቃድ በምድር መጮሂዬ  የሰዎችን ትኩርት ከእግዜሩ መመለስ  ይሄ  ነው ትንቢቱ!


አባቱ ካህን ሽማግሌ እናቱም አሮጊት በጌታን ትዕዛዝ  ያለ ነቀፋ  የሚሄዱ ፃድቃን
ታድያ አንድ ቀን ካህኑ በተራው ወደ ቤተመቅድስ ለማጠን ሲገባ ቅዱሱ የጌታ መልዐክ ምስራች ይዞ ከተፍ  የመጣው መልክት ልጅ ትወልዳላች ታላቅ ሰው ይሆናል ይህማ እልልልታ በእርጅና የተገኛ ተድላ ግና ይሄኛው እንደተለመዱት ተጠባቂ ልጆች ፈፅሞ አይደለም
እርሱ አገልጋይ ነው
የጌታውን ፍቃድ
መንገድ ጠራጊም ነው ለሚመጣው ንጉስ ፤ልብን ይመልሳል ወደ አምላክ ማርኮ፤ ድምፅ ብቻ ሆኖ ዋናውን ይገልጣል

እንደተባለልት አድጎም አገልጋይ ነው ነፍሳት የሚማርክ ወደ እግዚአብሔር ጉያ ሰውን የሚጠራ ወደ ንሰሀ ጥምቀት

ይህን ያዩ አይሁድ ወደ እርሱ ቀረበው
ይህን ምታደርገው በየትኛው ስልጣን 
ኧረ እስኪ ንገረን
እንደው ስንጠረጥር ኤልያስ መሰልከን ወይስ ክርስቶስ ነህ እንደውም ኢሳያስ ነህ ብለው ሲሞግቱት የመጥምቁ ምላሽ ፐ እንዴት አወቃችሁ እኔማ ይገርማችኋል   ብሎ አልሰበትም ራስ ተኮሩ ላይ እኔማ  የሚጮህ ድምፅ ነኝ!
ሚመጣ አካል አለ ከእኔ ለጥቆ
መንገድ ጠራጊው ነኝ ።

እንደው ካላችሁማ አንተ ማነህ  ??
በውሀ አጥማቂ የንጉሱ ባሪያ ፤ጫማው ልሸከም ከቶ ማይገባ፤ እኔ ላንስ ሚስፈልግ እሱ ሊልቅ ሚገባ  የእርሱ አገልጋይ ነኝ!
ይበቃል አትክረሙ እኔ ላይ እሱን ተመልከቱና ባይሆን  ንሰሀ ግቡ ለሚመጣው ንጉስ ልባችሁን ክፈቱ ነበረ ምላሹ!

ለራሱም አልኖረ ምቾት አልፈለገ ለእውነት ሲሞገት በሞቱም ጌታን አከበረ ጌታም መሰከረ ስለ አኗኗሩ
ከሴት ከተወለዱት የሚመስለው የለም!
ላኪውን ያስደሰተ ህይወት

እኛም  ወዳጆቼ ለዚህ ተጠርተናል
ንጉሱ ሊመጣ በደጅ አለሁ ይላል
የጌታን መንገድ ለመጮህ መጥተናል መንገድን ለመጥረግ
ብዙዎችን ወደ ጌታ ለመመለስ
ከእኛ ኋላ የሚመጣው የላቀ እንደሆነ
እኛ ግን ያነስን  እሱን  ለማሳየት ለዚህ ተጠርተናል
እናማ ራስን ለማሳየት ትኩረትን ለመሳብ ይቅር አንጋጋጥ ይልቅ ከኛ የላቀ አለ የሚታይ የሚሰማ የሚያደን
እሱን ብቻ እንግለጥ
እኛ ድምፅ ብቻ እንሁን!

🎼ድምፅ ነኝ እኔ የምጮህልህ
ማለት ያሰብከውን ማስተጋባልህ
ይሄው ነው ስራዬ መላክ ስትልከኝ
ልጅህን ማሳየት አድርጊ እንዳልከኝ🎼


ተባረኩልኝ

በ እህት ቃል
1