Forwarded from AAU - Muslim Students Union
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ ከትላንት እስከ ዛሬ!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጁት ታላቅ የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ተካሄደ።
በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።
መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።
መሰል ፕሮግራሞች በተሻለ አቀራረብ ሌሎች ቦታዎችም በአላህ ፈቃድ የሚቀጥሉ ይሆናል።
@aaumsu
በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።
መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።
መሰል ፕሮግራሞች በተሻለ አቀራረብ ሌሎች ቦታዎችም በአላህ ፈቃድ የሚቀጥሉ ይሆናል።
@aaumsu
🔥2
የ SBE ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት Architecture department መቀላቀል ለምትፈልጉ አዲስ ተማሪዎች ( 2nd year ) ለ መግቢያ ፈተና consultation እያዘጋጀ ይገኛል። እንዲዘጋጅ ትፈልጋላችሁ?
Anonymous Poll
57%
አዎ ይመቸኛል እመጣለሁ።
43%
አይ ይቅር አያስፈልግም
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
የኒቃቢስቷ መልዕክት!
ከአል-በያን ገጾች የተወሰደ...
የሰው ልጅ በሚኖርበት ምህዋር ውስጥ ይህቺ የሚኖርባት አለም: አለም ሆና ማንነቷን ይዛ ትቀጥል ዘንድ ሚናቸውን የተወጡ ብዙ ትናንሽ አለሞች አሉ። እምነት በራሱ አለምን አለም ያደረጋት አንዱ ግብአት ነው። ከእምነት ውስጥ ደግሞ እስልምና የአለሞች ሁሉ ውብ አለም ነው። ሰላት፣ ዱአ፣ ኢባዳ፣ ሰደቃ ፣ መሃባ እና ብዙ ደግሞ ኢስላምን ውብ የሆነ አለም አድርገው ያቆሙት የኢስላም የተዋቀሩ ጌጦች አሉ።
እነዚህ የተሰደሩ የሆኑ ጌጦች በጥንቃቄ እየተጠበቁ ካልቀጠልን የአንዱ ጌጥ መውጣት ስርዓተ-ጥለቱን ያጠፋል። የዲናችንን ውበትም ያደበዝዛል። ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ደግሞ ሌሎች ጌጦቻችንን አውድሞ ከአለሞች ሁሉ ደካማው አለም የሚል ስያሜን ያሰጠናል።
ወዳጄ!! አለም ላይ ያሉ በጣም ውድ ነገሮች በሙሉ ለማንም ክፍት አይደሉም። የተሸፈኑና ከዛም በላይ በጥበቃ ውስጥ ያሉ ናቸው። ኢስላም ሴትን በሂጃባ ወይም በኒቃቧ ሊጠብቃት ኖሯል። ኒቃብ ጨርቅ ቢመስልም ከጨርቅ በላይ ነው። የኢስላም 1 ጌጥ፣ መጠበቂያ፣ መታወቂያ፣ መከበሪያ፣ የሴትነት ክብር መገለጫም ጭምር ነው። አንድን ሰው ኒቃብ ጠል ሆኖ ስታገኘው ጨርቅ ጠል ሆኖ ሳይሆን ጥብቅነትን፣ ስርአትንና ኢስላምን ጠልቶ ነው። እናም ጥላቻውን፣ ግፉንና በደሉን እሰየው ብለህ የተቀበልክ ቀን ሰላትህም፣ ጀማዐህም፣ መስጂድህም፣ ዲንህም ይጎዳ ዘንድ እሰየው ብለህ እንደተቀበልክ ቁጠረው። ስለዚህ ጠላት ኒቃብ አይሆንም ሲል ኢስላማ አይሆንም እንዳለ የተረዳህ ቀን ደግሞ ታጋይ መሆን ትጀምራለህ። ጥልቅ የሆነና እምነትህን የሚገባ የሆነ ቦታው ላይ ሆኖ እስክታየው ድረስ እንቅልፍ የሚነሳህ፣ ያለህበትን ሁኔታ የሚገልጥልህ፣ ያለፈውን አስታውሶ የሚያነቃህ፣ ለዲንህ ደግሞ መስዋእትነትን የሚያስከፍልህ ትግል ማለት ነው።
ወዳጄ!! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለዲናችን መስዋእት የመሆን፣ ጠላት ፊት ቆሞ ለሞትና ለሸሂድነት ዝግጁ የመሆን ችግር የለብንም። ግን ያ ድሮ ወይ ዘንድሮም ቢሆን ለታጣቂ እንጂ ለእኛ አይሆንም። ምክንያቱም እንደምናየው በደም ትግል ውስጥ የመጡ መብቶቻችን በሙሉ ጊዜያዊ መብት እየሆኑ ተቸግረናል። ስለዚህ ልንነቃ ይገባል። ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ የሆነ የትግል መስመር ሊኖረን ይገባል። በየትኛውም የህይወት እርከን ላይ ስናልፍ የሀገራችን እና የኢስላማዊ መብታችንን ሁኔታ ሳንዘነጋ ከስራችንም ከላያችንም ካለው ሙስሊም ወገናችን ጋር በየመሳጂዶቻችን፣ ስራዎቻችን እና ትምህርት ቤቶቻችን የተጠና እቅድ እና እምቅ የሆነ ኃይል ኖሮን መሃላችን ላይ ያለውን ክፍተት በሙሉ እየደፈንን ልንጓዝ ይገባል።
መልእክቴ ነቃቤ ተነክቷል፤ መማር አቅቶኛል። እርዱኝ ሳይሆን በኒቃብ ስያሜ ሊያጠቁ ያሰቡት የጋራ እስልምናችንን ነውና እንንቃ!! ነው።
@aaumsu
ከአል-በያን ገጾች የተወሰደ...
የሰው ልጅ በሚኖርበት ምህዋር ውስጥ ይህቺ የሚኖርባት አለም: አለም ሆና ማንነቷን ይዛ ትቀጥል ዘንድ ሚናቸውን የተወጡ ብዙ ትናንሽ አለሞች አሉ። እምነት በራሱ አለምን አለም ያደረጋት አንዱ ግብአት ነው። ከእምነት ውስጥ ደግሞ እስልምና የአለሞች ሁሉ ውብ አለም ነው። ሰላት፣ ዱአ፣ ኢባዳ፣ ሰደቃ ፣ መሃባ እና ብዙ ደግሞ ኢስላምን ውብ የሆነ አለም አድርገው ያቆሙት የኢስላም የተዋቀሩ ጌጦች አሉ።
እነዚህ የተሰደሩ የሆኑ ጌጦች በጥንቃቄ እየተጠበቁ ካልቀጠልን የአንዱ ጌጥ መውጣት ስርዓተ-ጥለቱን ያጠፋል። የዲናችንን ውበትም ያደበዝዛል። ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ደግሞ ሌሎች ጌጦቻችንን አውድሞ ከአለሞች ሁሉ ደካማው አለም የሚል ስያሜን ያሰጠናል።
ወዳጄ!! አለም ላይ ያሉ በጣም ውድ ነገሮች በሙሉ ለማንም ክፍት አይደሉም። የተሸፈኑና ከዛም በላይ በጥበቃ ውስጥ ያሉ ናቸው። ኢስላም ሴትን በሂጃባ ወይም በኒቃቧ ሊጠብቃት ኖሯል። ኒቃብ ጨርቅ ቢመስልም ከጨርቅ በላይ ነው። የኢስላም 1 ጌጥ፣ መጠበቂያ፣ መታወቂያ፣ መከበሪያ፣ የሴትነት ክብር መገለጫም ጭምር ነው። አንድን ሰው ኒቃብ ጠል ሆኖ ስታገኘው ጨርቅ ጠል ሆኖ ሳይሆን ጥብቅነትን፣ ስርአትንና ኢስላምን ጠልቶ ነው። እናም ጥላቻውን፣ ግፉንና በደሉን እሰየው ብለህ የተቀበልክ ቀን ሰላትህም፣ ጀማዐህም፣ መስጂድህም፣ ዲንህም ይጎዳ ዘንድ እሰየው ብለህ እንደተቀበልክ ቁጠረው። ስለዚህ ጠላት ኒቃብ አይሆንም ሲል ኢስላማ አይሆንም እንዳለ የተረዳህ ቀን ደግሞ ታጋይ መሆን ትጀምራለህ። ጥልቅ የሆነና እምነትህን የሚገባ የሆነ ቦታው ላይ ሆኖ እስክታየው ድረስ እንቅልፍ የሚነሳህ፣ ያለህበትን ሁኔታ የሚገልጥልህ፣ ያለፈውን አስታውሶ የሚያነቃህ፣ ለዲንህ ደግሞ መስዋእትነትን የሚያስከፍልህ ትግል ማለት ነው።
ወዳጄ!! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለዲናችን መስዋእት የመሆን፣ ጠላት ፊት ቆሞ ለሞትና ለሸሂድነት ዝግጁ የመሆን ችግር የለብንም። ግን ያ ድሮ ወይ ዘንድሮም ቢሆን ለታጣቂ እንጂ ለእኛ አይሆንም። ምክንያቱም እንደምናየው በደም ትግል ውስጥ የመጡ መብቶቻችን በሙሉ ጊዜያዊ መብት እየሆኑ ተቸግረናል። ስለዚህ ልንነቃ ይገባል። ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ የሆነ የትግል መስመር ሊኖረን ይገባል። በየትኛውም የህይወት እርከን ላይ ስናልፍ የሀገራችን እና የኢስላማዊ መብታችንን ሁኔታ ሳንዘነጋ ከስራችንም ከላያችንም ካለው ሙስሊም ወገናችን ጋር በየመሳጂዶቻችን፣ ስራዎቻችን እና ትምህርት ቤቶቻችን የተጠና እቅድ እና እምቅ የሆነ ኃይል ኖሮን መሃላችን ላይ ያለውን ክፍተት በሙሉ እየደፈንን ልንጓዝ ይገባል።
መልእክቴ ነቃቤ ተነክቷል፤ መማር አቅቶኛል። እርዱኝ ሳይሆን በኒቃብ ስያሜ ሊያጠቁ ያሰቡት የጋራ እስልምናችንን ነውና እንንቃ!! ነው።
@aaumsu
❤1
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ለ2019 ዓ.ል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመደበኛው መርሃ ግብር ለመማር ቅበላ ላገኛችሁ የአንደኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ
ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች መስከረም 06 እና 07 2019 ዓ.ል በየተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ
1. የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውንና ኮፒ፣
2. አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
3. የማደሪያ ምድብ (Dormitory) ለተሰጣችሁ ብርድልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ ያስታውቃል፡፡
4. ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትኖሩ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል የዩኒቨርሲቲውን የመግቢያ ፈተና በተፈተናችሁበት UGA2019…. ቁጥር በመጠቀም ከታች ባለው ሊንክ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡ https://portal.aau.edu.et/NewStudents/DormitoryPlacement
5. በተጠቀሱት ቀናት (መስከረም 06 እና 07) ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች እንዲሁም በቦሌ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ጣቢያ ዩኒቨርስቲው ወደ አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ወደሚገኙት ካምፓሶቻችን የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
6. ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ ሆኖ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎችና ዶክመንቶች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ል መሆኑን ያሳውቃል፡፡
7. ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ስለ ዩኒቨርስቲዉ ገለፃ የሚደረገዉ ዐርብ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ል ይደረጋል፡፡
8. ዘግይቶ የትምህርት ኮርሶች ምዝገባ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ሲሆን
9. የ2019 ዓ.ል የመጀመሪያዉ ሴሚስተር ትምህርት የሚጀመረዉ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ይሆናል፡፡
10. ስለመቁረጫ ነጥብ ስለምዝገባ ሂደቶች በተመለከተ እና ተጨማሪ መረጃ ከታች ካሉት ሊንኮች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን::
Ø https://portal.aau.edu.et/NewStudents/Welcome
Ø www.aau.edu.et
Ø https://t.me/aauGAT
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር
@aaumsu
ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች መስከረም 06 እና 07 2019 ዓ.ል በየተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ
1. የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውንና ኮፒ፣
2. አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
3. የማደሪያ ምድብ (Dormitory) ለተሰጣችሁ ብርድልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ ያስታውቃል፡፡
4. ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትኖሩ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል የዩኒቨርሲቲውን የመግቢያ ፈተና በተፈተናችሁበት UGA2019…. ቁጥር በመጠቀም ከታች ባለው ሊንክ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡ https://portal.aau.edu.et/NewStudents/DormitoryPlacement
5. በተጠቀሱት ቀናት (መስከረም 06 እና 07) ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች እንዲሁም በቦሌ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ጣቢያ ዩኒቨርስቲው ወደ አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ወደሚገኙት ካምፓሶቻችን የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
6. ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ ሆኖ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎችና ዶክመንቶች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ል መሆኑን ያሳውቃል፡፡
7. ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ስለ ዩኒቨርስቲዉ ገለፃ የሚደረገዉ ዐርብ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ል ይደረጋል፡፡
8. ዘግይቶ የትምህርት ኮርሶች ምዝገባ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ሲሆን
9. የ2019 ዓ.ል የመጀመሪያዉ ሴሚስተር ትምህርት የሚጀመረዉ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ይሆናል፡፡
10. ስለመቁረጫ ነጥብ ስለምዝገባ ሂደቶች በተመለከተ እና ተጨማሪ መረጃ ከታች ካሉት ሊንኮች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን::
Ø https://portal.aau.edu.et/NewStudents/Welcome
Ø www.aau.edu.et
Ø https://t.me/aauGAT
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር
@aaumsu
👍2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ Self sponsorship የተመዘገቡ ተማሪዎች ወደ የትምህርት መስኮች መግቢያ ነጥብን ይፋ አድርጓል።
@aaumsu
@aaumsu