5killo Jem'a official Channel
1.16K subscribers
1.43K photos
285 videos
75 files
673 links
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt
👉Jem'a Tutors
👉Trainings and Da'ewa programs
👉Weekly lunches and halaqas(circles)
👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs)
👉Weekly Q&A sessions

Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Download Telegram
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ ከትላንት እስከ ዛሬ!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጁት ታላቅ የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ተካሄደ።

በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።

መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።

መሰል ፕሮግራሞች በተሻለ አቀራረብ ሌሎች ቦታዎችም በአላህ ፈቃድ የሚቀጥሉ ይሆናል።

@aaumsu
🔥2
የ SBE ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት Architecture department መቀላቀል ለምትፈልጉ አዲስ ተማሪዎች ( 2nd year ) ለ መግቢያ ፈተና consultation እያዘጋጀ ይገኛል። እንዲዘጋጅ ትፈልጋላችሁ?
Anonymous Poll
57%
አዎ ይመቸኛል እመጣለሁ።
43%
አይ ይቅር አያስፈልግም
የኒቃቢስቷ መልዕክት!

ከአል-በያን ገጾች የተወሰደ...

የሰው ልጅ በሚኖርበት ምህዋር ውስጥ ይህቺ የሚኖርባት አለም: አለም ሆና ማንነቷን ይዛ ትቀጥል ዘንድ ሚናቸውን የተወጡ ብዙ ትናንሽ አለሞች አሉ። እምነት በራሱ አለምን አለም ያደረጋት አንዱ ግብአት ነው። ከእምነት ውስጥ ደግሞ እስልምና የአለሞች ሁሉ ውብ አለም ነው። ሰላት፣ ዱአ፣ ኢባዳ፣ ሰደቃ ፣ መሃባ እና ብዙ ደግሞ ኢስላምን ውብ የሆነ አለም አድርገው ያቆሙት የኢስላም የተዋቀሩ ጌጦች አሉ።

እነዚህ የተሰደሩ የሆኑ ጌጦች በጥንቃቄ እየተጠበቁ ካልቀጠልን የአንዱ ጌጥ መውጣት ስርዓተ-ጥለቱን ያጠፋል። የዲናችንን ውበትም ያደበዝዛል። ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ደግሞ ሌሎች ጌጦቻችንን አውድሞ ከአለሞች ሁሉ ደካማው አለም የሚል ስያሜን ያሰጠናል።

ወዳጄ!! አለም ላይ ያሉ በጣም ውድ ነገሮች በሙሉ ለማንም ክፍት አይደሉም። የተሸፈኑና ከዛም በላይ በጥበቃ ውስጥ ያሉ ናቸው። ኢስላም ሴትን በሂጃባ ወይም በኒቃቧ ሊጠብቃት ኖሯል። ኒቃብ ጨርቅ ቢመስልም ከጨርቅ በላይ ነው። የኢስላም 1 ጌጥ፣ መጠበቂያ፣ መታወቂያ፣ መከበሪያ፣ የሴትነት ክብር መገለጫም ጭምር ነው። አንድን ሰው ኒቃብ ጠል ሆኖ ስታገኘው ጨርቅ ጠል ሆኖ ሳይሆን ጥብቅነትን፣ ስርአትንና ኢስላምን ጠልቶ ነው። እናም ጥላቻውን፣ ግፉንና በደሉን እሰየው ብለህ የተቀበልክ ቀን ሰላትህም፣ ጀማዐህም፣ መስጂድህም፣ ዲንህም ይጎዳ ዘንድ እሰየው ብለህ እንደተቀበልክ ቁጠረው። ስለዚህ ጠላት ኒቃብ አይሆንም ሲል ኢስላማ አይሆንም እንዳለ የተረዳህ ቀን ደግሞ ታጋይ መሆን ትጀምራለህ። ጥልቅ የሆነና እምነትህን የሚገባ የሆነ ቦታው ላይ ሆኖ እስክታየው ድረስ እንቅልፍ የሚነሳህ፣ ያለህበትን ሁኔታ የሚገልጥልህ፣ ያለፈውን አስታውሶ የሚያነቃህ፣ ለዲንህ ደግሞ መስዋእትነትን የሚያስከፍልህ ትግል ማለት ነው።

ወዳጄ!! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለዲናችን መስዋእት የመሆን፣ ጠላት ፊት ቆሞ ለሞትና ለሸሂድነት ዝግጁ የመሆን ችግር የለብንም። ግን ያ ድሮ ወይ ዘንድሮም ቢሆን ለታጣቂ እንጂ ለእኛ አይሆንም። ምክንያቱም እንደምናየው በደም ትግል ውስጥ የመጡ መብቶቻችን በሙሉ ጊዜያዊ መብት እየሆኑ ተቸግረናል። ስለዚህ ልንነቃ ይገባል። ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ የሆነ የትግል መስመር ሊኖረን ይገባል። በየትኛውም የህይወት እርከን ላይ ስናልፍ የሀገራችን እና የኢስላማዊ መብታችንን ሁኔታ ሳንዘነጋ ከስራችንም ከላያችንም ካለው ሙስሊም ወገናችን ጋር በየመሳጂዶቻችን፣ ስራዎቻችን እና ትምህርት ቤቶቻችን የተጠና እቅድ እና እምቅ የሆነ ኃይል ኖሮን መሃላችን ላይ ያለውን ክፍተት በሙሉ እየደፈንን ልንጓዝ ይገባል።

መልእክቴ ነቃቤ ተነክቷል፤ መማር አቅቶኛል። እርዱኝ ሳይሆን በኒቃብ ስያሜ ሊያጠቁ ያሰቡት የጋራ እስልምናችንን ነውና እንንቃ!! ነው።

@aaumsu
1
ለ2019 ዓ.ል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመደበኛው መርሃ ግብር  ለመማር ቅበላ ላገኛችሁ የአንደኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ
ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች መስከረም 06 እና 07 2019 ዓ.ል በየተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ
1.     የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውንና ኮፒ፣
2.     አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
3.     የማደሪያ ምድብ (Dormitory) ለተሰጣችሁ ብርድልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ ያስታውቃል፡፡
4.     ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትኖሩ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል የዩኒቨርሲቲውን የመግቢያ ፈተና በተፈተናችሁበት UGA2019…. ቁጥር በመጠቀም ከታች ባለው ሊንክ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡ https://portal.aau.edu.et/NewStudents/DormitoryPlacement
5.     በተጠቀሱት ቀናት (መስከረም 06 እና 07) ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች እንዲሁም በቦሌ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ጣቢያ ዩኒቨርስቲው ወደ አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ወደሚገኙት ካምፓሶቻችን የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
6.     ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ ሆኖ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎችና ዶክመንቶች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ል መሆኑን ያሳውቃል፡፡
7.     ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ስለ ዩኒቨርስቲዉ ገለፃ የሚደረገዉ ዐርብ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ል ይደረጋል፡፡
8.     ዘግይቶ የትምህርት ኮርሶች ምዝገባ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ሲሆን
9.     የ2019 ዓ.ል የመጀመሪያዉ ሴሚስተር ትምህርት የሚጀመረዉ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ል ይሆናል፡፡
10.      ስለመቁረጫ ነጥብ ስለምዝገባ ሂደቶች በተመለከተ እና ተጨማሪ መረጃ ከታች ካሉት ሊንኮች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን::
Ø  https://portal.aau.edu.et/NewStudents/Welcome
Ø www.aau.edu.et
Ø https://t.me/aauGAT
 
   የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር

@aaumsu
👍2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ Self sponsorship የተመዘገቡ ተማሪዎች ወደ የትምህርት መስኮች መግቢያ ነጥብን ይፋ አድርጓል።

@aaumsu
Don't forget to bring A4 size paper and pencil for the consultation.
🔖Thursday Sep 17, morning at 3:00 LT.
ሕያው ምስክር
AAU Muslim Students Union
ሕያው ምስክር - 2

የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል!

አቅራቢ፦ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

አዘጋጅ፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !!

©aaumsu

@fivekjemaa
5killo Jem'a official Channel
AAU Muslim Students Union – ሕያው ምስክር
የምስጋና እና አክብሮት መልዕክት ከቀድሞ የጅማ ዩኒቨርሲቲ (አግሪ ግቢ) አሚር አብዲ ኮርማ የተላለፈ ፦

በቅድሚያ ለሁላችሁም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። በአላህ ፈቃድ በግልም ሆነ በህብረት ለሰራችሁት ትልቅ ስራ፣ በተለይም ደግሞ ሌሎች ሰዎችን በማነቃቃት እና በማበረታታት በኩል ለነበራችሁ ሚና የከበረ ምስጋና እና አክብሮት አለኝ። አላህ በቀጣይም ለሌሎች ችግሮች መፍትሔ እንዲያደርጋችሁ እመኛለሁ።

በ 2016/17 ዓ.ል በነበረው ፈታኝ ወቅት፣ በቀንም ሆነ በሌሊት የ 24 ሰዓት መረጃዎችን እና ጥሪዎችን በመለዋወጥ፣ ምክር እና ድጋፍ በመስጠት አብራችሁን ስትታገሉ ነበር። ምስጋና ከሁሉም በላይ ለሆነው ለአላህ ይሁን፤ ከእሱ በመቀጠል ግን እናንተ መንገድ በማሳየት እና በመደገፍ ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ትልቅ ክብር ይገባችኋል። ውጤት የሚመጣው እንዲህ አይነት አንድነት እና ድምር ጥረት ሲኖር ነው!

በተለይም በወቅቱ በተማሪዎች ግሩፕ ውስጥ የነበሩ አባላት ያሳዩት ትልቅ አንድነት የሚደነቅ ነበር። ያንን ውስብስብ ሁኔታ ለመፍታት ከ Remedial እስከ GC ተማሪዎች ድረስ ወንዶች ብቻ ሳይሆኑ እህቶችም ጭምር እጅ ለእጅ ተያይዘው ትልቅ እገዛ አድርገዋል።

በዚህ አጋጣሚ ለሰራችሁት ሁሉ ጀዛኩሙላሁ አህሰነል ጀዛእ እያልኩኝ፣ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAU MSU)፤ እና ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ለሆኑት ወንድማችን ሙሀመድ አሚን ካሳው በወቅቱ ላሳዩት የስራ አመራር፣ ላደረጉት ያልተቋረጠ ድጋፍ እና አብሮነት የላቀ ምስጋናዬን እና አክብሮቴን ማቅረብ እወዳለሁ።

በመጨረሻም፣ ይህ አዎንታዊ ተሞክሮ እና ህብረት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና አብረን መስራት እንድንችል መልእክቴን አስተላልፋለሁ። ጠንክሩ!

©aaumsu

@fivekjemaa
5killo Jem'a official Channel
AAU Muslim Students Union – ሕያው ምስክር
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ያስተላለፋት መልዕክት:

አሰላም አለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካትሁ
​ቢስሚላህ በመጀመሪያ ጥሪያችንን አክብራችሁ በመገኘት ወንድም ሱደይስ፣ አብዲ ኮርማ፣ አብሮን ሊታደም ያልቻለውን ዶ/ር አብዱሰላምን ጨምሮ፣ እንዲሁም መላው ተሳታፊ ወንድም እና እህቶች በአላህ ስም እጅግ አድርገን እናመሰግናለን።

​በመቀጠል እኛ እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ እና ተማሪዎቻችን ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ያለፈ ( ከኮሮና ጀምሮ እስከ ረመዳን 2017) የትግል ጉዞ ብዙ የወሰድናቸው ትምህርቶች አሉ። ከዛም መካከል አንድ የወንድማችን ንግግር ማስታወስ እወዳለሁ፡

​ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር): "ችግር ሲመጣ ሌላ የሚፈታ አካል እንዲመጣ መፈለግ ሳይሆን "እኔ አለሁለት!" የሚል አቋም ሊኖራችሁ ይገባል።" የሚለው ምክራቸው ሁላችንም ልብ ውስጥ ተቀምጧል ብዬ አስባለሁ።

አጠቃላይ በእንቅስቃሴያቸው ውስጥ የነበረው ጥንካሬ እና ህብረት እጅግ የሚያስደንቅ ነው። በአላህ ፈቃድ ትግል ካለ ድል እንደሚመጣ ህያው መስክር ሆኖ ቀርቦልናል።

​ይህንን ተከትሎ ጀመዓችን ወይም አአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጅማ ላይ ጀግንነት እና ቁርጠኝነት ባሳዩት ወንድም እና እህቶች እንዲሁም በጀማአቸው ስም ስጦታ ማበርከት ይፈልጋል። ስጦታውንም በአዲሱ ዓመት መግቢያ ፕሮግራም ላይ አሚሮች መጥተው ይቀበሉ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።

ሙሐመድ ኢድሪስ
ፕሬዝዳንት

©aaumsu

@fivekjemaa
2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በቦሌ ቡልቡላ ከሚገኘው አንሷር መስጂድ ከተላለፈ የኹጥባ መልዕክት፦

በቅርብ ቀናት ውስጥ የሚገኙት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተለይም ምክንያቶች ሃይማኖታቸውን፣ የሃይማኖታቸውን ድንጋጌ እንዳይስፋፋ የሚገፉ፣ ከትምህርት ማዕከል ራሳቸውንም፣ ቤተሰቦቻቸውንም ሃገራቸውን እንዳይመጥኑ ከሚያደርጉት ጥረት፣ ከሚያደነቃፏቸው አካላት አላህ ሱብሃነ ወተዓላ እንዳያግዛቸው በምንችለው ነገር ሁሉ በሃሳባችን፣ በምክራችን እንዲሁም በዱዓችን እነሱን ማገዝ ይገባናል። ይህ በእኛ ላይ ትንሹ ግዴታ ነው።

@aaumsu
3