Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ችግሩን እንፈታለን ብለው ቃል የገቡ አካላት መጨረሻ ላይ ፈሩ፤ ችግሩን መፍታት አልቻሉም።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
እንደ ኃገር አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች፤ ሽማግሌዎች ከጀመዓው ጋር ተወያዩ፤ ለችግሩም መፍትሄ እንደሚያመጡ ቃል ገቡ። ነገር ግን ይህ ሳይሆን ቀረ።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ዩኒቨርሲቲው ከሁለት ሳምንት በኃላ ፈታለሁ ብሎ ቃል ከገባ በኃላ እንደገና ቃሉን በማጠፍ "እንደዚህ አይነት ነገር አላልኩም" በማለት ቃሉን አጠፈ።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
2017 ዓ.ል ረመዳን ሲደርስ ተማሪው ከኒቃብ ጨምሮ ያሉትን ጥያቄዎች ሰብስቦ ቢያቀርብም ዩኒቨርሲቲው ምንም የተነሳ ጥያቄ እንደሌለ አድርጎ አቀረበ። ይህ ሲሆን ተማሪው ሙሉ ትኩረቱን ወደ ኒቃቡ ጉዳይ ሙሉ ትኩረቱን አዞረ።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
እስከ 2016 ዓ.ል ድረስ ብዙ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። ከሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች ፒትሽን ተሰብስቧል፤ ብዙ ደብዳቤዎች ተጽፈዋል፤ ፌደራል መጅሊስ ድረስ ተኪዷል፤ ከሐገር ሽማግሌዎች እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ሲካሄዱ ነበር።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ጉዳዩ እየከረረ ሲመጣ ጉዳዩን ለማረጋጋት እና ለመሸንገል ሞከሩ። የተለያዩ የዩኒቨርሲቲው፤ የከተማው እና የጸጥታ አካላት በጉዳዩ ዙሪያ ለስብሰባ ቢቀመጡም ተማሪው "እኛ ሽምግልና አንፈልግም፤ ችግሩን የምትፈቱ ከሆነ ፍቱ!" የሚል የጸና አቋም ያዘ።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ጀመዓው ከዚህ በፊት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው የአካባቢው ማህበረሰብ ከጎናችን ነበር።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
በተለይ ሓረማያ፣ አዲስ አበባ እና ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች እና ሌሎች ጀመዓዎችም ከጎናችን ነበሩ።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ችግሩ ከተፈታም በኃላ ወደ መሬት ማውረዱ በራሱ ብዙ ስራ ፈጅቷል። ላይብረሪ፤ ካፌ፤ ካምፓሶች እና ሌሎች ቦታዎች በተግባር ለማውረድ ከወር በላይ ፈጅቷል። ቀጣይ አመት ፍሬሾች እስኪገቡ ድረስ ስራውን አላቆመም ነበር።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ችግር ሲመጣ ሌላ የሚፈታ አካል እንዲመጣ መፈለግ ሳይሆን "እኔ አለሁለት!" የሚል አቋም ሊኖራችሁ ይገባል።
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
@aaumsu
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات
ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል።
የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ ወንድማችን ሱደይስ አብዱረህማን፤ እንዲሁም በኔትዎርክ ምክንያት ሊቀላቀለን ያልቻለውን ወንድም አብዲ ኮርማን ከልብ እናመሰግናለን።
እንዲሁም ፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን!
በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል።
ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር የሚመለስ ይሆናል።
@aaumsu
ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል።
የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ ወንድማችን ሱደይስ አብዱረህማን፤ እንዲሁም በኔትዎርክ ምክንያት ሊቀላቀለን ያልቻለውን ወንድም አብዲ ኮርማን ከልብ እናመሰግናለን።
እንዲሁም ፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን!
በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል።
ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር የሚመለስ ይሆናል።
@aaumsu
❤1
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና ፓናል ውይይት ተዘጋጅቷል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን የተዘጋጀው ይህ ልዩ መድረክ ሊጀምር ደቂቃዎች ብቻ ነው የቀሩት!
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን የተዘጋጀው ይህ ልዩ መድረክ ሊጀምር ደቂቃዎች ብቻ ነው የቀሩት!
@aaumsu
🔥2❤1
አል በያን - ቅ1.pdf
13 MB
🔥 አዲስ ነገር!!! 🔥
በአዲሱ የትምሕርት ዘመን!!
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት!
በመነሻችን ላይ «ስለመንገዱ» መክረን ነበር... መንገዱ የሚጠይቀውን ሁሉ አንዳች ሳንሰስት ለመስጠት ቃል ተጋብተንም ጭምር!... እነሆ አሁን ደግሞ በመንገዳችን ላይ የነበሩትን አጠቃላይ ሂደቶች በምንዳስስበት «አል-በያን!» በተሰኘ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የተዘጋጀ መጽሔት ብቅ ብለናል። ይህ በችሮታው እንጂ በሌላ አልሆነምና፥ ሰዎችን መግለጽ ያስተማረው ጌታ ምሉዕነቱን የሚመጥን ምስጋና የተገባው ይሁን!!!
መጽሔታችን በሚቀጥሉት ጊዜያት በሙስሊም ተማሪዎች ጉዳዮች ላይ በማተኮር የተለያዩ ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ አርዕስቶችን በተከታታይ እየዳሠሠ፥ ለተማሪዎች እንዲሁም ውጪ ላለው ማኅበረሰብ ሰፊ ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ይሆናል።
ይህ ከ«ጥያቄ አለን!» ትውልድ ዘላቂ አሻራዎች ውስጥ አንዱ ነው! መንገዳችን ለታሪክ ይቀመጥ ዘንድ... በጊዜ ሐዲድ ላይ ብሩህ መዳረሻን እናኖር ዘንድ... ለትውልድ ነጻነትን እናወርስ ዘንድ... እስክሪብቷችንን አለመጣላችንን ያረጋገጥንበት ሌላ ክስተት።
መጽሔቱን በማዘጋጀት ሂደት ላይ «እኔም ለትውልድ የማወርሰው ብሩህ ነገ አለ!» ብላችሁ ብዕራችሁን የጨበጣችሁ ውድ ተማሪዎቻችን፥ አላህ (ሱ.ወ) መልካም ሥራችሁን ይባርክላችሁ። ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!!!
አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ የምንሆን ያድርገን።
መልካም ንባብ!
©aaumsu
@fivekjemaa
በአዲሱ የትምሕርት ዘመን!!
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት!
በመነሻችን ላይ «ስለመንገዱ» መክረን ነበር... መንገዱ የሚጠይቀውን ሁሉ አንዳች ሳንሰስት ለመስጠት ቃል ተጋብተንም ጭምር!... እነሆ አሁን ደግሞ በመንገዳችን ላይ የነበሩትን አጠቃላይ ሂደቶች በምንዳስስበት «አል-በያን!» በተሰኘ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የተዘጋጀ መጽሔት ብቅ ብለናል። ይህ በችሮታው እንጂ በሌላ አልሆነምና፥ ሰዎችን መግለጽ ያስተማረው ጌታ ምሉዕነቱን የሚመጥን ምስጋና የተገባው ይሁን!!!
መጽሔታችን በሚቀጥሉት ጊዜያት በሙስሊም ተማሪዎች ጉዳዮች ላይ በማተኮር የተለያዩ ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ አርዕስቶችን በተከታታይ እየዳሠሠ፥ ለተማሪዎች እንዲሁም ውጪ ላለው ማኅበረሰብ ሰፊ ግንዛቤን የሚያስጨብጥ ይሆናል።
ይህ ከ«ጥያቄ አለን!» ትውልድ ዘላቂ አሻራዎች ውስጥ አንዱ ነው! መንገዳችን ለታሪክ ይቀመጥ ዘንድ... በጊዜ ሐዲድ ላይ ብሩህ መዳረሻን እናኖር ዘንድ... ለትውልድ ነጻነትን እናወርስ ዘንድ... እስክሪብቷችንን አለመጣላችንን ያረጋገጥንበት ሌላ ክስተት።
መጽሔቱን በማዘጋጀት ሂደት ላይ «እኔም ለትውልድ የማወርሰው ብሩህ ነገ አለ!» ብላችሁ ብዕራችሁን የጨበጣችሁ ውድ ተማሪዎቻችን፥ አላህ (ሱ.ወ) መልካም ሥራችሁን ይባርክላችሁ። ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!!!
አላህ ለመልካም ለውጥ ሰበብ የምንሆን ያድርገን።
መልካም ንባብ!
©aaumsu
@fivekjemaa
🔥3👏1
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በGovernment Sponsorship መግባት ለሚፈልጉ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብን ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት፦
📌 ለNatural Science፡ 76.17
📌 ለSocial Science: 58.75
ውጤት የሚሰላው 50% Entrance exam፤ 50% UAT በማድረግ ከ100% ይሆናል።
@aaumsu
📌 ለNatural Science፡ 76.17
📌 ለSocial Science: 58.75
ውጤት የሚሰላው 50% Entrance exam፤ 50% UAT በማድረግ ከ100% ይሆናል።
@aaumsu
👍2
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
ከበኒ ኢስራኢል ምድር ....ጧሉትና ጃሉት
ክፍል 1
ጊዜው ከሙሳ ዐለይሂ ሰላም በኋላ ነው፤ የኢስራኢል ልጆች በሙሳ መንገድ ፀንተው በተወራትም ህግጋት ሲመሩ ነበር። ዘመናት በራቀ ቁጥር ግን ቀልቦቻቸው ደረቁ፤ በዲናቸውም አዳዲስ ነገሮችን አስገቡ፤ ከፊሎቻቸውም ጣኦታትን ማምለክ ጀመሩ። ከክፋታቸው ይመለሱ፣ በመልካም ይታዘዙ፣ ከክፉም ነገር ይታቀቡ ዘንድ እንዲሁም በመካከላቸው በተውራት ህግጋት እንዲፈርዱ አሏህ መልእክተኞችን አከታትሎ መላክን ቀጠለ።
ቀደም ባለ ጊዜ የኢስራኢል ልጆችን የሚዋጋ ሁሉ ይሸነፍ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ ከአላህ ጋር በቀጥታ ከተነጋገሩት ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ጀምሮ ከትውልድ ወደ ወደ ትውልድ ሲወራረሱት የነበረ ተውራትና ታቦትን ይዘው ስለነበር ነው። (ይህ ሲባል ታቦቱ /ሳጥኑ ውስጥ የሙሳ እና ሀሩን ቅርስ የነበረ ሲሆን ጦርነት ሲሄዱ ተሸክመውት ሄደው ከአላህ በሆነ ተአምር በርሱ በረካ ነስርን ያረጋግጥላቸው ነበር)
የኢስራኢል ልጆችም እነዚያን ክፉ ስራዎች መፈጸማቸውን በቀጠሉ ጊዜ አላህ ጠላቶቻቸውን በእነርሱ ላይ ሾመባቸው። ብዙዎች ጦር ሜዳ ላይ አለቁ፣ ልጆቻቸው እና ሴቶቻቸው ተማረኩ፣ጠላቶቻቸው በሀገራቸው ሰፊ ክፍሎችን ተቆጣጠሩ፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በቃ የአንድ ህዝብ ልቅናውም ሆነ ውድቀቱ ሚጀምረው ለጌታውን ትእዛዝ ከሚሰጠው ቦታ ነው።አሁን ላለንበት የበታችነትና በካፊሮች እጅ ስር መጨፍደድ አንዱ ምክንያት ከአሏህ መራቅ ነው።ሙስሊሙ ውጥንቅጡ ወጥቷል፤ ከቁርአን ብርሀን፣ ከነብዩም፣ ከሰሀቦቻቸው፣ ከድንቅ ተተኪዎችም በኋላ መርህ እንደሌለው ተራ ሰው ዘቀጥን ዱንያም ዋጠችን...ውጤቱንም እንደምናየው ነው– በየቦታው ችግራችን በዛ ከብዛታችንም ሀይል አጣን ተዳከምን።
የኢስራኢል ልጆች ታቦቱንና ተውራትን በአንድ የጠላት ንጉስ እስኪያስነጥቁ ድረስ በጥመት መቀጠላቸውን አላቆሙም ነበር። ከዚህም በኋላ ከመካከላቸው አንድን ነብይ አሏህ ላከ። ወደ አላህ እርሱን ብቻ እንዲያመልኩ እንዲጠራ አዘዘው። ነብያቸውም የኢስራኢል ልጆችን ወደ አላህ ጠራቸው።እነርሱም በመካከላቸው ንግስና አብቅቶ ነበርና ጠላቶቻቸውን በእርሱ መሪነት በአሏህ መንገድ ለመዋጋት አንድን ንጉስ እንዲሾምላቸው ጠየቁ።
<<أَلَمْ تَرَ إِلَى الْمَلَإِ مِن بَنِي إِسْرَائِيلَ مِن بَعْدِ مُوسَىٰ إِذْ قَالُوا لِنَبِيٍّ لَّهُمُ ابْعَثْ لَنَا مَلِكًا نُّقَاتِلْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ>>
"ከኢስራኢል ልጆች ከሙሳ በኋላ ወደ ነበሩት ጭፍሮች ለነቢያቸው ፡- «ለእኛ ንጉሥን አስነሳልን በአላህ መንገድ እንዋጋለን፤» ባሉ ጊዜ አላየህምን? (አላወቅህምን?)"
ነብያቸውም እንዲህ አላቸው:-
<<قَالَ هَلْ عَسَيْتُمْ إِن كُتِبَ عَلَيْكُمُ الْقِتَالُ أَلَّا تُقَاتِلُوا ۖ>>
"ከአሏህ ዘንድ በግዳጅነት ቢፃፍባችሁ ላለመዋጋት ትሻላችሁን??"
<< قَالُوا وَمَا لَنَا أَلَّا نُقَاتِلَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَقَدْ أُخْرِجْنَا مِن دِيَارِنَا وَأَبْنَائِنَا>>
"ከሀገሮቻችን እና ከልጆቻችን የተባረርን ስንሆን በአላህ መንገድ የማንዋጋ ለእኛ ምን አለን?" በማለትም መልሱ
መሪ እንዲሰጣቸው ጠየቁ.....ነገር ግን ፈተናውን ለመቀበል ዝግጁ ነበሩ ይሆን!?
ይቀጥላል....
ክፍል 1
ጊዜው ከሙሳ ዐለይሂ ሰላም በኋላ ነው፤ የኢስራኢል ልጆች በሙሳ መንገድ ፀንተው በተወራትም ህግጋት ሲመሩ ነበር። ዘመናት በራቀ ቁጥር ግን ቀልቦቻቸው ደረቁ፤ በዲናቸውም አዳዲስ ነገሮችን አስገቡ፤ ከፊሎቻቸውም ጣኦታትን ማምለክ ጀመሩ። ከክፋታቸው ይመለሱ፣ በመልካም ይታዘዙ፣ ከክፉም ነገር ይታቀቡ ዘንድ እንዲሁም በመካከላቸው በተውራት ህግጋት እንዲፈርዱ አሏህ መልእክተኞችን አከታትሎ መላክን ቀጠለ።
ቀደም ባለ ጊዜ የኢስራኢል ልጆችን የሚዋጋ ሁሉ ይሸነፍ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ ከአላህ ጋር በቀጥታ ከተነጋገሩት ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ጀምሮ ከትውልድ ወደ ወደ ትውልድ ሲወራረሱት የነበረ ተውራትና ታቦትን ይዘው ስለነበር ነው። (ይህ ሲባል ታቦቱ /ሳጥኑ ውስጥ የሙሳ እና ሀሩን ቅርስ የነበረ ሲሆን ጦርነት ሲሄዱ ተሸክመውት ሄደው ከአላህ በሆነ ተአምር በርሱ በረካ ነስርን ያረጋግጥላቸው ነበር)
የኢስራኢል ልጆችም እነዚያን ክፉ ስራዎች መፈጸማቸውን በቀጠሉ ጊዜ አላህ ጠላቶቻቸውን በእነርሱ ላይ ሾመባቸው። ብዙዎች ጦር ሜዳ ላይ አለቁ፣ ልጆቻቸው እና ሴቶቻቸው ተማረኩ፣ጠላቶቻቸው በሀገራቸው ሰፊ ክፍሎችን ተቆጣጠሩ፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በቃ የአንድ ህዝብ ልቅናውም ሆነ ውድቀቱ ሚጀምረው ለጌታውን ትእዛዝ ከሚሰጠው ቦታ ነው።አሁን ላለንበት የበታችነትና በካፊሮች እጅ ስር መጨፍደድ አንዱ ምክንያት ከአሏህ መራቅ ነው።ሙስሊሙ ውጥንቅጡ ወጥቷል፤ ከቁርአን ብርሀን፣ ከነብዩም፣ ከሰሀቦቻቸው፣ ከድንቅ ተተኪዎችም በኋላ መርህ እንደሌለው ተራ ሰው ዘቀጥን ዱንያም ዋጠችን...ውጤቱንም እንደምናየው ነው– በየቦታው ችግራችን በዛ ከብዛታችንም ሀይል አጣን ተዳከምን።
የኢስራኢል ልጆች ታቦቱንና ተውራትን በአንድ የጠላት ንጉስ እስኪያስነጥቁ ድረስ በጥመት መቀጠላቸውን አላቆሙም ነበር። ከዚህም በኋላ ከመካከላቸው አንድን ነብይ አሏህ ላከ። ወደ አላህ እርሱን ብቻ እንዲያመልኩ እንዲጠራ አዘዘው። ነብያቸውም የኢስራኢል ልጆችን ወደ አላህ ጠራቸው።እነርሱም በመካከላቸው ንግስና አብቅቶ ነበርና ጠላቶቻቸውን በእርሱ መሪነት በአሏህ መንገድ ለመዋጋት አንድን ንጉስ እንዲሾምላቸው ጠየቁ።
<<أَلَمْ تَرَ إِلَى الْمَلَإِ مِن بَنِي إِسْرَائِيلَ مِن بَعْدِ مُوسَىٰ إِذْ قَالُوا لِنَبِيٍّ لَّهُمُ ابْعَثْ لَنَا مَلِكًا نُّقَاتِلْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ>>
"ከኢስራኢል ልጆች ከሙሳ በኋላ ወደ ነበሩት ጭፍሮች ለነቢያቸው ፡- «ለእኛ ንጉሥን አስነሳልን በአላህ መንገድ እንዋጋለን፤» ባሉ ጊዜ አላየህምን? (አላወቅህምን?)"
ነብያቸውም እንዲህ አላቸው:-
<<قَالَ هَلْ عَسَيْتُمْ إِن كُتِبَ عَلَيْكُمُ الْقِتَالُ أَلَّا تُقَاتِلُوا ۖ>>
"ከአሏህ ዘንድ በግዳጅነት ቢፃፍባችሁ ላለመዋጋት ትሻላችሁን??"
<< قَالُوا وَمَا لَنَا أَلَّا نُقَاتِلَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَقَدْ أُخْرِجْنَا مِن دِيَارِنَا وَأَبْنَائِنَا>>
"ከሀገሮቻችን እና ከልጆቻችን የተባረርን ስንሆን በአላህ መንገድ የማንዋጋ ለእኛ ምን አለን?" በማለትም መልሱ
መሪ እንዲሰጣቸው ጠየቁ.....ነገር ግን ፈተናውን ለመቀበል ዝግጁ ነበሩ ይሆን!?
ይቀጥላል....
❤1🔥1
Forwarded from AAU - Muslim Students Union
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ ከትላንት እስከ ዛሬ!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጁት ታላቅ የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ተካሄደ።
በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።
መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።
መሰል ፕሮግራሞች በተሻለ አቀራረብ ሌሎች ቦታዎችም በአላህ ፈቃድ የሚቀጥሉ ይሆናል።
@aaumsu
በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።
መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።
መሰል ፕሮግራሞች በተሻለ አቀራረብ ሌሎች ቦታዎችም በአላህ ፈቃድ የሚቀጥሉ ይሆናል።
@aaumsu
🔥2