5killo Jem'a official Channel
1.16K subscribers
1.43K photos
285 videos
75 files
673 links
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt
👉Jem'a Tutors
👉Trainings and Da'ewa programs
👉Weekly lunches and halaqas(circles)
👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs)
👉Weekly Q&A sessions

Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Download Telegram
💫ልዩ የዳእዋ ፕሮግራም ለእህቶች💫

ሂጃብ እና የዘመኑ ፈተና

አላህ ሱ.ወ ሴትን ልጅ ካላቀበት እና ካከበረበት ነገሮች ውስጥ ሂጃብ አንዱ እና ትልቁ ነገር ነው።የተስተካከለ አለባበስ የአንዲት ሙስሊም ሴት ጥብቅነት መገለጫም ጭምር እንደሆነ ተቀምጦልናል። ታድያ አለባበሳችን ምን መምሰል አለበት...ምንድነው ሂጃብ መስፈርቶቹ እንዲሁም ምንድነው የተፈለገበት .....እሚለውን እና ሌሎችንም ለማውራት ቀጠሯችንን የፊታችን ቅዳሜ በታላቁ ሁዘይፋ መስጂድ አድርገናል።

ምን እሱ ብቻ ..

ከሂጃብ ጋር እየመጡ ያሉ ትምህርት ላይ እንቅፋት የሆኑ ክልከላዎች እና ዘመን አመጣሽ ውጣውረዶች ምንድናቸው ? በምን መልክ ማለፍ እንችላለን ? ለሚመጣውስ ትውልድ ምን ማበርከት እንችላለን ? የሚለውንም የምናነሳ ይሆናል።

ቦታ፡- ሁዘይፋ መስጂድ (የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
ቀን ፡- የፊታችን ቅዳሜ
ሰአት ፡-3፡00-6፡00
ተጋባዥ ፡- ሁሏም እህት ሁሏም እናት ሁሏም ተማሪ (አዲስ ግቢ የምትገቡ ተማሪዎች ብትመጡ በደንብ ትጠቀማላቹ)

@aaumsu
👌5
ጥቂት ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል!

ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ

በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!

ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !

@aaumsu
Forwarded from 5K Muslim Developers Circle(MDC)
💎የውመል ጁሙአ(ተወዳጁ ቀን)💎

💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }

      ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ 


🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-

" የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት
ያወርድለታል........

🌸"أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً"

ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣
ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣
ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣

ዛሬ ጁሙአ ነው በረሱል ﷺ ላይ ሰለዋት አውርደናል
اللهم صلِّ وسلم على نبينا محمد ﷺ
ብዙ ያልተነኩና የልተዳሰሱ አሻራዎች ያሉበት መንገድ!

ሕያው ምስክር ~ 2 ~ ጅማ ዩኒቨርስቲ የነፃነት ትግል!!

🗓 ዛሬ ከ ምሽቱ 3:00 እንገናኝ!


@aaumsu
ሕያው ምስክር - 2 - 3:00 ላይ ይጀመራል!

ከ2 ሰዓት ያነሰ ጊዜ ቀረን ማለት ነው። ስለ አባጅፋሯ ጅማ፤ ስለአባጅፋር ልጆች የመብት ጥያቄ ሂደት ከሕያው ምስክሮች ጋር ልዩ ቆይታ ይኖራል። መልዕክቱን ለሁሉም አድርሱ። ሰከንድ ሳያልፍ በሰዓቱ እንገኝ።

የጥያቄ አለን ትውልድ የሚዘነጋው ትግል የለም!

@aaumsu
1 ሰዓት ብቻ ቀረው!

ዝግጁ?

@aaumsu
"የጀመዓ ትልቁ ኃላፊነት የተማሪዎችn መብት እና ደህንነት ማስጠበቅ ነው።"

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ችግሩን እንፈታለን ብለው ቃል የገቡ አካላት መጨረሻ ላይ ፈሩ፤ ችግሩን መፍታት አልቻሉም።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
እንደ ኃገር አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች፤ ሽማግሌዎች ከጀመዓው ጋር ተወያዩ፤ ለችግሩም መፍትሄ እንደሚያመጡ ቃል ገቡ። ነገር ግን ይህ ሳይሆን ቀረ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ዩኒቨርሲቲው ከሁለት ሳምንት በኃላ ፈታለሁ ብሎ ቃል ከገባ በኃላ እንደገና ቃሉን በማጠፍ "እንደዚህ አይነት ነገር አላልኩም" በማለት ቃሉን አጠፈ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
2017 ዓ.ል ረመዳን ሲደርስ ተማሪው ከኒቃብ ጨምሮ ያሉትን ጥያቄዎች ሰብስቦ ቢያቀርብም ዩኒቨርሲቲው ምንም የተነሳ ጥያቄ እንደሌለ አድርጎ አቀረበ። ይህ ሲሆን ተማሪው ሙሉ ትኩረቱን ወደ ኒቃቡ ጉዳይ ሙሉ ትኩረቱን አዞረ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
እስከ 2016 ዓ.ል ድረስ ብዙ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። ከሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች ፒትሽን ተሰብስቧል፤ ብዙ ደብዳቤዎች ተጽፈዋል፤ ፌደራል መጅሊስ ድረስ ተኪዷል፤ ከሐገር ሽማግሌዎች እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ሲካሄዱ ነበር።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ጉዳዩ እየከረረ ሲመጣ ጉዳዩን ለማረጋጋት እና ለመሸንገል ሞከሩ። የተለያዩ የዩኒቨርሲቲው፤ የከተማው እና የጸጥታ አካላት በጉዳዩ ዙሪያ ለስብሰባ ቢቀመጡም ተማሪው "እኛ ሽምግልና አንፈልግም፤ ችግሩን የምትፈቱ ከሆነ ፍቱ!" የሚል የጸና አቋም ያዘ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ጀመዓው ከዚህ በፊት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው የአካባቢው ማህበረሰብ ከጎናችን ነበር።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
በተለይ ሓረማያ፣ አዲስ አበባ እና ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች እና ሌሎች ጀመዓዎችም ከጎናችን ነበሩ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ችግሩ ከተፈታም በኃላ ወደ መሬት ማውረዱ በራሱ ብዙ ስራ ፈጅቷል። ላይብረሪ፤ ካፌ፤ ካምፓሶች እና ሌሎች ቦታዎች በተግባር ለማውረድ ከወር በላይ ፈጅቷል። ቀጣይ አመት ፍሬሾች እስኪገቡ ድረስ ስራውን አላቆመም ነበር።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
አላህም ወቅቱን መርጦት ይመስላል በረመዳን መሆኑ

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
ችግር ሲመጣ ሌላ የሚፈታ አካል እንዲመጣ መፈለግ ሳይሆን "እኔ አለሁለት!" የሚል አቋም ሊኖራችሁ ይገባል።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات

ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል።

የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ ወንድማችን ሱደይስ አብዱረህማን፤ እንዲሁም በኔትዎርክ ምክንያት ሊቀላቀለን ያልቻለውን ወንድም አብዲ ኮርማን ከልብ እናመሰግናለን።

እንዲሁም ፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን!

በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል።

ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር የሚመለስ ይሆናል።

@aaumsu
1
በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና ፓናል ውይይት ተዘጋጅቷል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን  የተዘጋጀው ይህ ልዩ መድረክ ሊጀምር ደቂቃዎች ብቻ ነው የቀሩት!

@aaumsu
🔥21