Fidel Tutorial (ፊደል የጥናት አገልግሎት)
2.08K subscribers
857 photos
23 videos
192 files
185 links
* Professional Tutorial service
* Book online or via phone
* Kg to university
* Flashcards
* online Tutorials
Contact
+251979795154
+251979795468

Youtube: https://www.youtube.com/@FidelTutorial


To become a tutor
join https://t.me/fideltutores
Download Telegram
ለቀጣይ ዙር የ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች;
።።።፡።።።።:::::
ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ እየተቃረበ መሆኑን አውቃችሁ በተዘጋጃችሁት ልክ ተረጋግታችሁ ለመስራት ጥረት እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በተለይ በግጭት አካባቢ የነበራችሁ ተማሪዎች በብዙ ችግር ውስጥ ሁናችሁ ስትዘጋጁ እንደቆያችሁ ይታወቃል። ችግራችሁን በመገንዘብም ቀጣዩ ዙር ፈተና የተዘጋጀላችሁ መሆኑን በመገንዘብ ዕድላችሁን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት ምክራችንን እንለግሳለን።

በአንደኛው ዙር ፈተና (በተለይ በማህበራዊ ሳይንስ ፈተና) ወቅት የተከሰቱት ችግሮች  እናንተንም እንዳይገጥሟችሁ ማስታወስ ተገቢ ነው ብዬ ስላሰብሁ የሚከተሉትን ላጋራችሁ ወደድሁ:

1. በ2013 ተፈትነው ነገር ግን በድጋሚ  በመደበኛው ኘሮግራም ለመፈተን እድል የነበራቸው የተወሰኑ ተማሪዎች(ሁሉንም ለማለት አይደለም) ሲያጠኑ ስላልከረሙ እና የተሻለ ውጤት ማምጣት የማይችሉ መሆናቸውን በመገመት የፈተና ስርዓቱን ለማወክ ባደረጉት ሙከራ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው እና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ተስፋ የነበራቸው ተማሪዎቻችን ከፈተና ተስተጓጉለውብናል። ይህ ድድርጊት እጅግ በጣም ስሜታችንን ጎድቶት አልፏል። በመሆኑም በቀጣይ እንዳይደገም ትምህርት መውሰድ ተገቢ ነው።

2. አንዳንድ ተማሪዎች ፈታኞችን ያልተገባ ንግግር በመናገር እና በማበሳጨት እንዲሁም የክፍል ፈተና ስርዓቱ እንዲረበሽ በማድረግ ፈታኞች ፈተናውን በችግር እንዲመዘግቡት የማድረግ ያልተገባ ግፊትም ተስተውሏል።

ይህ ድርጊት ምንጩ አስከአሁን ግልፅ ባይሆንም በተለይ ፈታኞች በሳል ሁነው ችግሩን በጥበብ ማለፍ ካልቻሉ ተፅዕኖው ቀላል እንደማይሆን ስጋት መፍጠሩ አልቀረም።

በጊዜው ሁሉም ቦታ ለመድረስ ባይቻልም መድረስ በቻልንባቸው የፈተና ጣቢያዎች ፈታኞችን ለማረጋጋት እና ድርጊቱ ውስን ቁጥር ያላቸው የተለዬ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበው በትዕግስት የፈተና ስርዓቱን እንዲመሩት ለማግባባት ተሞክሯል። ሌሎች ያልደረስንባቸው ጣቢያዎች ሁኔታ ምንይመስል እንደነበር ግን እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ፈታኞች ይህን ታሪካዊ ሀላፊነታቸውን በትዕግስት እና በጥበብ ተወጥተውት እና ለብዙሀኑ ተማሪዎች ሲባል የአንዳንድ ተማሪዎችን ያልተገባ ስነምግባር በትዕግስት አልፈውት እንደሚሆን እንጠብቃለን።

3. በተለይ ደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ላይ የተፈጠረው ያለመረጋጋት ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲፈተኑ የሚያስችል ሁኔታ ነበር ብሎ ለማለት ያስቸግራል።  የነበረው ሁኔታ ፈተና አቋርጠው በሄዱት ላይ  ብቻም ሳይሆን በፈተና ሂደቱ ውስጥ በነበሩት ተማሪዎች ላይም ተፅዕኖው ከባድ እንደሚሆን ይገመታል።

  በዚህም ሁከት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው ውጤታማ ተማሪዎቻችን ባላሰቡት መንገድ ተስተጓጉለውብናል።

በአጠቃላይ የመጀመሪያው ዙር ፈተና እንደሀገር የመጀመሪያ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከት/ቢሮውም በኩል የነበሩ ከቅድመዝግጅት መጓደለም ጋር የተያያዙት መለስተኛ ችግሮች (በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ወቅት ማስተካከያ የተደረገባቸው ችግሮች)ተጨምረውበት በርካታ ተማሪዎቻችን ከፈተና ስርዓቱ የተስተጓጎሉበት ሁኔታ መፈጠሩ  የትምህርት ማህበረሰቡን እጅግ በጣም ያሳዘነ ክስተት ሆኗል።

የነበሩ የቅድመዝግጅት መጓደሎችን እና አጠቃላይ ሂደቱን በሚመለከት ለሚመለከተው አካል በጊዜው የግምገማ ሪፓርት ስላቀረብን እዚህ ላይ መዘርዘሩ አያስፈልግም።

በአጠቃላይ ከግምገማ ሪፓርታችንም ሆነ ከሌሎች ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት ውሳኔ ሰጭው አካል የሚሰጠው ውሳኔ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀጣዩ ዙር ፈተና የባለፋት ችግሮች በድጋሜ እናንተንም እንዳያጋጥሟችሁ ተገቢውን የጥንቃቄ ቅድመዝግጅት እንድታደርጉ ከወዲሁ እያሳሰብሁ መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!

የአብክመ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ
Congratulations to Argentina 🇦🇷🇦🇷🇦🇷
#QatarWorldCup
Study
-SAT
-TOEFL
-IELTS
with our professionals

BOOK
NOw !

Fidel Tutorial
0979795154/0979795468.
THE G.O.A.T
why is messi called the GOAT?

The word Goat is an abbreviation word, Greatest of all time, an internet slang initialism used to compliment athletes, musicians, Writers, or other celebrities for achieving great things in life.
Why is messi called the Goat? Leonel messi has won every Grand cups in the world competitions including the world cup holding so many records even from a young age.

10 La liga cups
4 champions league cups
1 World cup

-Top scorer in La Liga history with 474 Goals.
-Most international goals by a South American male 98.
-Most goals by a player for a single club 672.

Indeed a Goat!.......

@fideltutorial
አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት የአባልነት ምዝገባ መጀመሩ ይታወቃል። 

የኦንላይን ምዝገባ ለማድረግ ይህን ቅደም ተከተል ይከተሉ፦

1. በ www.abrehot.org.et/register/ በመግባት የምዝገባ ፎርሙን ይሙሉ።

2. ፎርሙን እንደጨረሱ ክፍያ ገፅ ይፈጽሙ፤ ዓመታዊ የአባልነት ክፍያ በቴሌብር ወይም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል መክፈል ይችላሉ።

3. ቅድመ ተከተሉን እንደጨረሱ አባልነትዎ ይረጋገጣል።

በ15 ቀን ውስጥ ዲጂታል የአባልነት መታወቂያ በኢሜይል ይደርስዎታል።
For all Junior Programmers

We have put a link step by step guides and paths to learn different tools and technologies.The intent of this guide is to give you an idea about the development landscape and to help guide your learning.

Flutter Developer
https://roadmap.sh/flutter

Android Developer
https://roadmap.sh/android

GraphQL Developer
https://roadmap.sh/graphql

Node.js Developer
https://roadmap.sh/nodejs

@fideltutorial
0979795154/0979795468.
ተከፋይ Intern መሆን ይፈልጋሉ?

#ደረጃ_ዶት_ኮም መረጃ የሚሰበስቡ ተከፋይ ተለማማጅ ሰራተኞች/Interns እየፈለገ መሆኑን አሳውቋል።

አመልካቾች ከሚከተሉት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በአንዱ ተመራቂ ተማሪዎች የሆኑናና በዚያው አካባቢ የሚኖሩ መሆን አለባቸው።

➤ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ

➤ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ

➤ ቀብሪ ዳር ዩኒቨርሲቲ

➤ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ

➤ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ

➤ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ

➤ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

➤ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው

ታህሳስ 17/2015 ዓ.ም

ለማመልከት ተከታዩን ሊንክ ይጠቀሙ፦

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScCC2eEOQ8c8BkxkBGPXy2pKUpgofa1gR1EdzlHtovDDSc9qg/viewform
Fidel Educational Consultancy

-Fidel guides students to be innovative and opens up an opportunity to explore and try different Educational sectors.

-Ethical Children that are well mannered, decent, considerate and respectful.

-Confident children that communicate well and promote a healthy companionship with others.

call us.
0979795154
0979795468.
የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች "ራስ ገዝነት"

ራስ ገዝ ሆነው የሚደራጁ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በዓለም አቀፍ ውድድር አዲስ ፕሬዝዳንቶችን እንደሚመርጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ይህ አሰራር በአገር ውስጥ ውድድር ተወስኖ የቆየውን የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ቅጥር ሂደት በማስፋት የውጭ ዜጎችም ጭምር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሪነት እንዲወዳደሩ ዕድል የሚሰጥ ነው ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ 10 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ ዕቅድ ይዟል። በዚህ እቅድ ከተካተቱት ውስጥ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ጅማ፣ ሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ እና መቐለ ዩኒቨርሲቲዎች ይገኙበታል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተያዘው በጀት ዓመት የራስ ገዝ አስተዳደርን ተግባራዊ በማድረግ የመጀመሪያው የመንግስት ዩኒቨርሲቲ እንደሚሆን ይጠበቃል።

መንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶቻቸውን ከሀገር ውስጥ ካሉ ምሁራን አወዳድረው ሲቀጥሩ ቢቆዩም፤ በሁለት ዩኒቨርሲቲዎች (በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በመቐለ ዩኒቨርሲቲዎች) ለተወሰኑ ዓመታት የውጪ ዜጎችም በፕሬዚዳንትነት ተመርጠው አገልግለዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች “ራስ ገዝ” መሆናቸው የአስተዳደር፣ የአካዳሚ፣ የፋይናንስ እና የሰው ኃብት አስተዳደራቸው ላይ ነጻነት እንዲኖራቸው እንደሚያደርግ በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር እና መሰረተ ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር ተናግረዋል።

በተለያዩ አገራት በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ እና በአመራርነት የሚሰሩ ዳያስፖራዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎችን ቢመሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ይችላሉ ሲሉም አክለዋል። 

ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ ዕጩዎች ሊኖራቸው የሚጠበቀው የትምህርት ደረጃ “ዶክትሬት ዲግሪ ወይም ተመጣጣኝ የሚወክል ትምህርት እና ልምድ” መሆን እንዳለበት በመመሪያው ሰፍሯል። ሆኖም የማስተርስ ዲግሪ ያላቸው ግለሰቦች “በልዩ ሁኔታ” ሊመረጡ እንደሚችሉ በመመሪያው ተቀምጧል። 

እስካሁን በነበረው አሰራር በትምህርት ሚኒስቴር ሹመት የሚያገኙ ፕሬዝዳንቶች የሥራ ዘመናቸው ስድስት ዓመት ሲሆን ለአንድ ተጨማሪ ጊዜ ሊመረጡ ይችላሉ። ምክትል ፕሬዝዳንቶች በአንጻሩ ሹመታቸው የሚጸድቀው በዩኒቨርስቲዎች ቦርድ ሲሆን አራት ዓመት የስራ ዘመን ይኖራቸዋል።

ራስ ገዝ እንደሚሆኑ የሚጠበቁ ዩኒቨርስቲዎች፤ ፕሬዝዳንቶቻቸውን የሚመርጡበትን መስፈርት፣ የአገልግሎት ዘመን እና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚወስኑ ዝርዝር ድንጋጌዎች እንደሚኖራቸው ዋና ስራ አስፈጻሚው አስረድተዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ ሲሆኑ ያለ ትምህርት ሚኒስቴር ጣልቃ ገብነት ፕሬዝዳንቶቻቸውን በቦርድ ማጽደቅ እንደሚችሉ ተገልጿል። #ኢትዮጵያኢንሳይደር
Aastu.Final.Exam.Collection.pdf
4.9 MB
📚Aastu University ‼️
📚All Final Exams
📚  ፈተና  በቀጣይ  ፉይናል ያለባቹ ሞክሩት

❗️የ ዘንድሮ ነው(2014) ፎቶ በእንደዚህ መልኩ አንስታችሁ ላኩልን። ለናንተም ውጤታችሁን ፎቶ ማንሳት በኋላ ውጤታችሁ ችግር ቢያጋጥመው መፍትሔ ይሆናል።
 
በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተመረጡ የጤና መስክ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር አመልክታችሁ የተቀመጡ መስፈርቶችን ያሟላችሁ አመልካቾች ታህሳስ 17 18 2015 ዓ.ም በአካል በመቅረብ ምዝገባ እንድታከናውን ዩኒቨርሲቲው ጥሪ አድርጓል።

@tikvahuniversty
📚AAU University ‼️
📚 Entrepreneurship Final Exams 2014 last weak
📚  ፈተና  በቀጣይ  ፉይናል ያለባቹ ሞክሩት

❗️የ ዘንድሮ ነው።
     
ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ🙏👇👇

@Fideltutorial
We are hiring!
Hawassa Branch


Fidel is Inviting University students, fresh graduates and Experienced tutors to assist children on their studies.

Please fill the form below :

Https://forms.gle/KsUieAxdTmejhAUs9

Hawassa 05, near to Lewi resort Round about.
0979795154/0979795468.
#Update #AddisAbaba

የ2ኛውን ዙር የሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ለመፈተን #በአዲስ_አበባ ከተማ አስተዳደር የተመዘገቡ ተማሪዎች በክፍለ ከተማቸው በኩል በ16 / 4 /2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሳይንስና ቴክኖሎጂ 5 ኪሎ ካምፓስ እንዲገቡ የከተማው ትምህርት ቢሮ ዛሬ አሳስቧል።

የ2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ ታህሳስ 21 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ መግለፁ ይታወሳል።


🔔ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇
@Fideltutorial