#MoE
• መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር በተመሳሳይ ጊዜ ይሰጣል።
• 200, 000 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ እንደሚሰጥ የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ገልጸዋል።
መሪ ስራ አስፈጻሚው ኤባ ሚጀና ( ዶ/ር ) በጉዳዩ ዙሪያ በተዘጋጀ አውደጥናት ላይ እንደገለጹት መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር ለሁሉም ቅድመ መደበኛ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ ይሰጣል።
የመጀመሪያው ፈተና በሰኔ ወር ከተሰጠ በኋላ ቀጣዩ የመውጫ ፈተና ከ6 ወራት በኋላ እንደሚሰጥም ዶ/ር ኤባ አስረድተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰይድ መሀመድ በበኩላቸው ፈተናውን ለ200, 000 የመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፈተናው ለሁሉም ተማሪዎች በኦንላይን እንደሚሰጥ የጠቀሱት አቶ ሰይድ " ይህ የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የተሻለ አማራጭ በመሆኑ ነው " ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱም ሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው በተመሳሳይ ጊዜ በኦንላይን እንደሚሰጥ አውቀው ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቶ ሰይድ አሳስበዋል።
በመውጫ ፈተና ብቃትና የፈተና ኮርሶች ልየታና የተገቢነት ማረጋገጥ ዙሪያ በተዘጋጀው አውደጥናት ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ጉዳዩ የሚመለከታቸው መምህራን ተሳታፊ መሆናቸውም ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
(ትምህርት ሚኒስቴር)
• መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር በተመሳሳይ ጊዜ ይሰጣል።
• 200, 000 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ እንደሚሰጥ የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ገልጸዋል።
መሪ ስራ አስፈጻሚው ኤባ ሚጀና ( ዶ/ር ) በጉዳዩ ዙሪያ በተዘጋጀ አውደጥናት ላይ እንደገለጹት መውጫ ፈተና በመጪው ሰኔ ወር ለሁሉም ቅድመ መደበኛ ተማሪዎች በአንድ ጊዜ ይሰጣል።
የመጀመሪያው ፈተና በሰኔ ወር ከተሰጠ በኋላ ቀጣዩ የመውጫ ፈተና ከ6 ወራት በኋላ እንደሚሰጥም ዶ/ር ኤባ አስረድተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰይድ መሀመድ በበኩላቸው ፈተናውን ለ200, 000 የመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፈተናው ለሁሉም ተማሪዎች በኦንላይን እንደሚሰጥ የጠቀሱት አቶ ሰይድ " ይህ የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የተሻለ አማራጭ በመሆኑ ነው " ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱም ሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው በተመሳሳይ ጊዜ በኦንላይን እንደሚሰጥ አውቀው ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቶ ሰይድ አሳስበዋል።
በመውጫ ፈተና ብቃትና የፈተና ኮርሶች ልየታና የተገቢነት ማረጋገጥ ዙሪያ በተዘጋጀው አውደጥናት ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ጉዳዩ የሚመለከታቸው መምህራን ተሳታፊ መሆናቸውም ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
(ትምህርት ሚኒስቴር)
Fidel December Edition Magazine.pdf
2.6 MB
እነሆ በውስጧ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን የያዘችው ወርሃዊዋ የፊደል መፅሄት ቀኗን ጠብቃ ወደ እናንተ መጥታለች።
በውስጧ
-ትምህርት
-ቤተሰብ
-ልዩ ፍላጎት
-ሳይንስና ቴክኖሎጂ
-ፊደል ሜዲካል
-ፋሽን
-ምን አዲስ በኢትዮጵያ?
-ፊደል እንግዳ
-ፊደል በዚህ ወር
-ፊደል የመፅሀፍት ጥቆማ
-ፊደል የፊልም ጥቆማ
እነዚህንና ብዙ ጉዳዮችን አካታለች።
ተጋበዙልን!
በውስጧ
-ትምህርት
-ቤተሰብ
-ልዩ ፍላጎት
-ሳይንስና ቴክኖሎጂ
-ፊደል ሜዲካል
-ፋሽን
-ምን አዲስ በኢትዮጵያ?
-ፊደል እንግዳ
-ፊደል በዚህ ወር
-ፊደል የመፅሀፍት ጥቆማ
-ፊደል የፊልም ጥቆማ
እነዚህንና ብዙ ጉዳዮችን አካታለች።
ተጋበዙልን!
የመውጫ ፈተናን በተመለከት ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና የውይይት መድረክ ተካሄደ።
**
በዚህ አመት ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናን በተመለከት ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሁም የስነ-ልቡና ግንባታ ስልጠና እና የውይይት መድረክ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስነ-ልቡና ምሁራን የሆኑ መምህራን እና የኮሌጅ ዲኖች በተገኙበት ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።
በመድረኩ መክፈቻ ስለመውጫ ፈተናው ሰፋ ያለ ማብራሪያ በማቅረብ ስልጠና የሰጡት የስነ-ልቦና ሙህር የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ የመውጫ ፈተና የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማንሳት ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ለተማሪዎች አስረድተዋል። ከነዚህ ጥቅሞች ውስጥ የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣ ተወዳዳሪ የሆነ ዜጋ ማፍራት እና እራስን ለመፈተሽ እንደሚያግዝ እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ የሆኑ ጥቅሞችን በመጥቀስ አስረድተዋል። አክለውም ተማሪዎች ፍራታቸውን አስወግደው ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመቀጠልም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የህግ ትምህርት ክፍል ዲኖች እስከ አሁን ለጤና እና ለህግ ተማሪዎች ይሰጥ በነበረው የመውጫ ፈተና ያላቸውን ልምድ ለተማሪዎች አካፍለዋል። ዲኖቹ አያይዘውም በሁለቱም ኮሌጆች እየተሰጠ ባለው የመውጫ ፈተና ተሞክሮው እንደሚያሳየው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተከታታይ ዓመታት ባስመዘገቡት ክፍተኛ ውጤት ዩኒቨሲቲው በደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ ሲካተት የቆየ መሆኑን አስታውሰው የነሱን አርአያ በመከተል ይህንን ልምድ ማስቀጠል እንደሚገባ እንዲሁም ከዘንድሮ ተመራቂዎችም ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቁ ገልፀዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ዲን መምህር ቃኘው ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ትምህርት ቤት የመውጫ ፈተና ሲጀመር የነበራቸውን ትዝታ ለተማሪዎቹ ያስታወሱ ሲሆን ተማሪዎች ስጋታቸውን አስወግደው ዝግጅቱ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ በማሳሰብ አሁንም ለመዘጋጀት በቂ ጊዜ እንዳላቸው አስታውሰዋል፡፡
በመድረኩ የተገኝተው ተማሪዎቹን ያወያዩት የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብቴ ዱላ እና የአካዳሚክ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ካሳሁን አቤ ስለመውጫ ፈተና ከተማሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ሀብቴ በበኩላቸው ተማሪዎች ለፈተናው ያላቸውን አሉታዊ አመለካከት በመቀየር ሰፋ ያለውን አውንታዊ አንድምታ መገንዘብ እንደሚያሻ ተናግረዋል፡፡ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለፈተናው ዝግጅት በቻለው አቅም ሁሉ እንደሚያግዛቸው እና ከጎናቸው በመሆን እንደሚረዳቸው ቃል ገብተዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ተማሪዎች ከራሳቸው የሚጠበቀውን ብቻ ካደረጉ የሚያስጨንቅ አንዳች ነገር እንደሌለ እንዲሁም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በመውጫ ፈተናዎች ላይ የነበረውን ውጤታማነት የዚህ አመት ተመራቂ ተማሪዎችም እንደሚያስቀጥሉ ባለሙሉ ተስፋ እንደሆኑ ገልፀዋል።
“ፈተናው ግቢ ላይ ከምትፈተኑት የተለየ ፈተና አይደለም” ሲሉ የገለፁት ረዳት ፕሮፈሰር ካሳሁን አቤ ፈተናው ጠቅላላ እውቀትን ያማከለ መሆኑን ገልፀው “አንድ ምግብ አብሳይ የሚያበስለውን ምግብ ለማዘጋጀት ምን እንደሚያስፈልገው በመጠየቅ ያንን ምግብ ለማብሰል ያለውን እውቀት እንደመገምገም ነው” ማለት በምሳሌ አስረድተዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ሚካኤል ያቦነሽ ፈተናው ከመሰጠቱ በፊት ማንኛውም ተማሪ በዩኒቨርሲቲው እና በህብረቱ የሚዘጋጁ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል፣ እርስ በእርስ በመተጋገዝ እንዲሁም በተናጠል በማንበብ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘገባው የወ/ዩ/ተ/ህብረት የመረጃ እና የህዝብ ግንኙነት ነው።
**
በዚህ አመት ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተናን በተመለከት ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሁም የስነ-ልቡና ግንባታ ስልጠና እና የውይይት መድረክ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስነ-ልቡና ምሁራን የሆኑ መምህራን እና የኮሌጅ ዲኖች በተገኙበት ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።
በመድረኩ መክፈቻ ስለመውጫ ፈተናው ሰፋ ያለ ማብራሪያ በማቅረብ ስልጠና የሰጡት የስነ-ልቦና ሙህር የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ የመውጫ ፈተና የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማንሳት ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ለተማሪዎች አስረድተዋል። ከነዚህ ጥቅሞች ውስጥ የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣ ተወዳዳሪ የሆነ ዜጋ ማፍራት እና እራስን ለመፈተሽ እንደሚያግዝ እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ የሆኑ ጥቅሞችን በመጥቀስ አስረድተዋል። አክለውም ተማሪዎች ፍራታቸውን አስወግደው ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመቀጠልም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የህግ ትምህርት ክፍል ዲኖች እስከ አሁን ለጤና እና ለህግ ተማሪዎች ይሰጥ በነበረው የመውጫ ፈተና ያላቸውን ልምድ ለተማሪዎች አካፍለዋል። ዲኖቹ አያይዘውም በሁለቱም ኮሌጆች እየተሰጠ ባለው የመውጫ ፈተና ተሞክሮው እንደሚያሳየው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተከታታይ ዓመታት ባስመዘገቡት ክፍተኛ ውጤት ዩኒቨሲቲው በደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ ሲካተት የቆየ መሆኑን አስታውሰው የነሱን አርአያ በመከተል ይህንን ልምድ ማስቀጠል እንደሚገባ እንዲሁም ከዘንድሮ ተመራቂዎችም ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቁ ገልፀዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ዲን መምህር ቃኘው ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ትምህርት ቤት የመውጫ ፈተና ሲጀመር የነበራቸውን ትዝታ ለተማሪዎቹ ያስታወሱ ሲሆን ተማሪዎች ስጋታቸውን አስወግደው ዝግጅቱ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ በማሳሰብ አሁንም ለመዘጋጀት በቂ ጊዜ እንዳላቸው አስታውሰዋል፡፡
በመድረኩ የተገኝተው ተማሪዎቹን ያወያዩት የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብቴ ዱላ እና የአካዳሚክ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ካሳሁን አቤ ስለመውጫ ፈተና ከተማሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ሀብቴ በበኩላቸው ተማሪዎች ለፈተናው ያላቸውን አሉታዊ አመለካከት በመቀየር ሰፋ ያለውን አውንታዊ አንድምታ መገንዘብ እንደሚያሻ ተናግረዋል፡፡ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለፈተናው ዝግጅት በቻለው አቅም ሁሉ እንደሚያግዛቸው እና ከጎናቸው በመሆን እንደሚረዳቸው ቃል ገብተዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ተማሪዎች ከራሳቸው የሚጠበቀውን ብቻ ካደረጉ የሚያስጨንቅ አንዳች ነገር እንደሌለ እንዲሁም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በመውጫ ፈተናዎች ላይ የነበረውን ውጤታማነት የዚህ አመት ተመራቂ ተማሪዎችም እንደሚያስቀጥሉ ባለሙሉ ተስፋ እንደሆኑ ገልፀዋል።
“ፈተናው ግቢ ላይ ከምትፈተኑት የተለየ ፈተና አይደለም” ሲሉ የገለፁት ረዳት ፕሮፈሰር ካሳሁን አቤ ፈተናው ጠቅላላ እውቀትን ያማከለ መሆኑን ገልፀው “አንድ ምግብ አብሳይ የሚያበስለውን ምግብ ለማዘጋጀት ምን እንደሚያስፈልገው በመጠየቅ ያንን ምግብ ለማብሰል ያለውን እውቀት እንደመገምገም ነው” ማለት በምሳሌ አስረድተዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ሚካኤል ያቦነሽ ፈተናው ከመሰጠቱ በፊት ማንኛውም ተማሪ በዩኒቨርሲቲው እና በህብረቱ የሚዘጋጁ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል፣ እርስ በእርስ በመተጋገዝ እንዲሁም በተናጠል በማንበብ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘገባው የወ/ዩ/ተ/ህብረት የመረጃ እና የህዝብ ግንኙነት ነው።
Fidel tutorial
we can help you with math!
from KG to University
Contact Us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
we can help you with math!
from KG to University
Contact Us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
FIDEL TUTORIAL CENTER
Math,
physics, Science,
and English Tutoring.
Maximize your learning with
our personalized sessions!
Call us
0979795154
0979795468
@fideltutorial
Math,
physics, Science,
and English Tutoring.
Maximize your learning with
our personalized sessions!
Call us
0979795154
0979795468
@fideltutorial
ነፃ የእንግሊዘኛ ቋንቋ መማሪያ ገፅ
የትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ነፃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ ያለምንም ክፍያ አቅርቦሎታል።
ልጆችዎ ይማራሉ - እርስዎም የእንግሊዝኛ ቋንቋዎን ያሻሽሉበታል።
የትም ሆነው ይማሩ የቋንቋ ክህሎትዎን ያዳብሩ!
አገልግሎቱን ለማግኘት ከታች የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ
👇👇👇
https://learn-english.moe.gov.et
የትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ነፃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ ያለምንም ክፍያ አቅርቦሎታል።
ልጆችዎ ይማራሉ - እርስዎም የእንግሊዝኛ ቋንቋዎን ያሻሽሉበታል።
የትም ሆነው ይማሩ የቋንቋ ክህሎትዎን ያዳብሩ!
አገልግሎቱን ለማግኘት ከታች የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ
👇👇👇
https://learn-english.moe.gov.et
ዕድሜያቸው ከ 17-21 ለሆኑ ተማሪዎች የተዘጋጀ ልዩ ሃካቶን (Hackaton)
በዚህ ውድድር መሳተፍ የሚፈልግ ተማሪ ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ መመዝገብ ይችላል።
ምዝገባው በነፃ ሲሆን ከህዳር 30 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ይቆያል።
ከእንድ እስከ ሦሥት ለሚወጡ ተማሪዎች ልዩ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
ለመመዝገብ 👉 hackathon.kibur.net
ለበለጠ መረጃ፦ 0113698558
በዚህ ውድድር መሳተፍ የሚፈልግ ተማሪ ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ መመዝገብ ይችላል።
ምዝገባው በነፃ ሲሆን ከህዳር 30 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ይቆያል።
ከእንድ እስከ ሦሥት ለሚወጡ ተማሪዎች ልዩ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
ለመመዝገብ 👉 hackathon.kibur.net
ለበለጠ መረጃ፦ 0113698558
Do you need help with your Degree?
We provide the best Assistants for your
-BA
-BSC
-MBA
-MSC Degree.
contact us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
We provide the best Assistants for your
-BA
-BSC
-MBA
-MSC Degree.
contact us
0979795154/0979795468.
@fideltutorial
ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የሁሉም ክልል ተማሪዎች በሁለተኛው ዙር ለፈተናው እንዲቀመጡ የተለየ ሲሆኑ እነርሱም፦
• የመጀመሪያ ዙር ፈተናን በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣
• በህግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው በነበረው መፈተኛ ሁኔታ ለመፈተን ያልቻሉ፣
• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣
• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘና ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣
• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣
• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣
• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ገፃችንን https://t.me/fideltutorial JOIN እና ሼር ያድርጉ!
የሁሉም ክልል ተማሪዎች በሁለተኛው ዙር ለፈተናው እንዲቀመጡ የተለየ ሲሆኑ እነርሱም፦
• የመጀመሪያ ዙር ፈተናን በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣
• በህግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው በነበረው መፈተኛ ሁኔታ ለመፈተን ያልቻሉ፣
• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣
• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘና ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣
• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣
• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣
• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ገፃችንን https://t.me/fideltutorial JOIN እና ሼር ያድርጉ!
በትግራይ ክልል የመማር ማስተማር ሂደትን በቀጣዮቹ አምስት ወራት ለማስጀመር እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በትግራይ ክልል ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል።
በክልሉ የትምህርት ሥራን ለማስጀመር የሚያስችሉ ተግባራትን ለማከናወን እቅዶች መያዛቸውንና ዝግጅት መጀመሩን በሚኒስቴሩ የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎቶች ዴስክ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ለኢፕድ ተናግረዋል።
በክልሉ የሰው ሀብት የማደራጀት፣ የፈረሱ ትምህርት ቤቶችን የመጠገንና ግብዓት የማሟላት እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እንደሚደረግ ኃላፊው አመልክተዋል።
በትግራይ ክልል የመማር ማስተማር ሥራው ሲጀመር ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ እንደሚሆነ የጠቆሙት ኃላፊው፤ በትግራይ ክልል የተማሪዎች ምገባ ለማስጀመር አጋር አካላት እና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
በትግራይ ክልል ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል።
በክልሉ የትምህርት ሥራን ለማስጀመር የሚያስችሉ ተግባራትን ለማከናወን እቅዶች መያዛቸውንና ዝግጅት መጀመሩን በሚኒስቴሩ የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎቶች ዴስክ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ለኢፕድ ተናግረዋል።
በክልሉ የሰው ሀብት የማደራጀት፣ የፈረሱ ትምህርት ቤቶችን የመጠገንና ግብዓት የማሟላት እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እንደሚደረግ ኃላፊው አመልክተዋል።
በትግራይ ክልል የመማር ማስተማር ሥራው ሲጀመር ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ እንደሚሆነ የጠቆሙት ኃላፊው፤ በትግራይ ክልል የተማሪዎች ምገባ ለማስጀመር አጋር አካላት እና ሌሎችም ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ እና የ3ኛ ዓመት ተማሪዎች አድማ በመምታት ትምህርት ማቋረጣቸውን ሰምተናል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዓመት ተማሪዎች ያለ አግባብ የምንመረቅበት ጊዜ በተለይም የ2013 ባች ተማሪዎች እስከ ሁለት ሴሚስተር ያህል ማለትም ከመመረቂያ ጊዜያችን አንድ ዓመት ዘግይተን እንድንመረቅ ዩንቨርሲቲው ወስኗል በሚል ምክንያት ተቃውሟቸውን ክፍል ባለመግባት እየገለፁ እንደሆነ ከተማሪዎቹ ያግኘነው መረጃ ያመለክታል።
በጉዳዩ ላይ ግልፅ ውይይት ለማድረግ ኮሚቴ አዋቅረን ጥረት ብናደርግም ዩንቨርሲቲው የኛን ጥያቄ ከመስማት ይልቅ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አካላትን በማሰማራት ማስፈራሪያ እያደረሰብን ነው ሲሉ ከሰዋል።
ቤተሰቦቻችን ከኛ ብዙ ነገር ይጠብቃሉ የሚሉት ተማሪዎቹ በሌሎች ዩንቨርሲቲዎች ከሚገኙ ጓደኞቻችን እኩል መመረቅ ባለብን ካላንደር መሰረት ተመርቀን ተወዳዳሪ እንሁን ማለታችን እንደ ስህተት ተወስዶ አግባብነት ያለው ጥያቄያችን በጉልበት ሊታፈን አይገባም ብለዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዓመት ተማሪዎች ያለ አግባብ የምንመረቅበት ጊዜ በተለይም የ2013 ባች ተማሪዎች እስከ ሁለት ሴሚስተር ያህል ማለትም ከመመረቂያ ጊዜያችን አንድ ዓመት ዘግይተን እንድንመረቅ ዩንቨርሲቲው ወስኗል በሚል ምክንያት ተቃውሟቸውን ክፍል ባለመግባት እየገለፁ እንደሆነ ከተማሪዎቹ ያግኘነው መረጃ ያመለክታል።
በጉዳዩ ላይ ግልፅ ውይይት ለማድረግ ኮሚቴ አዋቅረን ጥረት ብናደርግም ዩንቨርሲቲው የኛን ጥያቄ ከመስማት ይልቅ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አካላትን በማሰማራት ማስፈራሪያ እያደረሰብን ነው ሲሉ ከሰዋል።
ቤተሰቦቻችን ከኛ ብዙ ነገር ይጠብቃሉ የሚሉት ተማሪዎቹ በሌሎች ዩንቨርሲቲዎች ከሚገኙ ጓደኞቻችን እኩል መመረቅ ባለብን ካላንደር መሰረት ተመርቀን ተወዳዳሪ እንሁን ማለታችን እንደ ስህተት ተወስዶ አግባብነት ያለው ጥያቄያችን በጉልበት ሊታፈን አይገባም ብለዋል።
ለቀጣይ ዙር የ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች;
።።።፡።።።።:::::
ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ እየተቃረበ መሆኑን አውቃችሁ በተዘጋጃችሁት ልክ ተረጋግታችሁ ለመስራት ጥረት እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በተለይ በግጭት አካባቢ የነበራችሁ ተማሪዎች በብዙ ችግር ውስጥ ሁናችሁ ስትዘጋጁ እንደቆያችሁ ይታወቃል። ችግራችሁን በመገንዘብም ቀጣዩ ዙር ፈተና የተዘጋጀላችሁ መሆኑን በመገንዘብ ዕድላችሁን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት ምክራችንን እንለግሳለን።
በአንደኛው ዙር ፈተና (በተለይ በማህበራዊ ሳይንስ ፈተና) ወቅት የተከሰቱት ችግሮች እናንተንም እንዳይገጥሟችሁ ማስታወስ ተገቢ ነው ብዬ ስላሰብሁ የሚከተሉትን ላጋራችሁ ወደድሁ:
1. በ2013 ተፈትነው ነገር ግን በድጋሚ በመደበኛው ኘሮግራም ለመፈተን እድል የነበራቸው የተወሰኑ ተማሪዎች(ሁሉንም ለማለት አይደለም) ሲያጠኑ ስላልከረሙ እና የተሻለ ውጤት ማምጣት የማይችሉ መሆናቸውን በመገመት የፈተና ስርዓቱን ለማወክ ባደረጉት ሙከራ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው እና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ተስፋ የነበራቸው ተማሪዎቻችን ከፈተና ተስተጓጉለውብናል። ይህ ድድርጊት እጅግ በጣም ስሜታችንን ጎድቶት አልፏል። በመሆኑም በቀጣይ እንዳይደገም ትምህርት መውሰድ ተገቢ ነው።
2. አንዳንድ ተማሪዎች ፈታኞችን ያልተገባ ንግግር በመናገር እና በማበሳጨት እንዲሁም የክፍል ፈተና ስርዓቱ እንዲረበሽ በማድረግ ፈታኞች ፈተናውን በችግር እንዲመዘግቡት የማድረግ ያልተገባ ግፊትም ተስተውሏል።
ይህ ድርጊት ምንጩ አስከአሁን ግልፅ ባይሆንም በተለይ ፈታኞች በሳል ሁነው ችግሩን በጥበብ ማለፍ ካልቻሉ ተፅዕኖው ቀላል እንደማይሆን ስጋት መፍጠሩ አልቀረም።
በጊዜው ሁሉም ቦታ ለመድረስ ባይቻልም መድረስ በቻልንባቸው የፈተና ጣቢያዎች ፈታኞችን ለማረጋጋት እና ድርጊቱ ውስን ቁጥር ያላቸው የተለዬ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበው በትዕግስት የፈተና ስርዓቱን እንዲመሩት ለማግባባት ተሞክሯል። ሌሎች ያልደረስንባቸው ጣቢያዎች ሁኔታ ምንይመስል እንደነበር ግን እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ፈታኞች ይህን ታሪካዊ ሀላፊነታቸውን በትዕግስት እና በጥበብ ተወጥተውት እና ለብዙሀኑ ተማሪዎች ሲባል የአንዳንድ ተማሪዎችን ያልተገባ ስነምግባር በትዕግስት አልፈውት እንደሚሆን እንጠብቃለን።
3. በተለይ ደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ላይ የተፈጠረው ያለመረጋጋት ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲፈተኑ የሚያስችል ሁኔታ ነበር ብሎ ለማለት ያስቸግራል። የነበረው ሁኔታ ፈተና አቋርጠው በሄዱት ላይ ብቻም ሳይሆን በፈተና ሂደቱ ውስጥ በነበሩት ተማሪዎች ላይም ተፅዕኖው ከባድ እንደሚሆን ይገመታል።
በዚህም ሁከት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው ውጤታማ ተማሪዎቻችን ባላሰቡት መንገድ ተስተጓጉለውብናል።
በአጠቃላይ የመጀመሪያው ዙር ፈተና እንደሀገር የመጀመሪያ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከት/ቢሮውም በኩል የነበሩ ከቅድመዝግጅት መጓደለም ጋር የተያያዙት መለስተኛ ችግሮች (በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ወቅት ማስተካከያ የተደረገባቸው ችግሮች)ተጨምረውበት በርካታ ተማሪዎቻችን ከፈተና ስርዓቱ የተስተጓጎሉበት ሁኔታ መፈጠሩ የትምህርት ማህበረሰቡን እጅግ በጣም ያሳዘነ ክስተት ሆኗል።
የነበሩ የቅድመዝግጅት መጓደሎችን እና አጠቃላይ ሂደቱን በሚመለከት ለሚመለከተው አካል በጊዜው የግምገማ ሪፓርት ስላቀረብን እዚህ ላይ መዘርዘሩ አያስፈልግም።
በአጠቃላይ ከግምገማ ሪፓርታችንም ሆነ ከሌሎች ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት ውሳኔ ሰጭው አካል የሚሰጠው ውሳኔ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀጣዩ ዙር ፈተና የባለፋት ችግሮች በድጋሜ እናንተንም እንዳያጋጥሟችሁ ተገቢውን የጥንቃቄ ቅድመዝግጅት እንድታደርጉ ከወዲሁ እያሳሰብሁ መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
የአብክመ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ
።።።፡።።።።:::::
ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ እየተቃረበ መሆኑን አውቃችሁ በተዘጋጃችሁት ልክ ተረጋግታችሁ ለመስራት ጥረት እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በተለይ በግጭት አካባቢ የነበራችሁ ተማሪዎች በብዙ ችግር ውስጥ ሁናችሁ ስትዘጋጁ እንደቆያችሁ ይታወቃል። ችግራችሁን በመገንዘብም ቀጣዩ ዙር ፈተና የተዘጋጀላችሁ መሆኑን በመገንዘብ ዕድላችሁን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት ምክራችንን እንለግሳለን።
በአንደኛው ዙር ፈተና (በተለይ በማህበራዊ ሳይንስ ፈተና) ወቅት የተከሰቱት ችግሮች እናንተንም እንዳይገጥሟችሁ ማስታወስ ተገቢ ነው ብዬ ስላሰብሁ የሚከተሉትን ላጋራችሁ ወደድሁ:
1. በ2013 ተፈትነው ነገር ግን በድጋሚ በመደበኛው ኘሮግራም ለመፈተን እድል የነበራቸው የተወሰኑ ተማሪዎች(ሁሉንም ለማለት አይደለም) ሲያጠኑ ስላልከረሙ እና የተሻለ ውጤት ማምጣት የማይችሉ መሆናቸውን በመገመት የፈተና ስርዓቱን ለማወክ ባደረጉት ሙከራ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው እና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ተስፋ የነበራቸው ተማሪዎቻችን ከፈተና ተስተጓጉለውብናል። ይህ ድድርጊት እጅግ በጣም ስሜታችንን ጎድቶት አልፏል። በመሆኑም በቀጣይ እንዳይደገም ትምህርት መውሰድ ተገቢ ነው።
2. አንዳንድ ተማሪዎች ፈታኞችን ያልተገባ ንግግር በመናገር እና በማበሳጨት እንዲሁም የክፍል ፈተና ስርዓቱ እንዲረበሽ በማድረግ ፈታኞች ፈተናውን በችግር እንዲመዘግቡት የማድረግ ያልተገባ ግፊትም ተስተውሏል።
ይህ ድርጊት ምንጩ አስከአሁን ግልፅ ባይሆንም በተለይ ፈታኞች በሳል ሁነው ችግሩን በጥበብ ማለፍ ካልቻሉ ተፅዕኖው ቀላል እንደማይሆን ስጋት መፍጠሩ አልቀረም።
በጊዜው ሁሉም ቦታ ለመድረስ ባይቻልም መድረስ በቻልንባቸው የፈተና ጣቢያዎች ፈታኞችን ለማረጋጋት እና ድርጊቱ ውስን ቁጥር ያላቸው የተለዬ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበው በትዕግስት የፈተና ስርዓቱን እንዲመሩት ለማግባባት ተሞክሯል። ሌሎች ያልደረስንባቸው ጣቢያዎች ሁኔታ ምንይመስል እንደነበር ግን እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ፈታኞች ይህን ታሪካዊ ሀላፊነታቸውን በትዕግስት እና በጥበብ ተወጥተውት እና ለብዙሀኑ ተማሪዎች ሲባል የአንዳንድ ተማሪዎችን ያልተገባ ስነምግባር በትዕግስት አልፈውት እንደሚሆን እንጠብቃለን።
3. በተለይ ደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ላይ የተፈጠረው ያለመረጋጋት ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲፈተኑ የሚያስችል ሁኔታ ነበር ብሎ ለማለት ያስቸግራል። የነበረው ሁኔታ ፈተና አቋርጠው በሄዱት ላይ ብቻም ሳይሆን በፈተና ሂደቱ ውስጥ በነበሩት ተማሪዎች ላይም ተፅዕኖው ከባድ እንደሚሆን ይገመታል።
በዚህም ሁከት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው ውጤታማ ተማሪዎቻችን ባላሰቡት መንገድ ተስተጓጉለውብናል።
በአጠቃላይ የመጀመሪያው ዙር ፈተና እንደሀገር የመጀመሪያ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከት/ቢሮውም በኩል የነበሩ ከቅድመዝግጅት መጓደለም ጋር የተያያዙት መለስተኛ ችግሮች (በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ወቅት ማስተካከያ የተደረገባቸው ችግሮች)ተጨምረውበት በርካታ ተማሪዎቻችን ከፈተና ስርዓቱ የተስተጓጎሉበት ሁኔታ መፈጠሩ የትምህርት ማህበረሰቡን እጅግ በጣም ያሳዘነ ክስተት ሆኗል።
የነበሩ የቅድመዝግጅት መጓደሎችን እና አጠቃላይ ሂደቱን በሚመለከት ለሚመለከተው አካል በጊዜው የግምገማ ሪፓርት ስላቀረብን እዚህ ላይ መዘርዘሩ አያስፈልግም።
በአጠቃላይ ከግምገማ ሪፓርታችንም ሆነ ከሌሎች ነባራዊ ሁኔታዎች በመነሳት ውሳኔ ሰጭው አካል የሚሰጠው ውሳኔ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀጣዩ ዙር ፈተና የባለፋት ችግሮች በድጋሜ እናንተንም እንዳያጋጥሟችሁ ተገቢውን የጥንቃቄ ቅድመዝግጅት እንድታደርጉ ከወዲሁ እያሳሰብሁ መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
የአብክመ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ