✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ሚያዝያ ፴ ❖
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
❖ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
=>እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ
ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት::
እግዚአብሔር
ግን ደግ ነውና ይሔው ሚያዝያን አስፈጸመን::
+ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ:-
*ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
*ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል
(ሙተዋል)::
+እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪዋን ዘመን ደግሞ ለንስሃና
ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::
+"+ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ +"+
+በዚሕች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ: ወንጌላዊ:
ሐዋርያ: ሰማዕት: ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ
ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል::
+ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም: አባቱ አርስጥቦሎስ
ይባላሉ:: በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ
በሚገባ ተምሮ
ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል::
+የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ
በእድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር:: ለ3
ዓመታት ከጌታ
እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን
ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል::
+በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው::
ክህነትን ያገኘን ከርሱ ነውና:: ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ
ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ: ሊቀ
ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር::
+ቅዱሱ ክቅዱስ ዻውሎስ: ከበርናባስና ዼጥሮስ ጋር
ተጉዟል:: ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ
አካባቢ በዚህ ቀን [በ60 ዓ/ም አካባቢ]
አረማውያን ገድለውታል::
=>ዳግመኛ በዚህ ቀን የቅዱስ ማርቆስን ወላጆችን
እናስባቸው ዘንድ ይገባል::
❖ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) የጌታ ቅን አገልጋይ
የነበረ፡፡
❖ቅድስት ማርያም (እናቱ)
*ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ:
*ጌታችንን ያገለገለች:
*ቤቷን ለሐዋርያትና ለጌታ በስጦታ ያበረከተች ቅድስት
ናት::
+ቤቷም (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን
ስትሆን ይህች ቤት መንፈስ ቅዱስ ወርዶባታል::
የእመቤታችን ግንዘትም
ተከናውኖባታል::
❖እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ ቤተሰብ በረከትን
ያድለን::
=>ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ)
3.ቅድስት ማርያም (እናቱ)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
=>+"+ . . . እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ
ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ
ማርያም ቤት መጣ:: ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ
ባንኩዋኩዋ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ
ዘንድ ቀረበች:: የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ
ከደስታዋ የተነሳ ደጁን አልከፈተችም:: ነገር ግን ወደ
ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች::
+"+ (ሐዋ. 12:12-15)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/felegetibebmedia
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ሚያዝያ ፴ ❖
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
❖ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
=>እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ
ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት::
እግዚአብሔር
ግን ደግ ነውና ይሔው ሚያዝያን አስፈጸመን::
+ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ:-
*ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
*ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል
(ሙተዋል)::
+እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪዋን ዘመን ደግሞ ለንስሃና
ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::
+"+ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ +"+
+በዚሕች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ: ወንጌላዊ:
ሐዋርያ: ሰማዕት: ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ
ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል::
+ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም: አባቱ አርስጥቦሎስ
ይባላሉ:: በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ
በሚገባ ተምሮ
ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል::
+የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ
በእድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር:: ለ3
ዓመታት ከጌታ
እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን
ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል::
+በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው::
ክህነትን ያገኘን ከርሱ ነውና:: ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ
ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ: ሊቀ
ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር::
+ቅዱሱ ክቅዱስ ዻውሎስ: ከበርናባስና ዼጥሮስ ጋር
ተጉዟል:: ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ
አካባቢ በዚህ ቀን [በ60 ዓ/ም አካባቢ]
አረማውያን ገድለውታል::
=>ዳግመኛ በዚህ ቀን የቅዱስ ማርቆስን ወላጆችን
እናስባቸው ዘንድ ይገባል::
❖ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) የጌታ ቅን አገልጋይ
የነበረ፡፡
❖ቅድስት ማርያም (እናቱ)
*ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ:
*ጌታችንን ያገለገለች:
*ቤቷን ለሐዋርያትና ለጌታ በስጦታ ያበረከተች ቅድስት
ናት::
+ቤቷም (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን
ስትሆን ይህች ቤት መንፈስ ቅዱስ ወርዶባታል::
የእመቤታችን ግንዘትም
ተከናውኖባታል::
❖እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ ቤተሰብ በረከትን
ያድለን::
=>ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ)
3.ቅድስት ማርያም (እናቱ)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
=>+"+ . . . እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ
ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ
ማርያም ቤት መጣ:: ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ
ባንኩዋኩዋ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ
ዘንድ ቀረበች:: የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ
ከደስታዋ የተነሳ ደጁን አልከፈተችም:: ነገር ግን ወደ
ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች::
+"+ (ሐዋ. 12:12-15)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/felegetibebmedia
✝✝✝ እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✝✝
+*" 🌷ልደታ ለማርያም ድንግል🌷 "*+
✝ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ:: ✝
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "
=>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::
+ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::
+እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)
+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::
"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8)
=>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)
+"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9)
+እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች::
=>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
-ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:-
-ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::
+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::
=>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::
=>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ)
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቴክታና በጥሪቃ
4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር
=>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::
በውስጧም ሰው ተወለደ::
እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/felegetibebmedia
+*" 🌷ልደታ ለማርያም ድንግል🌷 "*+
✝ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ:: ✝
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "
=>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::
+ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::
+እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)
+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::
"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8)
=>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)
+"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9)
+እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች::
=>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
-ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:-
-ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::
+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::
=>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::
=>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ)
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቴክታና በጥሪቃ
4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር
=>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::
በውስጧም ሰው ተወለደ::
እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/felegetibebmedia
Telegram
ፈለገ ጥበብ ሚዲያ felegetbeb media
ይህ ቻናል የደብረ ዘይት ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ወ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ፈለገ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት የመረጃ ሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ሲሆን ይህ ቻናል ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሆኑ አስተምህሮቶች በየእለቱ የሚለቀቅበት ቻናል ነው ቻናላችን ስለተቀላቀሉ በእግዚአብሔር ፅኑ ፍቅር እናመሰግናለን ።
#የፈለገ_ጥበብ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የመረጃ_ሚዲያ_እና_ህዝብ_ግንኙነት_ክፍል
#FTM
#የፈለገ_ጥበብ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የመረጃ_ሚዲያ_እና_ህዝብ_ግንኙነት_ክፍል
#FTM
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ክብረ በአል በደብረዘይት ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ወደብረ ብስራ ቅዱስ ገብርኤል አብያተክርስትያናት በታላቅ ድምቀት ተከበረ፡፡
ግንቦት 1/2016 ዓ.ም
ፈለገ ጥበብ ሚዲያ
ግንቦት 1/2016 ዓ.ም
ፈለገ ጥበብ ሚዲያ
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
Forwarded from ️ፈለገ ጥበብ Photography (ፈለገ ጥበብ ፎቶ ማህደር ዘፈለገ ጥበብ ሚዲያ)
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ግንቦት ፪ ❖
❖ ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
+"+ ቅዱስ ኢዮብ +"+
+የትዕግስት አባት ቅዱስ ኢዮብ በቅዱስ መጽሐፍ ላይ
እንደተመለከትነው ያልተፈተነበት ነገር የለም:: ሐረገ
ትውልዱም
ከአባታችን አብርሃም ይመዘዛል::
*አብርሃም ይስሐቅን
*ይስሐቅ ኤሳውን
*ኤሳው ራጉኤልን
*ራጉኤል ዛራን
*ዛራ ኢዮብን ይወልዳሉ::
+ቅዱስ ኢዮብ የነበረው እሥራኤል በግብፅ በባርነት ሳሉ
ነበር:: ኢዮብ ይሕ ቀረህ የማይሉት ባለጠጋ: ደግና
እግዚአብሔርን
አምላኪ ነበር:: የኢዮብ ደግነት የተመሰከረው በሰው
(በፍጡር) አንደበት አልነበረም:: በራሱ በፈጣሪ አንደበት
እንጂ::
+በዚህ የቀና ጠላት ዲያብሎስ ግን ኢዮብን ይፈትነው
ዘንድ ከአምላክ አስፈቀደ:: ጌታችን የጻድቁን የትዕግስት
መጠን
ሊገልጥ ወዷልና ሰይጣን ኢዮብን በሐብቱ መጣበት::
በአንድ ጀምበርም ድሃ ሆነ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን ባረከ::
+ሰይጣን ቀጠለ:- የአብራኩን ክፋዮች (ልጆቹን)
አሳጣው:: ኢዮብ አሁንም አመሰገነ::
+በሦስተኛው ግን ሰውነቱን በቁስል መታው:: ቁስል ሲባል
በዘመኑ እንደምታዩት ዓይነት አልነበረም:: ከሰው ሕሊና
በላይ
የሆነ አሰጨናቂ ደዌ ነበር እንጂ:: ጻድቁ የአንድ ወጣት
እድሜ ያሕል በመከራው ጽናት እየተሰቃየ ገላውን በገል
ያከው
ነበር::ከአፉ ግን ተመስገን ማለትን አላቁዋረጠም::
+በመጨረሻም ሰይጣን በሚስቱ መጣበት::
"እግዚአብሔርን ተሳደብ" አለችው:: እርሱ ግን መለሰ:-
"እግዚአብሔር ሰጠ:
እግዚአብሔርም ነሣ: ስሙ የተባረከ ይሁን::"
+ከዚሕ ሁሉ ነገር በኋላ እግዚአብሔር ሰይጣንን ከጎዳናው
አስወገደው:: ጤናውን: ሐብቱን: ልጆቹን ለኢዮብ
መለሰለት::
ካለው እድሜ ላይ 140 ዓመት ጨመረለት:: ጻድቅና
የትዕግስት ሰው ቅዱስ ኢዮብ በ248 ዓመቱ በዚሕች ቀን
ዐረፈ::
=>እግዚአብሔር አምላክ ከጻድቁ ትዕግስትና በረከት
አይለየን::
❖ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ (የትእግስት አባት)
2.አባ ቴዎድሮስ ሊቀ ምኔት (የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ
መዝሙርና የአቡነ አረጋዊ ጉዋደኛ)
3."22" ሰማዕታት (የአባ ኤሲ ማሕበር)
❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
2፡ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
3፡ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
4፡ ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5፡ አባ ጳውሊ ገዳማዊ
6፡ አባ ሕርያቆስ ዘብሕንሳ
++"+ ወንድሞች ሆይ! የመከራና የትዕግስት ምሳሌ
የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ::
እነሆ
በትዕግስት የጸኑትን ብጹዓን እንላቸዋለን:: ኢዮብ እንደ
ታገሠ ሰምታቹሃል:: ጌታም እንደፈጸመለት አይታቹሃል::
ጌታ እጅግ የሚምር: የሚራራም ነውና:: +"+ (ያዕ.
5:10)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ ግንቦት ፪ ❖
❖ ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
+"+ ቅዱስ ኢዮብ +"+
+የትዕግስት አባት ቅዱስ ኢዮብ በቅዱስ መጽሐፍ ላይ
እንደተመለከትነው ያልተፈተነበት ነገር የለም:: ሐረገ
ትውልዱም
ከአባታችን አብርሃም ይመዘዛል::
*አብርሃም ይስሐቅን
*ይስሐቅ ኤሳውን
*ኤሳው ራጉኤልን
*ራጉኤል ዛራን
*ዛራ ኢዮብን ይወልዳሉ::
+ቅዱስ ኢዮብ የነበረው እሥራኤል በግብፅ በባርነት ሳሉ
ነበር:: ኢዮብ ይሕ ቀረህ የማይሉት ባለጠጋ: ደግና
እግዚአብሔርን
አምላኪ ነበር:: የኢዮብ ደግነት የተመሰከረው በሰው
(በፍጡር) አንደበት አልነበረም:: በራሱ በፈጣሪ አንደበት
እንጂ::
+በዚህ የቀና ጠላት ዲያብሎስ ግን ኢዮብን ይፈትነው
ዘንድ ከአምላክ አስፈቀደ:: ጌታችን የጻድቁን የትዕግስት
መጠን
ሊገልጥ ወዷልና ሰይጣን ኢዮብን በሐብቱ መጣበት::
በአንድ ጀምበርም ድሃ ሆነ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን ባረከ::
+ሰይጣን ቀጠለ:- የአብራኩን ክፋዮች (ልጆቹን)
አሳጣው:: ኢዮብ አሁንም አመሰገነ::
+በሦስተኛው ግን ሰውነቱን በቁስል መታው:: ቁስል ሲባል
በዘመኑ እንደምታዩት ዓይነት አልነበረም:: ከሰው ሕሊና
በላይ
የሆነ አሰጨናቂ ደዌ ነበር እንጂ:: ጻድቁ የአንድ ወጣት
እድሜ ያሕል በመከራው ጽናት እየተሰቃየ ገላውን በገል
ያከው
ነበር::ከአፉ ግን ተመስገን ማለትን አላቁዋረጠም::
+በመጨረሻም ሰይጣን በሚስቱ መጣበት::
"እግዚአብሔርን ተሳደብ" አለችው:: እርሱ ግን መለሰ:-
"እግዚአብሔር ሰጠ:
እግዚአብሔርም ነሣ: ስሙ የተባረከ ይሁን::"
+ከዚሕ ሁሉ ነገር በኋላ እግዚአብሔር ሰይጣንን ከጎዳናው
አስወገደው:: ጤናውን: ሐብቱን: ልጆቹን ለኢዮብ
መለሰለት::
ካለው እድሜ ላይ 140 ዓመት ጨመረለት:: ጻድቅና
የትዕግስት ሰው ቅዱስ ኢዮብ በ248 ዓመቱ በዚሕች ቀን
ዐረፈ::
=>እግዚአብሔር አምላክ ከጻድቁ ትዕግስትና በረከት
አይለየን::
❖ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ (የትእግስት አባት)
2.አባ ቴዎድሮስ ሊቀ ምኔት (የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ
መዝሙርና የአቡነ አረጋዊ ጉዋደኛ)
3."22" ሰማዕታት (የአባ ኤሲ ማሕበር)
❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
2፡ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
3፡ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
4፡ ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5፡ አባ ጳውሊ ገዳማዊ
6፡ አባ ሕርያቆስ ዘብሕንሳ
++"+ ወንድሞች ሆይ! የመከራና የትዕግስት ምሳሌ
የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ::
እነሆ
በትዕግስት የጸኑትን ብጹዓን እንላቸዋለን:: ኢዮብ እንደ
ታገሠ ሰምታቹሃል:: ጌታም እንደፈጸመለት አይታቹሃል::
ጌታ እጅግ የሚምር: የሚራራም ነውና:: +"+ (ያዕ.
5:10)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
✝✞✝ በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን:: ✝✞✝
🛑ግብረ-ሰላም 🛑
(ከአንድ ወንድም በደረሰኝ ጥያቄ መሠረት ለጊዜው እነዚህን ጉዳዮች ብቻ እንመልከት)
"ገብረ ሰላመ በመስቀሉ::
ትንሳኤሁ አግሃደ::"
1." ትርጉም "
=>"ግብረ-ሰላም" ማለት "የሰላም : የፍቅር : የአንድነት ተግባር" እንደ ማለት በጥሬው ሊተረጐም ይችላል::
2." ምንነት "
=>ግብረ-ሰላም የጌታን ትንሳኤ ተከትለው በሚመጡ 50 ቀናት የሚከናወን ተግባር ሲሆን መንፈሳዊና ሥጋዊ ድግሶች የሞሉበት ትውፊታዊ ክዋኔ ነው::
3." መነሻ "
=>ቤተ ክርስቲያናችን የሁሉ ነገሯ መሠረት መድኃኔ ዓለምና ትዕዛዛቱ ናቸው:: የግብረ ሰላምም መሠረቱ ቅዱስ መጽሐፍ ነው:: በብሉይ ኪዳን አገልጋይ ካህናትና ነቢያትን መመገብ በጐና የተለመደ ተግባር ነበር::
+ኦሪት ላይ እንደተጻፈው ቅዱስ ኢያሱ ርስትን ሲያካፍል ለካህናት አልሰጣቸውም:: ምክንያቱም የካህናቱ ርስት ሕዝቡ ነበርና:: (ኢያ. 21) በመጽሐፈ ነገሥት 2ኛ ያቺ ደግ ሱነማይት ሴት ለቅዱስ ኤልሳዕን ትመግበው : ታሳድረውም እንደ ነበርም ተጽፏል:: እንዲያውም ቤት ሁሉ ሠርታለታለች:: (2ነገ. 4:8)
+በሐዲስ ኪዳን ደግሞ የክብር ባለቤት : አማናዊው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰዎች ቤት ገብቶ ግብር ሲያገቡለት (ሲጋበዝ) እንደ ነበር ቅዱስ ወንጌል ይናገራል:: እንደ ማሳያም ቤተ ማርታን (ሉቃ. 10:38) : ቤተ ስምዖን ዘለምጽን (ማቴ. 26:6) : ቤተ አልዓዛር ወኒቆዲሞስን (ዮሐ. 12:1) መጥቀስ እንችላለን::
<< ስለዚህ ካህናትን ወደ ቤት ጠርቶ መጋበዙ (ግብረ ሰላም ማድረጉ) መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው:: >>
+በተአምረ ኢየሱስ ላይ እንደተጠቀሰው ደግሞ በበዓለ ሃምሳ ካህናትን እንደ አቅሙ (ከ1 ጀምሮ) ያበላ በፍርድ ቀን ከመከራ እንደሚያመልጥ ጌታ መናገሩ ተዘግቧል::
+በተለይ ግን አበው ሐዋርያትን ጌታ እንዲህ ብሏቸዋል ሲል ቅዱስ ማቴዎስ ነግሮናል::
"በምትገቡባትም በማናቸውም ከተማ ወይም መንደር : በዚያ የሚገባው ማን እንደሆነ በጥንቃቄ መርምሩ:: እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ:: ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ:: ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት:: (ይደርበት) ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ:: ከማይቀበላችሁም : ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ:: እውነት እላቹሃለሁ:: በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ፍርድ ይቀልላቸዋል::" (ማቴ. 10:11)
+በተጨማሪም "የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሠር" ያለውን የኦሪት ትዕዛዝ "ይደልዎ አስቦ ለዘይትቀነይ-ለሠራተኛ ደሞዙ ይገባዋል" ሲል ጌታ ተናግሮታል:: የአነጋገሩ ምሥጢር ብዙ ቢሆንም በጥሬው ግን የካህናት ደሞዝ ከምዕመናን መሆኑን ያሳያል:: (ዘዳ.25:4, 1ቆሮ.9:9, ማቴ.10:10
4." አፈጻጸም "
=>ግብረ-ሰላም በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ (በቤተ ምርፋቅ) ሊከወን ቢችልም ብዙ ጊዜ የሚፈጸመው በምዕመናን ቤት ነው:: ለምን? . . . ቤታቸው በአበው ካህናት ይባረክ ዘንድ ይገባልና::
+ከትንሳኤ ማግስት ጀምሮ ምዕመናን እንደ አቅማቸው:-
1.መምህረ ንስሃ (የነፍስ አባታቸውን)
2.ከደብሩ ካህናት በቁጥር
3.የደብሩን ሁሉ አገልጋዮች
4.የአድባራትን ሊቃውንት . . . ሊጠሩ ይችላሉ:: ባለጠጐች ከሆኑ ብዙ ሊጠሩ ይችላሉ:: የኔ ብጤ የሆነ ደግሞ እንደ አቅሙ ማለት ነው::
+የተጠሩ ካህናት (ሊቃውንት) ወደ ቤት ሲደርሱ የቤቱ አባወራ አደግድጐ : እማወራዋ አገልድመው ከበር ላይ ይጠብቃሉ:: "እንኩዋን ደህና መጣችሁ" እያሉ አስገብተው በየማዕረጋቸው እንዲቀመጡ ይደረጋል::
+ከሁሉ የሚቀድም ጸሎት ነውና ማዕዱ ቀርቦ ጸሎት በርዕሰ ደብሩ ወይም በመምህሩ ይደረጋል:: ሲበላም በመስሪያ (6 ሆነው) ሲሆን ይህም ከ6ቱ ቃላተ ወንጌል ብዙዎቹ የሚከወኑበት መሆኑን ያጠይቃል:: በየመሥሪያው አበው እየቆረሱ "በእንተ ማርያም" ሰጥተው በሥርዓት ይበላል::
+መጠጥም (ወይን : ጠላ : ጠጅ ወይም ሌላ ሊሆን ይችላል) ጐን ለጐን ይቀርባል:: አጥንት ካለ እንደየ ማዕርጋቸው ለመምህራንና ለአበው ፍሪምባ : ቅልጥም ለምክትል መምህራን ወዘተ. ተሰጥቶ በቃለ ማኅዘኒ "ስብሐት ለአብ" ተብሎ እግዚአብሔር ይመሰገናል::
+መምህሩ አፉን አጥርቶ ትምህርት ከሰጠ በሁዋላ አበው እየተነሱ ይመርቃሉ:: የዜማ መምህራን በበኩላቸው የክርስቶስን ትንሳኤና የማዳን ሥራ የሚያዘክሩ ወረቦችን እየቃኙ ይወርባሉ:: ይቸበችባሉ:: በመጨረሻም ኑዛዜ ተሰጥቶ ስንብት ይሆናል::
+አበውና ካህናት "ስብሐት" ብለው ያተረፉትንም የቤቱ ባለቤቶች : ሕጻናትና ጐረቤት ሁሉ በደስታ ተካፍሎ ይበላዋል:: እጅግ ታላቅ በረከት ነውና::
5." ግብረ-ሰላም በትውፊት "
=>ይህ መንፈሳዊ ተግባር ምንም እንኩዋ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቢሆንም በቤተ ክርስቲያንና በሃገራችን ታሪክም ተዘግቦ የሚገኝ : ለባለጠጐች : ለመሣፍንቱና ለነገሥታቱ ከነ ስሙም "ግብር ማግባት" የሚባል ነበር::
+በዘመነ ሐዋርያትና ሰማዕታት አገልጋይ ካህናትን ሰብስቦ መጋበዙ የሚታሰብ አልነበረም:: ምክንያቱም ጊዜው የመከራና ክርስቲያኖች መብታቸው የተነፈገበት ነበርና::
+ከዘመነ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ወዲህ ግን ተመሳሳይ ግብር የማግባት (የግብረ ሰላም) ተግባራት እንደ ነበሩ ይታመናል:: እንደ ምሳሌም በ4ኛውና 5ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ደጋግ ነገሥታት (እነ ቴዎዶስዮስ 1ኛና 2ኛ : አርቃድዮስ : አኖሬዎስ : ዘይኑን እና አንስጣስዮስ) እንዲሁ ያደርጉ እንደ ነበር ገድላተ ቅዱሳን ያሳያሉ::
+በሃገራችን ኢትዮዽያም ከብሉይ ኪዳን ሲያያዝ የመጣው ተግባር በክርስትና ጸንቶ መቀጠሉን በነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች ላይ መመልከት ይቻላል:: ሁሉም ነገሥታት ይህንን ያደርጉ ነበር ብሎ መናገር የሚቻልም ይመስለኛል:: በሕዝቡ ደረጃም አበው እና እማት ይህንን ሲከውኑ እዚህ ደርሰናል::
6." ዛሬስ "
=>ግብረ-ሰላም ዛሬም በትውፊታዊ ሥርዓቱ ቀጥሎ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች ይከወናል:: በተለይ ደግሞ በሰሜኑ አካባቢ:: ነገር ግን አፈጻጸሙ ላይ ከሚታዩ ስሕተቶች የተነሳ ለጊዜውም ቢሆን እያስነቀፈን ይገኛል::
1.የተግባሩን መንፈሳዊነት ያልተረዱ አንዳንድ ምዕመናን . . . ሲጀመር "እንካ ብላ : አፈር ብላ" ዓይነት ግብዣ እያደረጉ አበው ካህናትን ሲያቀሉ ተመልክተናል::
2.በአንድ ጊዜ ጠጅ : ጠላ : አረቄ እና ውስኪን ቀላቅለው የሚጋብዙ እንዳሉም ሰምቻለሁ::
3.በአንዳንድ ቦታዎች ደግሞ "ማኅሌተ ገንቦ" በሚል ኃጢአት የሆነውን ዘፈን የሚሞክሩም አይጠፉምና "ቢታሰብበት!" ባይ ነኝ::
☞ዘንድሮ (በ2012) ደግሞ ባብዛኛው በኮሮና ቫይረስ ሰበብ ቀርቷል ብሎ ለመናገር በሚያስደፍር ደረጃ ላይ መድረሱን ታዝቤአለሁ፡፡ አንዳንድ ደጋግ ሰዎች ለበረከት ቢያደርጉትም፡፡
+ይህንን የመሰለ መጽሐፋዊ : ትውፊታዊና ታሪካዊ የበረከት ሃብታችንን በሥርዓቱ ማስቀጠል ብንችል . . . ወዲህ እንጠቀማለን:: ወዲያ ደግሞ ለትውልድ እናስተላልፋለን::
‹‹የእግዚአብሔር ሙላቱ በእርሱ እንዲኖር በእርሱ በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ያሉት ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና ›› (ቆላ. 1:19-20)
✝✞✝ በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን:: ✝✞✝
🛑ግብረ-ሰላም 🛑
(ከአንድ ወንድም በደረሰኝ ጥያቄ መሠረት ለጊዜው እነዚህን ጉዳዮች ብቻ እንመልከት)
"ገብረ ሰላመ በመስቀሉ::
ትንሳኤሁ አግሃደ::"
1." ትርጉም "
=>"ግብረ-ሰላም" ማለት "የሰላም : የፍቅር : የአንድነት ተግባር" እንደ ማለት በጥሬው ሊተረጐም ይችላል::
2." ምንነት "
=>ግብረ-ሰላም የጌታን ትንሳኤ ተከትለው በሚመጡ 50 ቀናት የሚከናወን ተግባር ሲሆን መንፈሳዊና ሥጋዊ ድግሶች የሞሉበት ትውፊታዊ ክዋኔ ነው::
3." መነሻ "
=>ቤተ ክርስቲያናችን የሁሉ ነገሯ መሠረት መድኃኔ ዓለምና ትዕዛዛቱ ናቸው:: የግብረ ሰላምም መሠረቱ ቅዱስ መጽሐፍ ነው:: በብሉይ ኪዳን አገልጋይ ካህናትና ነቢያትን መመገብ በጐና የተለመደ ተግባር ነበር::
+ኦሪት ላይ እንደተጻፈው ቅዱስ ኢያሱ ርስትን ሲያካፍል ለካህናት አልሰጣቸውም:: ምክንያቱም የካህናቱ ርስት ሕዝቡ ነበርና:: (ኢያ. 21) በመጽሐፈ ነገሥት 2ኛ ያቺ ደግ ሱነማይት ሴት ለቅዱስ ኤልሳዕን ትመግበው : ታሳድረውም እንደ ነበርም ተጽፏል:: እንዲያውም ቤት ሁሉ ሠርታለታለች:: (2ነገ. 4:8)
+በሐዲስ ኪዳን ደግሞ የክብር ባለቤት : አማናዊው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰዎች ቤት ገብቶ ግብር ሲያገቡለት (ሲጋበዝ) እንደ ነበር ቅዱስ ወንጌል ይናገራል:: እንደ ማሳያም ቤተ ማርታን (ሉቃ. 10:38) : ቤተ ስምዖን ዘለምጽን (ማቴ. 26:6) : ቤተ አልዓዛር ወኒቆዲሞስን (ዮሐ. 12:1) መጥቀስ እንችላለን::
<< ስለዚህ ካህናትን ወደ ቤት ጠርቶ መጋበዙ (ግብረ ሰላም ማድረጉ) መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው:: >>
+በተአምረ ኢየሱስ ላይ እንደተጠቀሰው ደግሞ በበዓለ ሃምሳ ካህናትን እንደ አቅሙ (ከ1 ጀምሮ) ያበላ በፍርድ ቀን ከመከራ እንደሚያመልጥ ጌታ መናገሩ ተዘግቧል::
+በተለይ ግን አበው ሐዋርያትን ጌታ እንዲህ ብሏቸዋል ሲል ቅዱስ ማቴዎስ ነግሮናል::
"በምትገቡባትም በማናቸውም ከተማ ወይም መንደር : በዚያ የሚገባው ማን እንደሆነ በጥንቃቄ መርምሩ:: እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ:: ወደ ቤትም ስትገቡ ሰላምታ ስጡ:: ቤቱም የሚገባው ቢሆን ሰላማችሁ ይድረስለት:: (ይደርበት) ባይገባው ግን ሰላማችሁ ይመለስላችሁ:: ከማይቀበላችሁም : ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ:: እውነት እላቹሃለሁ:: በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ፍርድ ይቀልላቸዋል::" (ማቴ. 10:11)
+በተጨማሪም "የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሠር" ያለውን የኦሪት ትዕዛዝ "ይደልዎ አስቦ ለዘይትቀነይ-ለሠራተኛ ደሞዙ ይገባዋል" ሲል ጌታ ተናግሮታል:: የአነጋገሩ ምሥጢር ብዙ ቢሆንም በጥሬው ግን የካህናት ደሞዝ ከምዕመናን መሆኑን ያሳያል:: (ዘዳ.25:4, 1ቆሮ.9:9, ማቴ.10:10
4." አፈጻጸም "
=>ግብረ-ሰላም በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ (በቤተ ምርፋቅ) ሊከወን ቢችልም ብዙ ጊዜ የሚፈጸመው በምዕመናን ቤት ነው:: ለምን? . . . ቤታቸው በአበው ካህናት ይባረክ ዘንድ ይገባልና::
+ከትንሳኤ ማግስት ጀምሮ ምዕመናን እንደ አቅማቸው:-
1.መምህረ ንስሃ (የነፍስ አባታቸውን)
2.ከደብሩ ካህናት በቁጥር
3.የደብሩን ሁሉ አገልጋዮች
4.የአድባራትን ሊቃውንት . . . ሊጠሩ ይችላሉ:: ባለጠጐች ከሆኑ ብዙ ሊጠሩ ይችላሉ:: የኔ ብጤ የሆነ ደግሞ እንደ አቅሙ ማለት ነው::
+የተጠሩ ካህናት (ሊቃውንት) ወደ ቤት ሲደርሱ የቤቱ አባወራ አደግድጐ : እማወራዋ አገልድመው ከበር ላይ ይጠብቃሉ:: "እንኩዋን ደህና መጣችሁ" እያሉ አስገብተው በየማዕረጋቸው እንዲቀመጡ ይደረጋል::
+ከሁሉ የሚቀድም ጸሎት ነውና ማዕዱ ቀርቦ ጸሎት በርዕሰ ደብሩ ወይም በመምህሩ ይደረጋል:: ሲበላም በመስሪያ (6 ሆነው) ሲሆን ይህም ከ6ቱ ቃላተ ወንጌል ብዙዎቹ የሚከወኑበት መሆኑን ያጠይቃል:: በየመሥሪያው አበው እየቆረሱ "በእንተ ማርያም" ሰጥተው በሥርዓት ይበላል::
+መጠጥም (ወይን : ጠላ : ጠጅ ወይም ሌላ ሊሆን ይችላል) ጐን ለጐን ይቀርባል:: አጥንት ካለ እንደየ ማዕርጋቸው ለመምህራንና ለአበው ፍሪምባ : ቅልጥም ለምክትል መምህራን ወዘተ. ተሰጥቶ በቃለ ማኅዘኒ "ስብሐት ለአብ" ተብሎ እግዚአብሔር ይመሰገናል::
+መምህሩ አፉን አጥርቶ ትምህርት ከሰጠ በሁዋላ አበው እየተነሱ ይመርቃሉ:: የዜማ መምህራን በበኩላቸው የክርስቶስን ትንሳኤና የማዳን ሥራ የሚያዘክሩ ወረቦችን እየቃኙ ይወርባሉ:: ይቸበችባሉ:: በመጨረሻም ኑዛዜ ተሰጥቶ ስንብት ይሆናል::
+አበውና ካህናት "ስብሐት" ብለው ያተረፉትንም የቤቱ ባለቤቶች : ሕጻናትና ጐረቤት ሁሉ በደስታ ተካፍሎ ይበላዋል:: እጅግ ታላቅ በረከት ነውና::
5." ግብረ-ሰላም በትውፊት "
=>ይህ መንፈሳዊ ተግባር ምንም እንኩዋ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቢሆንም በቤተ ክርስቲያንና በሃገራችን ታሪክም ተዘግቦ የሚገኝ : ለባለጠጐች : ለመሣፍንቱና ለነገሥታቱ ከነ ስሙም "ግብር ማግባት" የሚባል ነበር::
+በዘመነ ሐዋርያትና ሰማዕታት አገልጋይ ካህናትን ሰብስቦ መጋበዙ የሚታሰብ አልነበረም:: ምክንያቱም ጊዜው የመከራና ክርስቲያኖች መብታቸው የተነፈገበት ነበርና::
+ከዘመነ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ወዲህ ግን ተመሳሳይ ግብር የማግባት (የግብረ ሰላም) ተግባራት እንደ ነበሩ ይታመናል:: እንደ ምሳሌም በ4ኛውና 5ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ደጋግ ነገሥታት (እነ ቴዎዶስዮስ 1ኛና 2ኛ : አርቃድዮስ : አኖሬዎስ : ዘይኑን እና አንስጣስዮስ) እንዲሁ ያደርጉ እንደ ነበር ገድላተ ቅዱሳን ያሳያሉ::
+በሃገራችን ኢትዮዽያም ከብሉይ ኪዳን ሲያያዝ የመጣው ተግባር በክርስትና ጸንቶ መቀጠሉን በነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች ላይ መመልከት ይቻላል:: ሁሉም ነገሥታት ይህንን ያደርጉ ነበር ብሎ መናገር የሚቻልም ይመስለኛል:: በሕዝቡ ደረጃም አበው እና እማት ይህንን ሲከውኑ እዚህ ደርሰናል::
6." ዛሬስ "
=>ግብረ-ሰላም ዛሬም በትውፊታዊ ሥርዓቱ ቀጥሎ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች ይከወናል:: በተለይ ደግሞ በሰሜኑ አካባቢ:: ነገር ግን አፈጻጸሙ ላይ ከሚታዩ ስሕተቶች የተነሳ ለጊዜውም ቢሆን እያስነቀፈን ይገኛል::
1.የተግባሩን መንፈሳዊነት ያልተረዱ አንዳንድ ምዕመናን . . . ሲጀመር "እንካ ብላ : አፈር ብላ" ዓይነት ግብዣ እያደረጉ አበው ካህናትን ሲያቀሉ ተመልክተናል::
2.በአንድ ጊዜ ጠጅ : ጠላ : አረቄ እና ውስኪን ቀላቅለው የሚጋብዙ እንዳሉም ሰምቻለሁ::
3.በአንዳንድ ቦታዎች ደግሞ "ማኅሌተ ገንቦ" በሚል ኃጢአት የሆነውን ዘፈን የሚሞክሩም አይጠፉምና "ቢታሰብበት!" ባይ ነኝ::
☞ዘንድሮ (በ2012) ደግሞ ባብዛኛው በኮሮና ቫይረስ ሰበብ ቀርቷል ብሎ ለመናገር በሚያስደፍር ደረጃ ላይ መድረሱን ታዝቤአለሁ፡፡ አንዳንድ ደጋግ ሰዎች ለበረከት ቢያደርጉትም፡፡
+ይህንን የመሰለ መጽሐፋዊ : ትውፊታዊና ታሪካዊ የበረከት ሃብታችንን በሥርዓቱ ማስቀጠል ብንችል . . . ወዲህ እንጠቀማለን:: ወዲያ ደግሞ ለትውልድ እናስተላልፋለን::
‹‹የእግዚአብሔር ሙላቱ በእርሱ እንዲኖር በእርሱ በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ያሉት ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና ›› (ቆላ. 1:19-20)
Telegram
ፈለገ ጥበብ ሚዲያ felegetbeb media
ይህ ቻናል የደብረ ዘይት ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ወ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ፈለገ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት የመረጃ ሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ሲሆን ይህ ቻናል ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሆኑ አስተምህሮቶች በየእለቱ የሚለቀቅበት ቻናል ነው ቻናላችን ስለተቀላቀሉ በእግዚአብሔር ፅኑ ፍቅር እናመሰግናለን ።
#የፈለገ_ጥበብ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የመረጃ_ሚዲያ_እና_ህዝብ_ግንኙነት_ክፍል
#FTM
#የፈለገ_ጥበብ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የመረጃ_ሚዲያ_እና_ህዝብ_ግንኙነት_ክፍል
#FTM