FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.5K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ዕዙ የላቀ የግዳጅ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ክፍሎች የማበረታቻ ሽልማትና እውቅና ሰጠ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

የ6ኛ ዕዝ በተጠናቀቀው በጀት አመት የላቀ የግዳጅ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ክፍሎች ዕውቅና እና ሽልማት ሰጥቷል። የመቆያ ጊዚያቸውን የሸፈኑ እንዲሁም የመመልመያ መስፈርቱን ላሟሉ አመራሮችም ማዕረግ የማልበስ ሰነ ስርዓት አካሂዷል።

በዕለቱ የላቀ የግዳጅ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ክፍሎች የተዘጋጀላቸውን ሽልማት በመስጠትና ለማዕረግ ተሿሚዎች ማዕረግ በማልበስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፋት የዕዙ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ሽልማቱ ጥንካሪያችሁን የበለጠ አጎልብታችሁ እንድትቀጥሉ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል።

በተጠናቀቀው በጀት አመት የላቀ የግዳጅ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ክፍሎች እና የማዕረግ ተሿሚዎች ባገኙት የማዕረግ እድገት እና ሽልማት ተጠቅመው በቀጣይም የላቀ ጀግንነት በመፈፀም ሃገርና ህዝብን የሚያኮራ ተግባር መፈፀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ዕዙ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የአሸባሪና የፅንፈኛ ቡድኖችን በመደምሰስ የፀረ ሰላም ሃይሎችን ፍላጎት በማምከን የተወጣው ግዳጅ በበጀት አመቱ ህዝባዊነቱን በተግባር ያሳየበትና የማድረግ ብቀቱን ያረጋገጠበት እንደሆነ ያወሱት ዋና አዛዡ የእነዚህ ክፍሎች ሚና ከፍተኛ እንደነበርም አንስተዋል።

በተገኘው ድልና ስኬት በመበረታታት በቀጣይ 2018 አዲስ አመት ለበለጠ ውጤታማ የተልዕኮ አፈፃፀም በመዘጋጀት የፀረ ሰላም ሃይሎችን ሙሉ ለሙሉ በማጥፋት የህዝብን ሰላምና ደህንነት ማረጋገጥ የሚጠበቅ መሆኑንም አመላክተዋል።

የማዕረግ ዕድገት ተሿሚዎች እና በበጀት አመቱ ተሸላሚ የሆኑ አመራሮችም ባስመዘገቡት ውጤትና በተሰጣቸው ሽልማት መደሰታቸውን ገልፀው በቀጣይ ክፍሎቻቸውን መርተው የተሻለ ድል በመቀዳጀት የሚሰጣቸውን ማንኛውም ግዳጅ በቁርጠኝነትና በጀግንነት እንደሚፈፅሙ ተናግረዋል።

ዘጋቢ ደባልቅ አቤ
ፎቶ ግራፍ ይህአለም አታላይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍3122👏4🔥3
የ6ኛ ዕዝ ክፍለ ጦር የሰላምን አማራጭ ባልተቀበለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ ወስዷል።

‎የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ13 ቀን 2017 ዓ.ም

‎በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ለግዳጅ የተሰማራው የዕዙ መከታ ክፍለ ጦር የሰላምን አማራጭ ባልተቀበለው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን የክፍለ ጦሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ሌተናል ኮሎኔል ድልነካ ከድር ተናግረዋል።

‎የክፍለ ጦሩ የሠራዊት አባላት በወሰዱት እርምጃ ፅንፈኛው ቡድን ፤መሳሪያዎችን እና ተተኳሾችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገልፀዋል። ዘጋቢ ገረመው ባሴ ነው።
‎              
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
32👍11👏2
የስትራቴጂክ መሳሪያዎች ኮር የመመልመያ መሥፈርቱን ላሟሉ አባላቱ ማዕረግ አልብሷል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

የስትራቴጂክ መሳሪያዎች ኮር በሰው ሃብት አስተዳደር መመሪያ መሠረት መመልመያ መሥፈርቱን ላሟሉ አባላቱ ማዕረግ አልብሷል።

በማዕረግ ማልበስ ስነ-ስርዓቱ ለይ ተገኝተው ማዕረግ ያለበሱት የኮሩ ዋና አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ግርማ ክበበው የዕለቱ ተሿሚዎች ከአሁን ቀደም ባሳዩት መልካም ስነ-ምግባርና በግዳጅ አፈፃፀማቸው ውጤታማ መሆናቸው ታይቶ ለማዕረግ ዕድገት በመብቃታቸው ተቋሙ የፈቀደላቸውን ማዕረግ ማልበስ ተችሏል ብለዋል። ዘገባው የኮሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
29👍15🔥3👏3
የኢትዮጵያዊያን የአዲስ ዓመት ስጦታ

‎የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

‎የኢትዮጵያ ህዝቦች የሚሳሱለት፣ጉልበት ገንዘባቸውን ሰጥተው ተንከባክበው እዚህ ያደረሱት ፍፃሜው ሰምሮ ለምረቃ ቀን ለመታደም የሚጓጉለት ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ህዝብ የአዲስ ዓመት ስጦታ ነው።

‎ኢትዮጵያዊያን በአንድነታቸው እና በህብረታቸው አለፍ ሲልም በፅናት እና ጀግንነታቸው አድዋ ላይ ደማቅ ታሪክ ሰርተው ከሀገርም አልፎ አፍሪካን በኩራት እንዳስጠሩ ሁሉ ዛሬም ድረስ ወርቃማው የድል ቀለማቸው በአዲሱ ትውልድ አልደበዘዘም።

‎ኢትዮጵያዊያን ልዩነትን ጌጥ ብዝሃነትን ውበት አድርገው በመተባበር መሆን ያለበትን ማድረግ ችለዋል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ የመጣችባቸው ጊዜያት ያለፈችባቸው ዓመታት አስረጅዎች ናቸው።

ከውጭም ይሁን ከውስጥ በጦርነት ፈትነውን እንደ ብረት የጠነከርንባቸው በትክክለኛ ሚዛን የረታናቸው ምንጊዜም ቢሆን በሃገር እና በህዝብ ለመጣብን የማንቀመስ የእሳት ነበልባል መሆናችንን ደግመን ደጋግመን በሚገባቸው ልክ ያሳየን ኩሩ ኢትዮጵያዊያን ነን።

‎"ለጮኽብህ ውሻ ሁሉ ድንጋይ ስትወረውር የምትውል ከሆነ ካሰብክበት አትደርስም" ያለውን ሰው ባላስታውስም በሀሳቡ ግን እስማማለሁ ይላል ፀሃፊው።
‎በመሆኑም የታላቁ ህዳሴ ግድብ በተባበረ ክንድ በጋራ አመለካከትና እሳቤ ወደ ፍፃሜው ተቃርቧል።

የኢትዮጵያ ህዝብ በታላቁ ህዳሴ ግድብም ሆነ በሀገር ጉዳይ የሚመጣን ሁሉ የማይደራደር ሥለመሆኑ ግድቡ በቂ ማሳያ ነው።

‎እንደ ወታደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስኬት የተለየ ደስታን ይፈጥራል። የግድቡን ደህንነት የሰራተኞችን ሰላም የጠበቀ፣ እጥፍ ድርብ ግዳጁን የተዋጣ ሙያተኛ ደግሞ በተለዬ አግባብ ደሥተኛነቱ ይለያል።

ወታደር ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ እስከ ህይወት መስዋዕትነት የሚከፍል የሀገር ባለአደራ ነው። እናም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለህዝባችንም ሆነ ለሠራዊቱ የአዲስ አመት ስጦታ በመሆኑ ከምንም በላይ ያኮራናል ያሥደስተናል።

‎በገረመው ባሴ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍4438👏7🥰3🔥2
ለጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መረጃ እና ማገገሚያ ማዕከል ድጋፍ ተደረገ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክቶሬት  በየደረጃው የሚገኙ የተቋሙን ክፍሎች በማስተባበር በበጀት ዓመቱ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል። በዛሬው ዕለትም ከ240 በላይ ለሚሆኑ የጌርጌሴኖን ሴት የአእምሮ ህሙማን ከዋና መምሪያዎች እና ሌሎች ክፍሎች ጋር በመተባበር ድጋፍ ተደርጓል። 

የመከላከያ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ሠራዊቱ አቅሙ በፈቀደ መጠን ከኪሱ በማዋጣት ከ348 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የአልባሳት እና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ለሀገር ዋጋ የከፈሉ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ራሳቸውን መርዳት የተሳናቸውን ወገኖቻችንን መርዳት እና ማገዝ የሁላችንም ሀላፊነት ሊሆን ይገባል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ሌላው የማህበረሰብ ክፍልም መጥቶ ሊጎበኛቸው እና ድጋፍ ሊያደርግላቸው እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

እኛ በውትድርና ሙያችን ለሀገርና ለህዝብ ከምንከፍለው እንዲሁም ከምንሰራው የሙያ መስክ እና ከምንሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ካለን ላይ ቀንሰን ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረጋችን ለሌላውም አርአያ መሆን አለብን ያሉት የመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልና ዲያግኖስቲክ ማዕከል ሃላፊ ብርጋዲየር ጄኔራል ሽዋዬ ሃይሌ ናቸው።

የማዕከሉ መስራች ሊቀ-ህሩያን መለሰ አየለ ለተደረገው ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቅርበው ለሀገር መስዋዕትነት የምትከፍሉ የሀገር ምሰሶዎች መጥታችሁ ስለጎበኛችሁን እጅግ ደስ ብሎናል እናመሠግናለን ብለዋል።

ማዕከሉ በ1998 ዓ.ም በበጎ ፈቃደኞች መመስረቱን ገልፀው ጎዳና ላይ የወደቁትን በማንሳት ወደ ቀደመ ጤንነታቸው ለመመለስ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ብዙዎቹ ከጎዳና ላይ የተነሱት ህሙማን በአሁኑ ሰዓት ከህመማቸው አገግመው ለሌሎቹ አገልግሎት እየሰጡ በማየታቸው ከመቼውም ጊዜ በላይ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ዘጋቢ ብርሃን እንዳየሁ
ፎቶ ግራፍ ዕፀገነት ዴቢሳ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
24👍21🔥2