FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.49K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
አባላቱና አመራሩ ተናበው በመስራታቸው የሽብር ቡድኑን ማጥፋት እየተቻለ ነው።  

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

ጀግና አመራር ጀግና ተዋጊን ይፈጥራል ይህም አመራሩና አባሉ ተናበዉ በመስራት የሚፈጥሩት ጥምረት የድል አድራጊነት አንዱ አካል መሆኑን የማዕከላዊ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጄር ጄኔራል አብድሮ ከድር ተናግረዋል።

ምክትል አዛዡ በራስ ዳሽን ኮር ተገኝተዋል የሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃፀም ዉሎ ተመልክተዋል። የተፈጥሮና ሰዉ ሰራሽ መሰናክሎችን በማቋቋም እና ከምንም በላይ ህዝባዊ ወገንተኝነትን በማስቀደም የሰላም ፀር የሆነዉን አሸባሪ ቡድን በገባበት ገብቶ እስከመጨረሻው በመደምሰስ ለህዝብ እፎይታን መስጠት እንደሚጠበቅ አሥገንዝበዋል።

ሜጄር ጄኔራል አብድሮ ከድር ህዝብና መንግስት የሰጣችሁን አደራ በመጠበቅ ጠላትን አምርሮ በመጥላት ሀገርን በንቃት መጠበቅ እና ራስን ካልሆነ አመለካከት በማዉጣት ከሀሰት ፕሮፖጋንዳ በመውጣት እስካሁን ካስመዘገባችሁት ድል በላይ ለማሥመዝገብ የበለጠ ራሳችሁን ማዘጋጄት ይገባችኋል ብለዋል።

የኮሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው መንግስቱ በበኩላቸዉ አንደ ሀገር ብሎም እንደ ክፍል የተሰጠንን ግዳጅ በብቃት በመወጣትና የአሸባሪዉ ኦነግ ሸኔን በገባበት ገብተን በመደምሰስ የተሠጠንን ተልዕኮ እየፈፀምን ነው እንፈፅማለንም ብለዋል።

ጠላት ጫካ ለጫካ ቢሹለከለክም ሰራዊቱ እግር በእግር እየተከታተለ እየደመሰሰዉ ይገኛል ሲሉ ብርጋዲየር ጄኔራል አበባዉ መንግስቴ ተናግረዋል ። ዘጋቢ ብሩክ ታደሰ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👏2119👍6🔥2
በሁርሶ የ10ኛ ዙር ምልምል ሰልጣኞች ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
    
የሁርሶ ኮንቲንጀትንት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ምልምል ሰልጣኞች ከስልጠና ጎን ለጎን ለአራት ወራት በእግር እና በመረብ ኳስ እንዲሁም በገመድ ጉተታ ስፖርታዊ ውድድሮችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል።
   
በሰፖርታዊ ውድድር ፋፃሜ ላይ ተገኝተው ለአሸናፊ ቡድኖች ዋንጫ በመስጠት ንግግር ያደረጉት የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ ስፖርት ለወታደር ተልዕኮ ትልቅ እገዛ የሚያደርግ የጥንካሬው መገለጫ መለያ ባህሪው ነው ብለዋል።
   
የስፖርታዊ ውድድሩ ዋና አላማ ሰልጣኞች ከስልጠና ጎን ለጎን እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ እንዲግባቡ የሚረዳ ከመሆኑም ባለፈ አሃዳዊ ፍቅር እንዲኖራቸው አንድነታዊ መተሳሰብ እንዲያጠናክሩ በሰነ -ልቦና ዝግጁነት ውስጣዊ ሞራል መነቃቃት እንዲፈጠሩ የሚያሥችል መሆኑንም ገልፀዋል።
  
የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ስፖርት አስተባባሪ ሻለቃ ባሻ ደገፉ ማሞ በበኩላቸው በስፖርታዊ ውድድሩ ለተቋሙ ስፖርት ክለብ ተተኪ መሆን የሚችሉ ችሎታ ያላቸው ወጣቶች የመመልመል የመለየት ስራ መሠራቱን ተናግረዋል።
   
ውድድሩ ውስጣዊ ፍክክር ኖሮት በውጤት እንዲጠናቀቅ የሻለቃ አመራሮች እና አሰልጣኞች ሚና ከፍተኛ ሲሆን ተወዳዳሪዎች በወታደራዊ ዲስፕሊን  ታንፀው ጨዋታውን ለፍፃሜ አድርሰዋል።

በውድድሩም በእግር ኳስ አምሰተኛ ሻለቃ አንደኛ ሻለቃን 1ለ0 ፤ መረብ ኳስ ስድስተኛ ሻለቃ ሁለተኛ ሻለቃን 3ለ1፤ ገመድ ጉተታ ሁለተኛ ሻለቃ አንደኛ ሻለቃን 2ለ1 ያሸነፉ ሲሆን የተዘጋጀላቸውን ዋንጫ ከዕለቱ የክብር እንግዳ እጅ ተቀብለዋል።

ዘጋቢ ተስፋዬ ያረጋል
ፎቶግራፍ አበበ እያሱ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
48👍18🔥10🥰1