FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.49K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ዕዙ ተተኪ አመራሮችን የማፍራትና የማብቃት ሃላፊነቱን እየተወጣ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 03 ቀን 2017 ዓ.ም

ዕዙ ተተኪ አመራሮችን የማፍራትና የማብቃት ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጄነራል ግዛው ኡማ ተናግረዋል።

በአማራ ክልል በግዳጅ ላይ ለሚገኙ ጥሩ የስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ እና የመቆያ ጊዜያቸውን ለሸፈኑ  ለምስራቅ ዕዝ ስታፍ መስመራዊ መኮንኖች እና ባለሌላ ማዕረግተኞች ማዕረግ የማልበስ ስነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

በዕለቱ ለማዕረግ ተሿሚዎች ማዕረግ አልብሰው ንግግር ያደረጉት የምስራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጀር ጄኔራል ግዛው ኡማ የዕዙ የሠራዊት አባላት በተሰማራበት ቀጠና ግዳጁን በላቀ ውጤት እየፈፀመ መሆኑን በመጥቀስ ተቋማችንና ዕዛችን ትግል የትውልድ ቅብብሎሽ መሆኑን በመገንዘብ በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ተሞክሮ በመውሰድ ተተኪ አመራሮችን  የማፍራትና የማብቃት ሃላፊነታችንን እየተወጣን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የሀገራችን ብሄራዊ ጥቅምና ሀገራዊ ፍላጎትን ለማሟላት እንደ ሠራዊት ቀጣይ ለሚሰጠን ግዳጅ ዝግጁ ለመሆን ከእናንተ ከአመራሮች ብዙ ይጠበቃል ያሉት ምክትል አዛዡ ማዕረግ መልበስ ማለት ለሚቀጥለዉ ሃላፊነት መዘጋጀት ስለሆነ ራስን በዲሲፕሊን በማነፅ  ወደፊት ትልቅ ሃላፊነት እንዳለባቸሁ አዉቃችዉ ስራችሁን መስራት ይኖርባችኋል ብለዋል፡፡

ዘጋቢ ታደሰ ይሴ
ፎቶ ግራፍ ማሩፍ ደስታ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
39👍8
ለማዕከላዊ ዕዝ ስታፍ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 03 ቀን 2017 ዓ.ም

ስልጠናው በወታደራዊ የአመራርነት ክህሎት ላይ ትኩረቱን በማድረግ አካላዊና ስነ-አዕምሯዊ ግንባታዎችን አክሎ ተሰጥቷል።

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የስታፍ አመራሩን ያነጋገሩት የማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ ስልጠናው የስታፉ አመራር በተመደበበት የስራ ዘርፍ የቢሮ ስራዎችን ከመተግበርና ከማስተግበር ባሻገር በመስክ ስልታዊ እንቅስቃሴ ውጊያን መርቶ የመፈፀምና የማስፈፀም የላቀ ክህሎት ለመፍጠር አስችሎታል ብለዋል።

ዘመኑ የደረሰበትን የውትድርና ሳይንስ መረዳት ፣ ጊዜው የፈጠረውን የሳይኮሎጅ ጦርነት መገንዘብ ፣ ከሃሰት የፕሮፖጋንዳ ትርክት መጠበቅና በአንፃሩ ቴክኖሎጅውን ተጠቅሞ አስፈላጊ መረጃዎችን በማግኘት ፈጣን የኢንፎርሜሽን ልውውጥ በማከናወን ስታፉ ምን ጊዜም ከዘመን ጋር አብሮ መዘመን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የተዋጊው ሃይል ድል አድራጊነት በተግባር የሚረጋገጠው የስታፍ ክፍሉ በሚሰጠው ጠንካራ የድጋፍ አገልግሎት መሆኑን የጠቀሱት ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ ተመራቂ አመራሮች ከስልጠና የተገኘውን አቅም ወደ ተግባር በመለወጥ የተሰለፋችሁለትን ሃገርና ህዝብ የመጠበቅ ህገ-መንግስታዊ ተልዕኮ በቁርጠኝነት መፈፀም አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።

የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የጊቤ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል አርዓያ ገብረ በበኩላቸው የዕዙ ስታፍ አመራር በወሰደው ስልጠና በየትኛውም ቦታ ላይ ተመድቦ ለመስራት የሚያስችለውን ሁለንተናዊ አቅም መፍጠሩን ገልፀው ተጣጣፊና ሁለ ገብ ሆኖ  ተገንብቷል ሲሉ አረጋግጠዋል። ዘገባው የዕዙ ሚዲያ ቡድን ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
42👍18
ጤና ይስጥልን ጥቂት ሥለጤናዎ የወባ በሽታ ምልክቶችና መከላከያ መንገዶች

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮጵያ በአሁን ወቅት የክረምት ወቅትነቱን ተከትሎ የወባ ወረርሽኝ በስፋት ሊከሰት እንደሚችል ይገመታል፡፡

የወባ በሽታ በትንኝ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍ በዋነኛነት በትኩሳት የሚገለጥ ተወሳስቦ ለከፍተኛ አደጋ ሊዳርግ የሚችል በሽታ ነው፡፡ 

የወባ በሽታ በዓለም ላይ የበርካቶችን ህይወት  የሚቀጥፍ በትንኝ አማካኝትት የሚከሰት ተላላፊ በሽታ  እንደሆነም ይነገራል፡፡

የወባ በሽታ ሲታሰብ ትንኟ ከታማሚ ሰው የበሽታውን ተህዋስ በተለይ በኢትዮጵያ ፕላዝሞዴም ፋሲፋረም በተለምዶ ቢጫ ወባ የሚባለውን እና አንድ ሶስተኛው ደግሞ ቫይቫክስ በተባለ ተህዋስ ዝርያ የሚከሰት ነው፤ ወባዋ የበሽታውን ተህዋስ ከታመመ ሰው አሊያም ታሞ ከዳነ ሰው ትወስዳለች፡፡

ወንድ እና ሴቴ ተህዋስ በወባ ውስጥ አንድ ሳምንት ያድግና ትንኟ ለመራባት የሰው ደም የሚያስፈልጋት በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ሰውን በምትነክስበት ጊዜ በሽታውን ወደ ሌላ ሰው ታስተላልፋለች፡፡

ትንኟ ለመራባት ቆላማ አካባቢ በመምረጥ ከባህር ጠለል በላይ 1ሺህ 400 ሜትር በታች በሆኑ አካባቢዎች ላይ እንደምትገኝና ከዛ በላይ ባለ ከፍታ የመራባት ምጣኔዋ እንደሚቀንስ ይገለፃል፡፡

በሽታው ከዚህ በፊት ለተያዘ ሰው እንዲሁም በተለይ ነብሰ ጡር እና ህፃናት ላይ የመከላከል አቅማቸው አናሳ በመሆኑ የከፋ ጉዳት ያደርሳል፡፡

በአብዛኛው የክረምት ወቅት አልፎ የበጋ ወቅት ሲጀምር ውሀዎች ሙሉ ለሙሉ ስለማይደርቁ እና የታቆሩ ውሀዎች ስለሚኖሩ እንዲሁም በትንንሽም ውሀዎች የመራባት እድል ስለሚኖር ለትንኞች መራባት አመቺ ይሆናል፡፡

የወባ በሽታ ምልክቶች፦

• ትኩሳት • ቁርጥማት  • ማስመለስ  • ማስቀመጥ
• ብርድ ብርድ ማለት  • የከፋ ሲሆን ደግሞ አይን ቢጫ ያደርጋል፡፡

የወባን በሽታን ለመከላከል ትንኟ የምትራባባቸውን ቦታዎች ማጽዳት ያስፈልጋል ያቆሩ የቆሸሹ ነገሮችን ማስወገድም ይገባል፡፡

ጸረ-ትንኝ ኬሚካሎች በሚረጩበት ጊዜ ቀለም መቀባት፣ ማጠብ እንደማይገባ እንዲሁም በጸረ ትንኝ የተነከረ አጎበር መጠቀም እንደሚገባ የህክምና ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
21👍18🔥1
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ ሲንቀሳቀስ የነበረውን ፅንፈኛ መምታት ተችሏል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ ላይ የመንግስትን የሠላም ጥሪ ባልተቀበሉ ፅንፈኛች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የአንድ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል ዋለ አዲስ ተናግረዋል።

ከሰሞኑ በምስራቅ በለሳ ወረዳ ሃሙሲት እና ጣይመን አካባቢ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ፅንፈኛች ላይ በተደረገው ዘመቻ በርካታ የፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ በርካቶች መቁሰላቸውን በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የአንድ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል ዋለ አዲስ ገልፀዋል።

ሻምበል ዋለ አዲስ በተደረገው ዘመቻ RBG የቡድን መሳሪያ ፣ ብሬን ፣ የድሽቃ እና የብሬን ሸንሸሎች እና ሳጥን ፣ ቦንቦች እና ከዝናዎችን መማረክ መቻሉን ገልፀዋል።

የምስራቅ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታዘብ በበኩላቸው በተደጋጋሚ ጦርነትን ለማስቀረት መንግስት የሠላም ጥሪ ቢያቀርብም የሠላም ጥሪውን ያልተቀበሉ ቡድኖች ላይ ሠራዊቱ ተገቢውን እርምጃ ወስዷል ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል እኛም ከሠራዊቱ ጎን ተሠልፈናል ብለዋል። ዘጋቢ ኤፍሬም ቢሸው ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
34👍21👏5🔥1
በሰሜን ሸዋ ዞን መርሀ-ቤቴ ወረዳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ፅንፈኞች ወደ ሠላም ተመልሰዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በሰሜን ሸዋ ዞን መርሀ-ቤቴ ወረዳ በፊጥራ ንዑስ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 67  የፅንፈኛው አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው እጅ መስጠታቸውን የአየር ወለድ ክፍለጦር ዘመቻ ሃላፊ ሌተናል ኮሎኔል መኩሪያ ሙሉነህ ተናገሩ።

ክፍለ ጦሩ በቀጠናው ውጤታማ ግዳጅ ከመፈፀሙ በሻገር በተከታታይ ከዞን አመራር ፣ከወረዳ አመራር   እና ከህብረተሰቡ ጋር ባደረገው ውይይት የተገኘ ስኬት መሆኑን በመግለፅ ጫካ የነበራችሁ የጦርነትን አስከፊነትና ውድመት በመረዳት የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሠላም መምጣታችሁ የሚመሰገን ነው ብለዋል።

የሰሜን ሽዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ኤሊያስ አበበ በበኩላቸው የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበል የስልጡን ማህበረሰብ መገለጫ መሆኑን በመናገር የመሬ ህዝብ ምርጫው ሰላም እና ብልጽግና ልማት እና እድገት እንጂ እንደ ጨለማው ዘመን ወደኋላ መመለስ አይደለም ሲሉ ገልፀዋል።

የመንግስት የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ሃይሎችም በሰላም ዙሪያ ከመንግስት ጋር ሆነው እንደሚሰሩ የገለፁ ሲሆን ተቋርጠው የነበሩ የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመልካም አስተዳደር እና የመሰረተ ልማት ስራዎች  እንዲቀጥሉ ከህዝብ እና ከመንግስት ጎን ሆነው በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ዘጋቢ ታከለ ታለ
ፎቶ ግራፍ ኤፍሬም ታምራት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
44👍16🔥7👏2😁2
የማዕረግ እድገት ለበለጠ ሀላፊነትና ዲሲፕሊን የሚያዘጋጅ ሹመት መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በላቀ የግዳጅ አፈፃፀም ተልዕኳቸውን በመወጣት የመቆያ ጊዜያቸውን ለሸፈኑ የሰራዊት አባላት መዓረግ የማልበስ ስነ ስርዓት የተከናወነ ሲሆን የማዕረግ ዕድገት ለሌላ ከፍተኛ ሀላፊነት እና ወታደራዊ ዲሲፕሊን የሚያዘጋጅ መሆኑን የማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ ገልፀዋል።

ጄኔራል መኮንኑ ለከፍተኛ እና መስመራዊ መኮንኖች ማዕረግ በማልበስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት እለት፤ መዓረግ ለበለጠ ተነሳሽነትና ሀላፊነት መታጨት በመሆኑ ወቅቱ የሚጠይቀውን ወታደራዊ ቁመና መላበስ እንደሚገባ አመላክተዋል።

የማዕረግ ተሿሚ የሰራዊት አባላት ለተሰጣቸው ሀላፊነት ቦታ በመስጠት ከነበራቸው አፈፃፀም ባሻገር ተደማሪ  የተቋም አቅም ለመሆን ዝግጁ መሆን አለባቸው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ በስራቸው ለሚገኙ የሰራዊት አባላት ዓርዓያ በመሆን የተጣለባቸውን ህገ መንግስታዊ ተልዕኮ በብቃት መፈፀምና በሀላፊነት መንፈስ መትጋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። 

የማዕከላዊ ዕዝ የሰው ሀይል ስምሪት እድገት ቡድን መሪ ሻቃ ይርጋለም ዘሪሁን በበኩላቸው ተሿሚዎች የሰራዊቱ መተዳደሪያ ደንብ አዋጅ በሚያዘው መሰረት በነበራቸው የስራ አፈፃፀም ከአቻዎቻቸው በመወዳደር ብልጫ የነበራቸው ሲሆኑ በዕዙ ማሰልጠኛ ማዕከል ገብተው  በስነ ልቦና እና አካል ብቃት እንዲሁም ታክቲካል ስልጠናዎችን በብቃት ሰልጥነው የተሾሙ መሆኑን  አረጋግጠዋል። ዘጋቢ መሀመድ አህመድ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
35👍20🔥2
የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ክፍለጦር በህገወጥ ቡድኑ ላይ እርምጃ ወስዷል።  

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም
                   
የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል ብርሃኑ በላይ እንዳሉት ፅንፈኛው ቡድን የተለመደ የዝርፊያና እገታ ተግባሩን ለማራመድ በደቡብ ወሎ ዞን በከለላ ወረዳ ላይ ሙከራ ቢያደርግም በህገወጥ ቡድኑ ላይ ሠራዊቱ በወሰደው እርምጃ በርካታ የቡድኑ አባላትን ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።
  
ክፍለጦሩ ባደረገው ዘመቻ የህገወጥ በድኑ ላይ እርምጃ በመውሰድና በማቁሰል፣ 06 አባላትን መማረክ ችሏል። በዚህም ብሬን ፣ክላሽ ፣የቃታ መሳሪያ መማረክ የተቻለ ሲሆን ሠራዊቱ በህገ-ወጥ ቡድኑ ላይ የሚያደርገውን ስምሪት አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል። ዘገባው የክፍለጦሩ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
45👍32🔥4👎2