FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.5K subscribers
30.7K photos
35 videos
9 files
8.51K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ቴዎድሮስ ኮር በወርቃማ ቀለም የተፃፈ የዘለዓለማዊ ታሪክ ባለቤት ነው"
    ሌተናል ጄኔራል መሠለ መሠረት

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
 
የምዕራብ ዕዝ ቴዎድሮስ ኮር ሁሌም የተሠጡትን ተልዕኮዎች በአንፀባራቂ ድል የሚፈፅምና በወርቃማ ቀለም የተፃፈ ዘለዓለማዊ ታሪክ ባለቤት መሆኑን የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሠለ መሠረት ገልፀዋል።

አዛዡ በኮሩ 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ቴዎድሮስ ኮር በሠሜኑ ህግ ማስከበር ዘመቻ ከ700 ኪ.ሜ በላይ በእግር ተጉዞ በጠላት ይዞታ ውስጥ በመግባት የጠላትን ቅስም ሠባብሮ ድል መጎናፀፉን አስታውሰዋል።

አሸባሪውን የሸኔ ቡድን የመመንጠር ግዳጅን ተቀብሎ በምዕራብ ኦሮሚያ በመሠማራት በወለጋ አራቱም ዞኖችና በምዕራብ ሸዋ ዞን ግንደ በረትና አቡነ ግንደ በረት ፤ በአዳበርጋ ፤ ሜታ ወልቂጤ እና ሜታ ሮቢ ቀጠናዎች የነበረውን የአሸባሪውን የሸኔ አባላት እና አመራር የደመሠሠ እና የማረከ ፤በርካታ የቡድንና ነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን በእጁ  ያስገባ የአናብስት ስብስብ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሠለ መሠረት የኮሩ አመራርና አባላት ይህንን ተነግሮ የማያልቅ የድል አድራጊነት እና የአሸናፊነት መንፈሳችሁን አቅባችሁ ሀገር እና ህዝብ እንዲሁም ተቋማችንን የሚያኮራ የላቀ ድል በማስመዝገብ ኢትዮጵያን የማፅናት ተልዕኳችሁን በተጨማሪ ገድሎች አጅባችሁ እንደምትወጡ እምነቴ ፅኑ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምሬሳ ፊጤ በበኩላቸው ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ከ2014 እስከ 2016 የካቲት ወር መጀመሪያ ያሉት ግዜያት ለሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሕዝብ መጥፎ ትውስታ እንደነበር አስታውሠው በኦሮማ እና አማራ ህዝቦች ስም በሚነግዱ ፅንፈኛ እና አሸባሪ ቡድኖች ሲደርስበት የነበረውን ግፍ አውስተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በንግግራቸው የምዕራብ ዕዝ ቴዎድሮስ ኮር ወደ ዞኑ ከገባ ከየካቲት 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከአካቢው ህዝብ እና መስተዳድር ጋር  በመቀናጀት የሽብር ቡድኖችን አከርካሪ ሠብሮ ቀጠናው የሠላም አየር እንዲነፍስበት አስችሏል ብለዋል።

አቶ ምሬሳ ፊጤ በመጨረሻም የምዕራብ ዕዝ አመራርና አባላት በተለይም የቴዎድሮስ ኮር ህዝባችንን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሸጋገር ስትሉ ለከፈላችሁልን ሁለንተናዊ መስዋዕትነት በዞኑ ህዝብና መስተዳድር ስም ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፤ ሁሌም ከጎናችሁ በመሆን ለቀሪ ግዳጆች መሳካት የተለመደ ደጀንነታችን ከምንግዜውም በላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

ዘጋቢ ሲሳይ ደመቀ
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
34👍13👎3👏1
በምዕራብ ዕዝ የቴዎድሮስ ኮር የምስረታ በዓል አካባበር በምስል

ፎቶግራፍ ኤርሚያስ ተስፋ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍2315🔥7👏4
መቻል የብሄራዊ ቡድን አጥቂዋን ሴናፍ ዋቁማን አስፈረመ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የተጫዋችነት ዘመኗን በጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ በማድረግ በአዳማ ከተማ ፣ በመቻል እንዲሁም ያለፉትን ሁለት የውድድር አመታት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥሩ ጊዜ ማሳለፍ የቻለችው እና የፕሪምየርሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ያጠናቀቀችው ሴናፍ ዋቁማ በኢንስትራክተር መሠረት ማኔ ለሚመራው መቻል ፊርማዋን አኑራለች።

ለ2018 የውድድር አመት ተቋሙን የሚመጥን ውጤት ለማስመዝገብ ከዋና አሰልጣኝ ጀምሮ ምክትል አሰልጣኝ እንዲሁም የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ እና በሴቶች ፕሪምየርሊግ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች ወደ ቡድኑ መቀላቀል የቻለው የመቻል ሴት እግር ኳስ ቡድን አጥቂዋን ሴናፍ ዋቁማን የግሉ አድርጓል።

መቻል ሴት እግር ኳስ ቡድን በኢንስትራክተር መሠረት ማኔ እየተመራ ለመጀመሪ ጊዜ እየተካሄደ በሚገኘው ጀግኒት ዋንጫ ውድድር ነገ ነሃሴ 20 ቀን 2017 ዓ.ም 5:00 ሰዓት መቻል ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ለዋንጫ ለማለፍ በአበበ ቢቂላ ስታዲዮም ይጫወታሉ። ዘጋቢ ገረመው ጨሬ ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
10👍5