FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.4K subscribers
30.7K photos
34 videos
9 files
8.5K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
በጋዜጠኛ ሌተናል ኮሎኔል ፈይሳ ናኔቻ የተፃፈው የወታደር ውሎ አዳር መፅሀፍ ተመረቀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

የወታደር ውሎ አዳር የተሰኘው መፅሀፍ፣ የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማን ጨምሮ፣ ጄኔራል መኮንኖች ፅሀፊያን እና ደራሲያን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በአደዋ ድል መታሰቢያ ሁለገብ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተመርቋል።

የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ታሪኮች የሀገር ሀብት በመሆናቸው፣ሰንዶ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ጠቁመው የጋዜጠኛው መፅሃፍም የመከላከያ ሠራዊቱን ሁለንተናዊ የግዳጅ ውሎ አስገራሚ የኋላ ታሪኮች የሚያትት በመሆኑ አመሥግነውታል።

በመከላከያ ስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት የሚዲያ ስራዎች ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል አስፋው ማመጫ፣ ለምርቃት የበቃውን መፅሀፉ ዳሰሳ በማድረግ የሰራዊቱን ህይወት በሚገባ የሚገልፅ እና የሚያሳይ መሆኑን አመላክተው በመፅሀፉ ውትድርና እና ኢትዮጵያዊነት ያላቸውን ግንኙነት፣ በግልፅ፣ማሳየት እንደተቻለም አብራርተዋል።

በመፅሀፉት ምርቃቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር  ፕሬዚዳንት፣ ደራሲ አበረ አዳሙ፣በመፅሀፉ ላይ የመመዘኛ ዳሰሳ አድርገዋል። በዚህም መፅሀፉ የመፅሀፍ መመዘኛ መስፈርትን በጥሩ ሁኔታ ማሟላቱን ገልፀው ወታደራዊ ታሪኮች ሀገርን በሚመጥን መልኩ ተሰንደው እና በመፅሃፍ ተዘጋጅተው ለትውልድ መተላለፍ እንዳለባቸው አመላክተዋል። ለሀገር መስዋዕት እየከፈለ ሠላምን እያረጋገጠ  ለሚገኘው የመከላከያ ሠራዊትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ዘጋቢ ቢያድግልኝ መሪ
ፎቶ ግራፍ አበረ አየነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
24👍18👏6🔥2🥰1🏆1