FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
39.5K subscribers
30.8K photos
36 videos
9 files
8.52K links
# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Download Telegram
ተቋሙን የሚመጥን ሎጀስቲክሳዊ ስራ ከምንጊዜውም በላይ እየተሠራ ነው፡፡
ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምን ለአራት ቀናት ተመልክቷል።

የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ  ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል የዘንድሮው የእቅድ አፈፃፀም ውይይት ከወትሮው ለየት የሚያደርገው ሀገራችን ባከናወነቻቸው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ተግባራት በዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ መድረኮች ያላት ተቀባይነት እና ተደማጭነቷ እያደገ በመምጣቷ በተቋማችንም በወታደራዊ ዘርፉ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የሚደረጉ የወታደራዊ ጉዳዮች ትብብር እያደገ ሀገራት ከእኛ ጋር በትብብር ለመስራት የተነሱበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

በዋና መምሪያው ስር የሚገኙ የመምሪያ እና የክፍል ሃላፊዎች በተሰጣቸው ተልዕኮ እና በእቅዱ መሰረት አፈፃፀማቸውን በማስመልከት ባቀረቧቸው ሪፖርቶች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተቀመጠው በበጀት ዓመቱ ዋና መምሪያው የሠራዊቱን ሁለንተናዊ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት የተመዘገበበት ሰፊ ስራ ተሠርቷል።
 
የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል በመርሐ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ አፈፃፀማችን የተቋማችንን ፈጣን ለዉጥ ታሳቢ በማድረግ፣ ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጡ ትጥቆች በውስጥ አቅም በማዘጋጀት ወጪን በመቀነስ፣ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና ወጤታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ዝግጁነታችንን ያረጋገጥንበት የአፈፃፀም ብቃት ከፍ ብሎ የታየበትና አዳዲስ የስራ ባህል የተላመድንበት አመት ነው ብለዋል።

የሰራዊቱን የዕለት ተዕለት ቀለብ፤ አልባሳት፣ ትጥቅ እንዲሁም ሞብሊቲን በማረጋገጥ የውጊያ ድጋፍ አገልግሎት አሰጣጡን እያሳለጠ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በልማቱ ዘርፍም በተቋማችን እንዲተገበሩ የታቀዱ የልማት ስራዎች ውስጥ የማዕከሎች የግንባታ ስራ በማጠናቀቅ እና በማልማት አመራሩና ሙያተኛው የተሰጡትን ተልዕኮዎች በአግባቡ አሳክቶ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያደርስ፤ የሥራ ተነሳሽነቱ ይበልጥ እንዲጨምር መደረጉንም አንስተዋል።

በአዳዲስ ሀሳቦች ችግር ፈቺ ወጪ ቆጣቢ አሰራሮች ላይ አተኩሮ እንዲሰራ ማዕከላቱን ውብ፣ ፅዱ እና ለስራ የተመቹ የማድረግ ስራ መሠራቱን ገልፀዋል።

ሌተናል ጄኔራል አብዱራህማን ኢስማኤል በተቋማችን የተጀመረውን የሪፎርም ትግበራ የሚያሳኩ፣ የአመራሩንና የሙያተኛውን የመፈፀም አቅም የሚያሳድጉ የሰነ-ልቦና ግንባታዎች፣ ስልጠናዎች በተከታታይ በመከናወናቸው አሁን ላይ በሙያዊ ስነ-ምግባር የታነፀ ወታደራዊ ባህል እና ጨዋነትን ያከበረ የተቋቋመበትን ተልእኮ እና የሚሰጠውን ግዳጅ ታሳቢ ያደረገ አባላት መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

በሰላምም ሆነ በውጊያ የሚኖር ተልዕኮን በማገናዘብ፣ ሃብትን በአግባቡ የሚያስተዳድር፣ ቀልጣፋ፣ የማይቋረጥ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍ በተፈለገው ጊዜና ቦታ በፍጥነትና በጥራት መስራት የሚያስችል የሎጀስቲክስ አቅም የተፈጠረ መሆኑ በውይይቱ ተገልፃል፡፡ ዘገባው የወርቅነህ ተስፋው ነው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
34👍3
የመከላከያ ሚኒስቴር ተጠሪ ክፍሎች በበጀት ዓመቱ የእቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢንጅነር አይሻ መሀመድ የውይይቱ ዋና ዓላማ የእቅድ አፈፃፀማችንን የጋራ ለማድረግ፣ ጠንከራ ጎኖቻችንን ይዘን ለመዝለቅ እና ክፍተቶች ካሉ የበለጠ በማሻሻል ተግባራቶቻችን ሁሉ የተቋማችን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ ፋይዳ ያላቸው እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡

ሁሉም ተጠሪ ክፍሎች በተመደበላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የስራ አፈፃፀማቸውን እንደሚያቀርቡ እና በቀረቡት ላይ ውይይት ተደርጎ በመጨረሻም በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ገለፃ እንደሚደረግ የሚኒስቴሩ እቅድ እና ሪፖርት ዝግጅት ክትትል ዳይሬክተር ኮሎኔል ፈይሳ ታደሰ ገልፀዋል፡፡

የመከላከያ ፋይናንስ ሥራ አመራር ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ማርታ ሉዊጅ የተቋሙን የሰው ሃይል፣ የውስጥ ገቢ፣ የግብዓት፣ የአግልግሎት አሰጣጥ እና የኢንስፔክሽን ስራዎች አቅምን ለማሳደግ መልካም ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡ በተለይም ደግሞ የፋይናንስ ስርዓት፣ የግዥ አፈፃፀም፣ የንብረት አያያዝ ስርዓት በመመሪያ እና በአሰራር ተግባራዊ እንዲሆኑ በማድረግ በኩል አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

የፋይናንስ ስርዓቱን በቴክኖሎጅ ማዘመን፣ የሴቶችን አቅም በማሳደግ እና ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ፣ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የሰራዊት አባላት እና የማህበረስብ ክፍሎች የበጎ አድራጎት ተግባራትን መከወን፣ የተመደበውን በጀት በአግባቡ ስራ ላይ ማዋል የበጀት ዓመቱ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫ ሆነው ሲተገበሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ ብርሃን እንዳየሁ
ፎቶግራፍ ድምሩ ህሩይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍2619
በተሳሳተ ፕሮፖጋንዳ ተታለው ጫካ የገቡ 100 የፅንፈኛው አባላት እጅ ሰጡ። 

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

በሰሜን ሽዋ ዞን ሚዳ ወረዳ  ህብረተሰቡን ሲያሸብሩ የነበሩ 01 ሴትን ጨምሮ 100 አመራርና ተዋጊ እጅ መስጠታቸውን የአየር ወለድ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ኢብራሂም ሀጅ ተናግረዋል።

ሻለቃ ኢብራሂም ሀጅ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛ ቡድን አማራን ነፃ እናወጣለን በሚል ፕሮፖጋንዳ ተታልለው ወደ ጫካ ከገቡ በኋላ የፅንፈኛው ሀይል የውሸት ፕሮፖጋንዳ ሲገባቸው እና የሠራዊቱ የህዝብ ወገንተኝነትና ተከታታይ የህዝብ መድረክ በመሰራቱ መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ በመቀበል እጃቸውን ለሠራዊቱ ሰጥተዋል ብለዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰይድ ኢብራሂም  በበኩላቸው የሰላም እጦቱ በወረዳው ተፈጥሮ መቆየቱን ገልፀው ከቅርብ ጊዚ ወዲህ የህዝብ በደል እና እንግልት እንዲሁም የፅንፈኛውን ቡድን የውሸት ፕሮፖጋንዳ ተረድተው ወደ ሰላም በመመለሳቸው አመሥግነዋል።

በቀጣይም ከጥምር ጦሩ ጋር በመሆን ወረዳውን አልፎም ዞኑን ወደ ቀደመ ሰላሙ እንመልሳለን ሲሉ ተናግረዋል።

በሰላም የገቡት የፅንፈኛው አባላትም ጫካ ያለው ሀይል ለህዝብ የቆመ ሳይሆን የውጪ ተላላኪና ለዘረፋ የቆመ ሀይል መሆኑን በመረዳት እጅ መሥጠት መቻላቸውን ተናግረው የምናውቃቸው በፅንፈኛው የተታለሉት በሰላም እጃቸውን እንዲሰጡ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።

ዘጋቢ ታከለ ታለ
ፎቶ ግራፍ መኮንን አባይ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
👍3731😁2🔥1🏆1
የ6ኛ ዕዝ ማሠልጠኛ በየደረጃው ያለ አመራርን እያበቃ መሆኑ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ማረጋገጥ እና ጦርነትን ማስቀረት የሚቻለው የሠራዊቱን የጀግንነት ቁመና ማረጋገጥ ሲቻል በመሆኑ ስልጠና የማያቋርጥ የሠራዊቱ የዕለት ተዕለት ተግባር መሆኑን የ6ኛ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሸናል ሜጄር ጄኔራል ነገሪ ቶሊና ገልፀዋል።

ጄኔራል መኮንኑ በ6ኛ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ተገኝተው ሰልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙ ሰልታዊ አመራሮች ተሞክሯቸውን አካፍለዋል።

የጦርነት አውድ መረዳት የሚችል ሠራዊት መገንባት ለነገ የማንለው ጉዳይ በመሆኑ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ በክህሎት ልቀን መገኘት ሁሌም በስልጠና ማዳበር ነው ያሉት ሜጄር ጄኔራል ነገሪ ቶሊና ሠራዊት ተለዋዋጭ የውጊያ ዘዴዎችን ተረድቶ የስልጠና አቅሞችን በመጠቀም ተልዕኮውን በብቃት እየፈፀመ መሆኑን ተናግረዋል።

በክህሎት ደረጃ ከፍተኛ ሙያዊ ልህቀት ያለው በዘመናዊ የጦርነት ሰልቶች የበቃ ሰትራቴጅካዊ አስተሳሰብ የታጠቀ ሁሌም ራሱን በማሻሻልና በማብቃት የተዘጋጀ ተዋግቶ ሌሎችን ማዋጋት የሚችል አመራር ለመፍጠር ስልጠና ከፍተኛ አቅም መሆኑን አብራርተዋል።

ማሰልጠኛ ማዕከሉ የሠራዊቱ ታክቲካልና ሰነ-ልቦናዊ ዝግጁነት የሚጎለብትባቸው አቅሞች በመሆናቸው ተደማሪ የእውቀት ማዕከላት ናቸው ያሉት ምክትል አዛዡ ሠራዊቱ በአግባቡ ሊገለገልባቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ዘጋቢ አዲሱ አራጋው
ፎቶግራፍ ሌሊሴ አራርሜ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
41👍5🏆4
በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ የልማት ስራዎች እንዲስፋፉ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ16 ቀን 2017 ዓ.ም

በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ የተሻለ ሰላምና መረጋጋት በመኖሩ ያለስጋት የልማት ስራዎች እንዲሰሩ የሴክተር 3 የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሴክተር 3 ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ተክሉ ሁሪሳ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ አባላት የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ የፀጥታ አካላትን በመደገፍና በጋራ በመጣመር የክልሉ የስራ ሃላፊዎችና ህብረተሰቡ ከቦታ ወደ ቦታ ተንቀሳቅሶ ያለስጋት የሰላምና የልማት ስራዎችን እንዲሰሩ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ብርጋዲየር ጀኔራል ተክሉ ሁሪሳ በከተማ ይሁን በገጠር አካባቢዎች የተጀመሩትን የልማት ስራዎች አልሸባብ በማደናቀፍ ትንኮሳ እንዳያደርግና የአካባቢውን ሰላም እንዳያውክ የሰላም አስከባሪ አባላቱ ቀድሞ አካባቢውን ቅኝት የማድረግና የእጀባ ስራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ደንብና መመሪያን በማክበር የሰላም አስከባሪ አባላቱ በጨዋነት ግዳጁን እየፈፀመ ይገኛል ያሉት የሴክተሩ አዛዥ ሠራዊቱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ ንቁ ሆኖ ባህልና ጨዋነቱን ጠብቆ የቀጣዩን ተልዕኮ መፈፀም እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል፡፡  

ዘጋቢ ሰመረ እሸቱ
ፎቶግራፍ አይናለም ተክለፃዲቅ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
44👏11🏆3👍2