Fana Media Corporation S.C (FMC)
205K subscribers
71.2K photos
1.45K videos
23 files
59.2K links
This is FMC's official Telegram channel.

For more updates please visit
https://fanamc.com
Download Telegram
የዕለቱ የምንዛሪ ዋጋ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ወርቅውሃ ጌታቸው በመላ አፍሪካ ጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል 2ኛ ወርቅ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ)በናይጄሪያ አቡጃ እየተካሄደ በሚገኘው 2ኛው የመላ አፍሪካ ጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል በ3 ሺህ ሜትር መሠናክል ሃምሳ አለቃ ወርቅውሃ ጌታቸው የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።

በዚህም አትሌቷ ለመከላከያው መቻል ስድስተኛ፤ ለራሷ ደግሞ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገብ ችላለች።

ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የ3 ሺህ መሠናክል ውድድር የመቻሏ አስር አለቃ ባአለምላይ ሹመት 2ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቅቃለች።

ኢትዮጵያን በመወከል በስፖርት ፌስቲቫሉ እየተካፈለ የሚገኘው የመከላከያው መቻል ስፖርት ክለብ በውድድሩ 6 ወርቅ፣7 ብር እና 2 ነሐስ በአጠቃላይ 15 ሜዳሊያዎችን በመያዝ ውድድሩን መቀጠሉን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል።
ባለፉት 2 ሳምንታት ከደረሱት ሰብሎች 53 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከደረሱት ሰብሎች 53 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቦ ወደ ጎተራ መግባቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ኢሳያስ ለማ እንዳሉት÷ በዘንድሮ የመኸር ወቅት 607 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፡፡ የታቀደውን ግብ ለማሳካትም የድህረ ምርት ብክነትን መቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎችን…

https://www.fanabc.com/archives/273075
ማስታወቂያ

#InfinixEthiopia

ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ይግዙ ኩፖን ይወስዱ፡፡ ባሻዎት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ ያጋሩ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት እንዲሁም በርካታ የኢንፊኒክስ ምርቶችን ያሸንፉ ይሸለሙ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
የብልጽግና ፓርቲ የፎቶ አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዝዬም ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የፎቶ አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዝዬም ተከፍቷል፡፡ በሥነ-ስርዓቱ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የፌደሬሽን ምክርቤት አፈጉባዔ አገኘው ተሻገር እና…

https://www.fanabc.com/archives/273078
አገልግሎቱ የኦዲት ግኝቶችን በማስተካከልና አሰራሩን በማሻሻል ሪፖርት እንዲያቀርብ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የፋይናንስና ሌሎች የአሠራር ጉድለቶቹን እንዲያርምና የሕዝብ ቅሬታና እሮሮ የሚቀርብባቸው አሠራሮቹን እንዲያሻሽል ተጠየቀ፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2015/16 ኦዲት ዓመት በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ2015 በጀት ዓመት የፋይናንስና ሌሎች አሠራሮች ላይ የሂሳብ እና የክዋኔ ኦዲት አድርጓል፡፡ ይህን ተከትሎም በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሁለት ክፍለ ጊዜ ተከፍሎ…

https://www.fanabc.com/archives/273081
ማስታወቂያ


📍ፒያሳ ላይ ሱቅ መሸጥ ጀምረናል
📍ከ900 ሺ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ በተለያዩ የካሬ አማራጮች እንደምርጫዎ የቀረበ
📍ከሚኒሊክ አደባባይ ፊት ለፊት ባለ 5 ወለል ዘመናዊ የንግድ ሱቅ ማዕከል ከቴምር ፕሮፐርቲስ
📍20 ካሬ ድረስ የሚሆኑ
📍2 ቤዝመንት ያለው G+5 ሁሉም
📍ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ
📍ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ከ 📍3,900,000 - 10,000,000 ብርሙሉ ክፍያ አማራጭ አሉ።
📍1st floor 5,500,000 =100% total price 2,000,000 advance ( ቅድመ ክፍያ)
📍Ground floor 7,000,000=100% total price 2,800,000 advance ( ቅድመ ክፍያ)
📍2nd floor 4,800,000 =100% total price 1,500,000 advance ( ቅድመ ክፍያ)
📍3rd floor 4,200,000 =100% total price 1,200,000 advance ( ቅድመ ክፍያ)
📍4th&5th floor 3,900,000 =100% total price 900,000 advance ( ቅድመ ክፍያ)
ለበለጠ መረጃ
☎️ 0932084420 / 0966903656
የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በባሕርዳር ከተማ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ላይ በባሕርዳር የገቡ ከፍተኛ አመራሮች የከተማዋን የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው። በጉብኝቱ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፣ የብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባሕል ግንባታ…

https://www.fanabc.com/archives/273093
ኢትዮጵያና ጣልያን በሴቶችና ሕጻናት ላይ በትብብር ለመስራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በጣልያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ዴዔታ ጆርጂዮ ሲሊ ከተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል። ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ጣልያንና ኢትዮጵያ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ግንኙነት እንዳላቸው ገልፀው ÷ጣልያን የኢትዮጵያ ቁልፍ አጋርና በልማት ትብብርና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ የምታደርገውን ጠንካራ ተሳትፎ አድንቀዋል።…

https://www.fanabc.com/archives/273096
የአቴከር ሕዝቦች የባህል ፌስቲቫል በኡጋንዳ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በባህል የሚያስተሳስረው የአቴከር ሕዝቦች የባህል ፌስቲቫል በኡጋንዳ በድምቀት ተከፍቷል። “የጋራ ቅርሶችን በማክበር፣ ወደ ሰላም፣ ብልጽግና እና የባህል ህዳሴ ጎዳና ማምራት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው ፌስቲቫል መክፈቻ ላይ የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጀሲካ አሉፖ ታድመዋል። በፌስቲቫሉ ኢትጵያን በመወክል የአቴከር…

https://www.fanabc.com/archives/273103
የህብረቱን ከቀረጥ ነጻ የገበያ እድል በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የሰጠውን ከቀረጥ ነፃ የገበያ እድል በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል ውይይት ተካሂዷል፡፡ መድረኩ በአውሮፓ ህብረት የአካባቢን ዘላቂ ጠቀሜታ እውን ለማድረግ እየተተገበሩ ያሉ የሕግ ማዕቀፎች ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ አልባሳት በሚያመርቱ ኩባንያዎች ላይ የሚሳድረው ተጽዕኖ ላይ ያተኮረ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ የአውሮፓ ህብረት የአካባቢን ዘላቂ ጠቀሜታ እውን ለማድረግ…

https://www.fanabc.com/archives/273105
የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የአሜሪካ ዶላር ግዢ እንዲቋረጥ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የአሜሪካ ዶላር ግዢ ከዛሬ ጀምሮ ማቆሙን አስታወቀ፡፡ የሩሲያ ባንክ እንዳስታወቀው፥ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በሀገር ውስጥ ምንዛሪ ላይ የሚደረጉ የውጭ ምንዛሪ ግዢዎችን የገበያውን ተለዋዋጭነት ለመቀነስ የዶላር ግዢው ተቋርጧል። ባንኩ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የሩሲያ ምንዛሪ የመግዛት አቅም መዳከሙን ተከትሎ እንደሆነ…

https://www.fanabc.com/archives/273070
ማስታወቂያ

ህፃናት ደስተኛ ሆነው ማደጋቸው ለወደፊት ህይወታቸው ብሩህ መሠረት ነው።
ለህፃናት የምናደርገውን ክብካቤ ይደግፉ!
በዚህ በጎ ተግባር ለመሳተፍ ይሄን ሊንክ ይጫኑ
https://bit.ly/3wkasIq
ለበለጠ መረጃ በ +251907222333 ይደውሉ
ከመንደር አጀንዳ ተላቅቀን በዓለም መድረክ የሚገባንን የመሪነት ሚና መጫወት አለብን – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከመንደር አጀንዳ ተላቅቀን በዓለም መድረክ የሚገባንን የመሪነት ሚና መጫወት አለብን ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። “የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሀሳብ የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የፎቶ አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዝዬም ተከፍቷል፡፡ አውደ ርዕዩን ምክትል ጠቅላይ…

https://www.fanabc.com/archives/273114
ሩሲያ በዩክሬን የሃይል መሰረተ ልማት ላይ ከባድ ጥቃት መፈጸሟ ተነገረ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በዩክሬን የሃይል መሰረተ ልማት ላይ ከባድ ፍንዳታዎች የተሰሙበት ጥቃት መፈጸሟን የሀገሪቱ ኢነርጂ ሚኒስትር ኽርማን ሃሉሼንኮ አስታውቀዋል፡፡ ከጥቃቱ ቀደም ብሎ የዩክሬን አየር ሃይል በመላው ሀገሪቱ የሚሳኤል ስጋት እንዳለ ማስጠንቀቂያ መስጠቱም ነው የተገለጸው፡፡ የቢቢሲ ዘገባ እንደሚለው፤ ሩሲያ በተደጋጋሚ የዩክሬን የኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጥቃት ፈጽማለች፡፡ በህዳር ወር…

https://www.fanabc.com/archives/273118