Exit Exam Preparation
38.3K subscribers
81 photos
1 video
8 files
17 links
Exit Exam በከፍተኛ ውጤት ለማለፍ የሚረዳ ፣ ከዚ በፊት የነበሩ የExit Exam ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያቸው የያዘ Quiz Bot


@Exit_Exam_preparationbot
Download Telegram
ባለፈው ወር የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 48,692 (23.8 በመቶ) የሚሆኑት ተፈታኞች ብቻ ፈተናውን ማለፋቸው ተሰምቷል።

ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 236,460 ተማሪዎች ውስጥ 204,028 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።

32,000 በላይ ተማሪዎች ተመዝግበው 'በግል ምክንያት' ሳይፈተኑ መቅረታቸውን አንድ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትን ጠቅሶ መረጃ አጋርቷል።

በአጠቃላይ 342 ተቋማት ማለትም 70 የመንግሥት እና 272 የግል ተቋማት በፈተና አሰጣጡ ላይ መሳተፋቸው ተገልጿል።

የመውጫ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች 48,692 ተፈታኞች ብቻ ያለፉ ሲሆን፤ በቅሬታ ሂደት ላይ ያሉ ውጤቶች አሐዙን ሊያሳድጉት ይችላሉ ተብሏል።


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
52😢13🥰2👏1
#coc

የብቃት ምዘና ፈተና በተመለከት አጠቃላይ ማብራሪያ

የ coc ፈተና ከ 2019 Gc ጀምሮ በጤና ሚንስትር ለጤና ዘርፍ ተመራቂ ተማሪዎች የሚሰጥ ፈተና ነው ። በ 13 የጤና ዘርፎች የሚሰጠው ፈተናው ከ2015ዓ.ም ጀምሮ ደሞ የመውጫ ፈተና ያለፉ ተማሪዎች ብቻ እንዲወስዱት ተደርጓል ። ፈተናው በከፍተኛ ትምህርት መምህራን ሚዘጋጅ ሲሆን ሁሉም ጥያቄዎች scenario based ናቸው ፈተናው ለ የ department በተመረጡ standard text book እና updated guide lines ላይ ተመስርቶ ነው ሚዘጋጀው ከመውጫ ፈተና ያለው ልዩነት ተማሪው understand ማድረጉን ላይ ሳይሆን knows how ወይ ደሞ evaluate አድርጎ ለታካሚ ሚወስደውን decision ላይ በብዛት ማተኮሩ ነው።

ፈተናውን ለመፈተን ቴምፖ ግዴታ ነው!

ምዝገባው በዚህ ወር ጀምሮ እስከ ቀጣይ ወር መጀመሪያ እንደሚቀጥል ሲጠበቅ ፈተናው በሚያዚያ ወር መጨረሻ አሊያ ደሞ በግንቦት መጀመሪያ ይሰጣል ።


ፈተናውን እንድታልፉ ሚረዳቹ ከዚ በፊት የነበሩ ጥያቄዎችን ከነ መልስና ማብራሪያው ተዘጋጅቶላቹሀል ይሄን በመንካት እራሳችሁን ለፈተናው አዘጋጁ
👉@Exit_Exam_preparationbot



ያለፉ ተማሪዎች ሊስት ወደ ከተማ መስተዳድር ስማቸው ተልኮ license ከዛው ሚወስዱ ይሆናል።



የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
111👍21🔥5😁4🤔4👏1💔1🖕1
#exit_exam

ለቅሬታ የሚሰጡ ምላሾች ዛሬ ነው ሚጠናቀቁት።
ከ15 ሺህ በላይ ቅሬታዎች ገብተው የተወሰኑት በአግባቡ ተስተካክለዋል። አቶ ተፈሪ(eaes)

የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
61👍22😢19😁6🕊6
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 907 ተማሪዎች አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው 17ኛ ዙር ተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሕክምና ዶክትሬት እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
23
#AdigratUniversity

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 167 ተማሪዎች አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 16ቱ የሕክምና ዶክተሮች መሆናቸው ተገልጿል።

የተቋሙ 12ኛ ዙር ተመራቂዎች 121 በመጀመሪያ ዲግሪ እና 46 በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ  ናቸው።


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
24
#WolaitaSodoUniversity

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 352 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን ከ2,300 በላይ ተማሪዎች ትናንት ማስመረቁ ይታወቃል።

የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
36👍2🥰2
በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተሰማሩ 52 የግል ኮሌጆች ታገዱ

የኢ. ፌ. ዲ. ሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የተሰጠውን ስልጣንና ተግባር መሰረት በማድረግ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ባደረገው የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች 52 የግል ኮሌጆች ከዘርፉ እንዲወጡ ማድረሱን አስታወቀ፡፡

ተቋማቱ  በዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታቸው ምክንያት ከከፍተኛ ትምህርት ሴክተር እንዲወጡ የታዘዙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት  ዝርዝር አሳውቋል፡፡

ባለስልጣኑ እንዳታወቀው ተቋማቱ  አራት ጊዜ በደብዳቤ፣ አንድ ጊዜ በስልክ እንዲሁም  አንድ ጊዜ በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ በስልክ ጥሪ በተደጋጋሚ ጥሪ ባለማክበራቸው ህጋዊነታቸው ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም ተቋማቱ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንድያደርጉ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ተግባራዊ ባለማድረጋቸው ህጋዊነታቸው የተቋረጠ ሰለሆነ  በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተሰማርተው ዜጎች ላይ  ጉዳት እንዳያደርሱ የከፍተኛ ትምህርት አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ እና አስፈላው የህግ እንደሚወሰድባቸው መገለፁን ብስራት ሬዲዮ ከኢ. ፌ. ዲ. ሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የደረሰው መረጃ ያመላክታል፡፡

የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
83👍8😁7🔥5🤨2
በጦርነቱ ምክንያት በደረሰ የ server ችግር ምክንያት ያዘጋጀንላቹ የ exam መዘጋጃ የቴሌግራም ቦት እሁን ላይ እየሰራ ስላልሆነ በሌላ አማራጮች ችግሩን እስክንቀርፍ ትንሽ ይታገሱን።
😁84🙏3736🤔8🥰5
#EAES

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና የሚዘጋጅባቸው የትምህርት አይነቶች እና የክፍል ደረጃዎች ይፋ ሆነዋል።

ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፦

በተፈጥሮ ሳይንስ
እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ እና ፊዝክስ

በማኅበራዊ ሳይንስ
እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ እና ኢኮኖሚክስ

የመልቀቂያ ፈተናው በየትምህርት አይነቱ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል።

የዝግጅት አግባቡ 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞው እና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት (Common Contents) ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን፤ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል ተብሏል።

የኢኮኖሚክስ የትምህርት አይነት ግን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን እንደሚሆን አገልግሎቱ ጠቁሟል።


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉 @Exit_Exam_prep
52👏5
#ExitExam

ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ዲግሪ ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና በሰኔ ወር ለመስጠት አቅዷል፡፡

በሚኒስቴሩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ በሆኑት እዮብ አየነው (ዶ/ር) በተፈረመና በቀን 24/07/18 ዓ.ም ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተላከ ሰርኩላር፤ ተቋማቱ በ2018 ዓ.ም ሰኔ ወር ላይ የመውጫ ፈተና የሚሰጥባቸውን ፕሮግራሞች እና እጩ ተመራቂዎች እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚሰጥባቸውን ፕሮግራሞች በመለየት ከላይ በተየያዘው ቅጽ መሰረት እስከ ሚያዚያ 02/2018 ዓ.ም ድረስ በኢሜል አድራሻ manayesh997@gmail.com እንዲልኩ ሚኒስቴሩ ጠይቋል፡፡


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
108👍20🥰5😁3👏1
#RemedialExam

የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የሚሰጠው የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ደግሞ በግንቦት ወር አጋማሽ እንደሚሆን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተናን አስመልክቶ ያጋራው መርሐግብር ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥ ጠቁሟል (ምስሉ ከላይ ተያይዟል)፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ በይፋ ያወጣው መረጃ የለም፡፡

የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በትምህርት ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።


የ University  መረጃ የምትገኙበት 
👉
@Exit_Exam_prep
51👍3🔥2