ewca_eth
146 subscribers
1.75K photos
41 videos
2 files
59 links
Develop and conserve scientifically Ethiopia's Wildlife resources and protected areas through active participation.
Download Telegram
የተሻሻለውን የባለስልጣኑ የህግ ማዕቀፍ እንዲፀድቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የንግድና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አሻ ያህያ ገለፁ ፡

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ለባለድርሻና አጋር አካላት ባዘጋጀው የ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀምና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ የውይይት መድረክ በትናንትናው ዕለት በአዳማ ከተማ አካሒዷል።

በውይይቱም የባለስልጣኑ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሠለች ተስፋዬ የባለስልጣኑን የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አቅርበዋል። በተጨማሪም የባለስልጣኑ አጋር አካላት በበኩላቸው ዓመታዊ ሪፖርታቸውን አቅርበዋል። የቀረበውን ሪፖርትና ዕቅድ መነሻ በማድረግ ሠፊ ውይይት ተካሒዷል።

በውይይቱም የመረሃ ግብሩ ተሣታፊዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በጥበቃ ቦታዎች ላይ የሚስተዋሉ ህገወጥ ተግባራት በቁርጠኝነት ከመከላከል አንፃር ፣ ሳይሻሻል ዓመታትን የተሻገራውን የህግ ማዕቀፍ እንዲላቅና ተግባራዊ እንዲሆን ከማድረግ አንፃር ፣ ዘርፉን የተመለከቱ የጥናት ዉጤቶች ተግባራዊ ማድረግን በተመለከተ ፣ እጨመረ የመጣውን የ ሠው የዱር እንስሳት ግጭት ከመከላከል አኳያ ፣ ለሬንጀሮች የህይወት መድህን ዋስት እንዲኖራቸው ከማድረግ አንፃር ፣ ህግ የማስከበር ስራው ትኩረት ከመስጠት አኳያ እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ኮነስተው የጋራ ውይይት ተደርጓል።

በዕለቱ ውይይቱን የመሩት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሠብሳቢ ወ/ሮ አሻ ያህያ ከተሳታፊዎች .የተነሡ ጉዳዮች መነሻ በማድረግ የብሔራዊ ፓርኮች ጉዳይ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ብቻ እንዳልሆነና የሁሉንም አካላት ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው ከኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ በጥበቃ ቦታዎች ላይ እየደረሱ ያሉ ጫናዎችን ለመከላከል እና የተሻሻለው የህግ ማዕቀፍ እንዲፀድቅ ቋሚ ኮሚቴውን ድጋፋን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በበኩላቸው የብሔራዊ ፓርኮችን እና የዱር እንስሳትን ህልውና ለመጠበቅ ተቋሙ ከአጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እየሠራ መሆኑን አንስተው በቀጣይ ተሻሽሎ ለሚመለከተው አካል የቀረበው የህግ ማዕቀፍ ቢፀድቅ በርካታ ችግሮችን እንደሚቀረፋ ገልጸዋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የባለስልጣኑ አጋርና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ አሁናዊ ገፅታ
ጳጉሜ 4/2016 ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን
ለመላው ኢትዮጵያውያን መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ ዘንድ
በልካም ምኞቱን ይገልፃል!
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ
በዓሉ የሰላም፣ የደስታ እና የአብሮነት ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን እየገለፀ
የዱር እንስሳት መጠለያ የሆኑት ብሔራዊ ፖርኮቻችን ላይ
የሚፈጸሙ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በጋራ እንከላከል በማለት ጥሪውን ያስተላልፋል።
የዱር እንስሳት ሀብታችንን በጋራ እንጠብቅ!
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆን ይመኛል፡፡

ኢድ-ሙባረክ

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን
የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት (TSA) ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃግብር በአድዋ ሙዚየም እየተካሄደ ነው።
ኢዱጥባ
መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም
*****
በቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ አስተዋፅዖ ላይ አጠቃላይ መረጃዎችን ለማቅረብ እንዲያስችል ተደርጎ የተዘጋጀው የቱሪዝም የሳተላይት አካውንት ማስጀመሪያ ስነሰርዓት በአድዋ ሙዚየም በመካሔድ ላይ ነው።