ለቦይንግ 737 አውሮፕላን ሰለባዎች የሙት አመት መታሰቢያ ተደረገ
************************
(ኢ.ፕ.ድ)
መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ET302 ማክስ 8 አውሮፕላን የተከሰከበት ቦታ ላይ ዛሬ የሙት አመት መታሰቢያ ስነስርአት እየተከናወነ ይገኛል።
ስነስርአቱ የተዘጋጀው በአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆን በሚልኪ የማስታወቂያ ስራዎች አስተባባሪነት የሚከናወን መሆኑን የሚልኪ አድቨርታይዚንግ ስራ አስኪያጅ አቶ ቀልቤሳ መገርሳ ተናግረዋል።
በስነስርአቱ ለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ጸሎት ያደረጉ ሲሆን የአካባቢው ፈረሰኞች ዛሬ ለአመት የዘለቀው ሀዘን የሚያበቃበት ቀን መሆኑን ለማሣወቅ ጥቁርና ነጭ ሰንደቅ አላማዎየችን በመያዘ ተገኝተዋል። አባ ገዳዎችም ምስጋና አቅረበዋል።
በአውሮፕላኑ ተሣፍረው የነበሩ የ33 አገር ዜጎች በሙሉ ህይወታቸው ማለፉና ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጆ እንደ ነበር ይታወሳል።
ዘገባ እና ፎቶ በራስወርቅ ሙሉጌታ
************************
(ኢ.ፕ.ድ)
መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ET302 ማክስ 8 አውሮፕላን የተከሰከበት ቦታ ላይ ዛሬ የሙት አመት መታሰቢያ ስነስርአት እየተከናወነ ይገኛል።
ስነስርአቱ የተዘጋጀው በአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆን በሚልኪ የማስታወቂያ ስራዎች አስተባባሪነት የሚከናወን መሆኑን የሚልኪ አድቨርታይዚንግ ስራ አስኪያጅ አቶ ቀልቤሳ መገርሳ ተናግረዋል።
በስነስርአቱ ለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ጸሎት ያደረጉ ሲሆን የአካባቢው ፈረሰኞች ዛሬ ለአመት የዘለቀው ሀዘን የሚያበቃበት ቀን መሆኑን ለማሣወቅ ጥቁርና ነጭ ሰንደቅ አላማዎየችን በመያዘ ተገኝተዋል። አባ ገዳዎችም ምስጋና አቅረበዋል።
በአውሮፕላኑ ተሣፍረው የነበሩ የ33 አገር ዜጎች በሙሉ ህይወታቸው ማለፉና ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጆ እንደ ነበር ይታወሳል።
ዘገባ እና ፎቶ በራስወርቅ ሙሉጌታ
የኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ የተሰራጨባቸው ሃገሮች
/ የካቲት 30, 2012 / ከቀኑ 10:00 ሠዓት /
★ ጣሊያን (Italy)
※ 7,424 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 1,541 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 366 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 133 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ ሞተዋል።
★ ኢራን (Iran)
※ 7,161 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 595 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 237 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 43 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ የሞቱ ናቸው።
★ ደቡብ ኮሪያ (South Korea)
※ 7,478 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 165 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 53 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 2 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ የሞቱ ናቸው።
✔ የሌሎች ሃገሮች የኮሮና ቫይረስ ስርጭት
★ ስፔን (Spain)
※ በስፔን 235 አዲስ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ በአጠቃላይ 909 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
★ ጀርመን (Germany)
※ በጀርመን 200 አዲስ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ በአጠቃላይ 1,112 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
★ አልባኒያ (Albania)
※ አልባኒያ 2 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ስዎች እንዳገኘች ሪፖርት አድርጋለች።
★ ግብጽ (Egypt)
※ ግብጽ በቫይረሱ የመጀመሪያ ሰው (1 ሰው) እንደሞተባት ሪፖርት አድርጋለች።
መልካም ጤንነት!!
EthioTena - ኢትዮጤና
/ የካቲት 30, 2012 / ከቀኑ 10:00 ሠዓት /
★ ጣሊያን (Italy)
※ 7,424 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 1,541 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 366 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 133 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ ሞተዋል።
★ ኢራን (Iran)
※ 7,161 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 595 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 237 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 43 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ የሞቱ ናቸው።
★ ደቡብ ኮሪያ (South Korea)
※ 7,478 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከነዚህ መካከል 165 ሰዎች አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ናቸው።
※ 53 ሰዎች በቫይረሱ ሞተዋል። ከእነዚህ መካከል 2 ሰዎች በአንድ ቀን ውስጥ የሞቱ ናቸው።
✔ የሌሎች ሃገሮች የኮሮና ቫይረስ ስርጭት
★ ስፔን (Spain)
※ በስፔን 235 አዲስ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ በአጠቃላይ 909 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
★ ጀርመን (Germany)
※ በጀርመን 200 አዲስ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ በአጠቃላይ 1,112 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
★ አልባኒያ (Albania)
※ አልባኒያ 2 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ስዎች እንዳገኘች ሪፖርት አድርጋለች።
★ ግብጽ (Egypt)
※ ግብጽ በቫይረሱ የመጀመሪያ ሰው (1 ሰው) እንደሞተባት ሪፖርት አድርጋለች።
መልካም ጤንነት!!
EthioTena - ኢትዮጤና
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ (face mask) አጠቃቀምና እነማን መጠቀም እንዳለባቸው ልብ ይበሉ::
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ (face mask) አጠቃቀሙና እነማን መጠቀም እንዳለባቸው በቅጡ ባለመረዳት ሰዎች ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረጉ ይስተዋላል፡፡
ለመሆኑ ማስክ መጠቀም ያለባቸው እነማን ናቸው?
ጤና ሚኒስቴር መልስ አለው ....
1. የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ መጠቀም የሚያስፈልገን በበሽታው የተያዘ ወይም የተጠረጠረ ሰው አጠገብ ወይም እየተንከባከብን ከሆነ ብቻ፣
2. ሳልና ትኩሳት ካለብን ለሌላው ጥንቃቄ በማድረግ ሲያስለን ወይም ሲያስነጠሰን ነው። እንዲህ ከሆነ ደግሞ ሌሎች ተጨማሪ ጥንቃቄዎችን ማድረግ ያስፈልጋል ለምሳሌ ሰው የሚበዛበት ቦታ ከመሄድ ራስን መቆጠብ ፣ እጅ በደንብ መታጠብ ፣ መጨባበጥ ማቆም እና ማስኩን በስርዓት ማስወገድ እና ለባለሙያ ማሳወቅ ያስፈልጋል::
3. የማስክ አጠቃቀምም ውጤታማ የሚሆነው እጅን በንጹህ ውሃና ሳሙና አዘውትሮ መታጠብ ሲቻል እና አወገገዱም ጥንቃቄ የተሞላበት ሲሆን ብቻ ነው፡፡
ህብረተሰባችን መረጃዎችን ከአስተማማኝ ምንጮች ብቻ በመቀበል፣ የተሳሳቱ መረጃዎች የሚያስከትሉትን መደናገር እና ፍርሀት እርሶም ይከላከሉ!
የበለጠ መረጃ ሲያስፈልግ ነጻ በሆነው 8335 የስልክ መስመር ላይ መደወል ይቻላል፡፡
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ (face mask) አጠቃቀሙና እነማን መጠቀም እንዳለባቸው በቅጡ ባለመረዳት ሰዎች ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ሲዳረጉ ይስተዋላል፡፡
ለመሆኑ ማስክ መጠቀም ያለባቸው እነማን ናቸው?
ጤና ሚኒስቴር መልስ አለው ....
1. የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ መጠቀም የሚያስፈልገን በበሽታው የተያዘ ወይም የተጠረጠረ ሰው አጠገብ ወይም እየተንከባከብን ከሆነ ብቻ፣
2. ሳልና ትኩሳት ካለብን ለሌላው ጥንቃቄ በማድረግ ሲያስለን ወይም ሲያስነጠሰን ነው። እንዲህ ከሆነ ደግሞ ሌሎች ተጨማሪ ጥንቃቄዎችን ማድረግ ያስፈልጋል ለምሳሌ ሰው የሚበዛበት ቦታ ከመሄድ ራስን መቆጠብ ፣ እጅ በደንብ መታጠብ ፣ መጨባበጥ ማቆም እና ማስኩን በስርዓት ማስወገድ እና ለባለሙያ ማሳወቅ ያስፈልጋል::
3. የማስክ አጠቃቀምም ውጤታማ የሚሆነው እጅን በንጹህ ውሃና ሳሙና አዘውትሮ መታጠብ ሲቻል እና አወገገዱም ጥንቃቄ የተሞላበት ሲሆን ብቻ ነው፡፡
ህብረተሰባችን መረጃዎችን ከአስተማማኝ ምንጮች ብቻ በመቀበል፣ የተሳሳቱ መረጃዎች የሚያስከትሉትን መደናገር እና ፍርሀት እርሶም ይከላከሉ!
የበለጠ መረጃ ሲያስፈልግ ነጻ በሆነው 8335 የስልክ መስመር ላይ መደወል ይቻላል፡፡
አንድ መቶ ሰባ ስድስት (176) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
👉 3 ሰዎች አርፈዋል፤
👉 75 ሰዎች አገግመዋል
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5636 የላብራቶሪ ምርመራ 176 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3521 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 28 (17 ከጤና ተቋም እና 11 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን አንድ ናሙና ከጤና ተቋም የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። በተጨማሪ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል።
በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 60 ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰባ አምስት (75) ሰዎች (31 ከአዲስ አበባ፣ 28 ከሶማሊ ክልል፣ 10 ከኦሮሚያ ክልል፣ 5 ከአማራ ክልል እና 1 ከአፋር ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 545 ነው።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
👉 3 ሰዎች አርፈዋል፤
👉 75 ሰዎች አገግመዋል
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5636 የላብራቶሪ ምርመራ 176 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3521 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 28 (17 ከጤና ተቋም እና 11 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን አንድ ናሙና ከጤና ተቋም የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። በተጨማሪ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል።
በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 60 ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰባ አምስት (75) ሰዎች (31 ከአዲስ አበባ፣ 28 ከሶማሊ ክልል፣ 10 ከኦሮሚያ ክልል፣ 5 ከአማራ ክልል እና 1 ከአፋር ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 545 ነው።
ትንቢት በሚራዘምበት አገር ምርጫ ቢራዘም ምን ይገርማል?
ዘንድሮ “መራዘም” ብሎ ቃል ክብሪት ሆኗል። ባሳለፍነው ሳምንት የፌደሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የህዝብና ቤት ቆጠራው መራዘም ያልተዋጠላቸውና የተዋጠላቸው የምክር ቤቱ አባላት ተረት ተታኩሰዋል።
አንዲት የምክር ቤቱ አባል “እንኳን ዘንቦብሽ ድሮም ጤዛ ነሽ” በማለት ቆጠራው መራዘሙን ሲተቹ ፤ ሌላ የምክር ቤት አባል “ለማያቅሽ ታጠኚ” ብለው እርፍ አሉ።
ከዚህ ቀደምም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫውን ለማራዘም ባደረገው ውይይት ሃሳቡን የተቃወሙ የምክር ቤቱ አባል “ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ነሽ ይሏታል” ብለው ተርተው ነበር። ለትችቱ ምላሽ የሰጡ ሌላ የምክር ቤቱ አባል ደግሞ “ጅብ የማያውቁት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላል” ብለው ተርተዋል። የመልስ ምቱ ይበልጥ ጠንክሮ “ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ” እና “አዛኝ ቅቤ አንጓች” ታክለዋል።
በርግጥ ምክር ቤቶቹ ለተረትና ምሳሌዎች አዲስ አይደሉም። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበር ተፈቅዶላቸው ፓርላማ የገቡ ጥቂት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በገዢው ፓርቲ ሰዎች በሚተኮሱ ተረቶች ሲቆስሉ ኖረዋል። ልዩነቱ ያኔ ተራች መንግስት ነበር። የያኔዎቹ የተቃውሞ ጎራ ሰዎች እንኳን ለብሽሽቅ ተረት የሚወክሉትን ህዝብ ጥያቄ ለማቅረብ የማትበቃ ሁለት ደቂቃ ነበር የሚሰጣቸው። ከዛ ሃሳባቸው ሳያልቅ ሰዓታቸው ያልቃል ፤ አይ ዴሞክራሲ !
ዛሬ ደግሞ ተረት ተራቹ ተቃዋሚው ቡድን ሆኗል። የፌዴራል መንግስቱን የተቆጣጠረው ገዢ ፓርቲም “እሾህን በእሾህ” አይነት ስትራቴጂ ቀይሷል። ሁኔታዎች በዚህ መልኩ የሚቀጥሉ ከሆነ የሁለቱ ምክር ቤት አባሎች ከሕገመንግስቱ እኩል ለተረት መጽሐፍት ትኩረት መስጠት መጀመራቸው አይቀሬ ነው። https://www.press.et/Ama/?p=34542
ዘንድሮ “መራዘም” ብሎ ቃል ክብሪት ሆኗል። ባሳለፍነው ሳምንት የፌደሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የህዝብና ቤት ቆጠራው መራዘም ያልተዋጠላቸውና የተዋጠላቸው የምክር ቤቱ አባላት ተረት ተታኩሰዋል።
አንዲት የምክር ቤቱ አባል “እንኳን ዘንቦብሽ ድሮም ጤዛ ነሽ” በማለት ቆጠራው መራዘሙን ሲተቹ ፤ ሌላ የምክር ቤት አባል “ለማያቅሽ ታጠኚ” ብለው እርፍ አሉ።
ከዚህ ቀደምም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫውን ለማራዘም ባደረገው ውይይት ሃሳቡን የተቃወሙ የምክር ቤቱ አባል “ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ነሽ ይሏታል” ብለው ተርተው ነበር። ለትችቱ ምላሽ የሰጡ ሌላ የምክር ቤቱ አባል ደግሞ “ጅብ የማያውቁት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላል” ብለው ተርተዋል። የመልስ ምቱ ይበልጥ ጠንክሮ “ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ” እና “አዛኝ ቅቤ አንጓች” ታክለዋል።
በርግጥ ምክር ቤቶቹ ለተረትና ምሳሌዎች አዲስ አይደሉም። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበር ተፈቅዶላቸው ፓርላማ የገቡ ጥቂት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በገዢው ፓርቲ ሰዎች በሚተኮሱ ተረቶች ሲቆስሉ ኖረዋል። ልዩነቱ ያኔ ተራች መንግስት ነበር። የያኔዎቹ የተቃውሞ ጎራ ሰዎች እንኳን ለብሽሽቅ ተረት የሚወክሉትን ህዝብ ጥያቄ ለማቅረብ የማትበቃ ሁለት ደቂቃ ነበር የሚሰጣቸው። ከዛ ሃሳባቸው ሳያልቅ ሰዓታቸው ያልቃል ፤ አይ ዴሞክራሲ !
ዛሬ ደግሞ ተረት ተራቹ ተቃዋሚው ቡድን ሆኗል። የፌዴራል መንግስቱን የተቆጣጠረው ገዢ ፓርቲም “እሾህን በእሾህ” አይነት ስትራቴጂ ቀይሷል። ሁኔታዎች በዚህ መልኩ የሚቀጥሉ ከሆነ የሁለቱ ምክር ቤት አባሎች ከሕገመንግስቱ እኩል ለተረት መጽሐፍት ትኩረት መስጠት መጀመራቸው አይቀሬ ነው። https://www.press.et/Ama/?p=34542
የዩናይትድ ኪንግደም ተመራማሪዎች ዴዛማታሶን ( Dexamethasone) የኮሮናቫይረስ ህሙማንን ከሞት መታደጉን አረጋግጠናል አሉ
*****************************
(ኢፕድ)
የዩናይትድ ኪንግደም ተመራማሪዎች ርካሽና በቀላሉ በየትኛውም አካባቢ ሊገኝ የሚችለው ዴዛማታሶን( Dexamethasone) የተሰኘው መድሃኒት የኮሮናቫይረስ ህመምተኛን ከሞት ሊታደግ እንደሚችል አረጋግጠናል አሉ። ተማማሪዎቹ እንደሚሉት መድሃኒቱ እስካሁን ጥቅም ላይ ከዋሉት መድሃኒቶች ሁሉ ሞትን በመቀነስ ተወዳዳሪ የለውም።
ቬንትሌተር ለሚያስፈልጋቸው ህመምተኞች መድሃኒቱ ከ40- 28 በመቶ የሚሆኑትን የማዳን አቅም ያለው ሲሆን፣ ኦክስጂን በአጋዥ የመተንፈሻ መሳሪያ ለሚያስፈልጋቸው ህመምተኞች ደግሞ ከ25 -20 በመቶ የሚሆኑትን የማዳን አቅም አለው ተብሏል።
ዋና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ፒተር ሆርቢ እንደሚሉት “ይህ መደሃኒት እስካሁን ከተገኙት መደሃኒቶች በሙሉ ሞትን በመቀነስ ረገድ ተወዳዳሪ የለውም፤ ሞትን ትርጉም ባለው ሁኔታ ቀንሷል፤ በዘርፉ በተካሄዱ የምርምር ሂደትም ትልቅ ዕምርታ ነው።”
ምርምሩን የመሩት ፕሮፌሰር ማርቲን ላንድሬይ በበኩላቸው “የመድሃኒቱ አስፈላጊነት አጠያያቂ አይደለም፤ በዋጋም በጣም ርካሽ ነው፤ ለአንድ ሰው የሚያስፈልገው 35 ፓውንድ ብቻ ነው። ከዚህም በላይ ይላሉ ፕሮፌሰር ላንድሬይ መደሃኒቱ በየትኛውም አካባቢ በቀላሉ ሊገኝ የሚቻል ነው” ብለዋል።
ፕሮፌሰር ላንድሬይ መድሃኒቱ በራሳቸው ለመተንፈስ ለሚችሉ ህመምተኞች አያስፈልጋቸውም፤ መድሃኒቱ የሚያስፈልጋቸው በሆስፒታል ለተኙ ጽኑ ህመምተኞች ብቻ ነው። ማንም መድሃኒቱን ገዝቶ እቤቱ መጠቀም ይችልም ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገረዋል።
*****************************
(ኢፕድ)
የዩናይትድ ኪንግደም ተመራማሪዎች ርካሽና በቀላሉ በየትኛውም አካባቢ ሊገኝ የሚችለው ዴዛማታሶን( Dexamethasone) የተሰኘው መድሃኒት የኮሮናቫይረስ ህመምተኛን ከሞት ሊታደግ እንደሚችል አረጋግጠናል አሉ። ተማማሪዎቹ እንደሚሉት መድሃኒቱ እስካሁን ጥቅም ላይ ከዋሉት መድሃኒቶች ሁሉ ሞትን በመቀነስ ተወዳዳሪ የለውም።
ቬንትሌተር ለሚያስፈልጋቸው ህመምተኞች መድሃኒቱ ከ40- 28 በመቶ የሚሆኑትን የማዳን አቅም ያለው ሲሆን፣ ኦክስጂን በአጋዥ የመተንፈሻ መሳሪያ ለሚያስፈልጋቸው ህመምተኞች ደግሞ ከ25 -20 በመቶ የሚሆኑትን የማዳን አቅም አለው ተብሏል።
ዋና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ፒተር ሆርቢ እንደሚሉት “ይህ መደሃኒት እስካሁን ከተገኙት መደሃኒቶች በሙሉ ሞትን በመቀነስ ረገድ ተወዳዳሪ የለውም፤ ሞትን ትርጉም ባለው ሁኔታ ቀንሷል፤ በዘርፉ በተካሄዱ የምርምር ሂደትም ትልቅ ዕምርታ ነው።”
ምርምሩን የመሩት ፕሮፌሰር ማርቲን ላንድሬይ በበኩላቸው “የመድሃኒቱ አስፈላጊነት አጠያያቂ አይደለም፤ በዋጋም በጣም ርካሽ ነው፤ ለአንድ ሰው የሚያስፈልገው 35 ፓውንድ ብቻ ነው። ከዚህም በላይ ይላሉ ፕሮፌሰር ላንድሬይ መደሃኒቱ በየትኛውም አካባቢ በቀላሉ ሊገኝ የሚቻል ነው” ብለዋል።
ፕሮፌሰር ላንድሬይ መድሃኒቱ በራሳቸው ለመተንፈስ ለሚችሉ ህመምተኞች አያስፈልጋቸውም፤ መድሃኒቱ የሚያስፈልጋቸው በሆስፒታል ለተኙ ጽኑ ህመምተኞች ብቻ ነው። ማንም መድሃኒቱን ገዝቶ እቤቱ መጠቀም ይችልም ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገረዋል።
ምልክት የማያሳዩ የኮሮና ታማሚዎችን ጭምር ለመለየት የሚያስችል የምርመራ መሳሪያ ተሰራ
ምልክት የማያሳዩትን ጨምሮ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኮሮና ቫይረስ ታማሚዎችን በቀላሉ ለመለየት የሚያስችል የምርመራ መሳሪያ መስራታቸውን በእንግሊዝ የበርሚንግሃም ዩኒቨርስቲ ተመራማሪዎች አስታወቁ፡፡
አብዛኞቹ የቫይረሱ ታማሚዎች በቫይረሱ መያዛቸው የታወቀው ከታመሙ በኋላ መሆኑ አሳሳቢ ነው ያሉት ተመራማሪዎቹ ግኝታቸው በስፋት ለመመርመር እና ምልክት የማያሳዩትን የቫይረሱን ተጠቂዎች ጭምር ለመለየት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡
የሚሰበሰቡ የቫይረሱን ናሙናዎች 98 በመቶ ያህል የመለየት አቅም አለውም ተብሏል፡፡
ዴይሊ ሜይል ጨዋታ ቀያሪ ያለው አዲሱ ግኝት በቫይረሱ ስንያዝ ሰውነታችን ሊያዘጋጅ የሚችለውን የጸረ እንግዳ አካል (antibodies) ሁኔታ በማጤን የሚሰራ ነው፡፡
1 ሺ የሚጠጉ የእንግሊዝ የጤና ሰራተኞች በተሳተፉበት የጥናት ሂደትም ውጤታማነቱ ተረጋግጧል፡፡
በቫይረሱ ሊጠቁ እንደሚችሉ ከሚታሰቡ 10 ሰዎች 8 ምልክቶቹን ላያሳዩ እንደሚችሉ የመስኩ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ ምንጭ -አልአይን
ምልክት የማያሳዩትን ጨምሮ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኮሮና ቫይረስ ታማሚዎችን በቀላሉ ለመለየት የሚያስችል የምርመራ መሳሪያ መስራታቸውን በእንግሊዝ የበርሚንግሃም ዩኒቨርስቲ ተመራማሪዎች አስታወቁ፡፡
አብዛኞቹ የቫይረሱ ታማሚዎች በቫይረሱ መያዛቸው የታወቀው ከታመሙ በኋላ መሆኑ አሳሳቢ ነው ያሉት ተመራማሪዎቹ ግኝታቸው በስፋት ለመመርመር እና ምልክት የማያሳዩትን የቫይረሱን ተጠቂዎች ጭምር ለመለየት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡
የሚሰበሰቡ የቫይረሱን ናሙናዎች 98 በመቶ ያህል የመለየት አቅም አለውም ተብሏል፡፡
ዴይሊ ሜይል ጨዋታ ቀያሪ ያለው አዲሱ ግኝት በቫይረሱ ስንያዝ ሰውነታችን ሊያዘጋጅ የሚችለውን የጸረ እንግዳ አካል (antibodies) ሁኔታ በማጤን የሚሰራ ነው፡፡
1 ሺ የሚጠጉ የእንግሊዝ የጤና ሰራተኞች በተሳተፉበት የጥናት ሂደትም ውጤታማነቱ ተረጋግጧል፡፡
በቫይረሱ ሊጠቁ እንደሚችሉ ከሚታሰቡ 10 ሰዎች 8 ምልክቶቹን ላያሳዩ እንደሚችሉ የመስኩ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ ምንጭ -አልአይን
በዚህ ወሳኝ ወቅት መከላከያን አንስቶ ማብጠልጠል የለየለት የሀገር ክህደት ወንጀልና ባንዳነት ነው።
👉ምሁራን ለሀገራቸው የሚሰጡት ትልቁ ስጦታ እውቀታቸውን ነው። ከተራ ወታደር እስከ ጀነራል መኮንኖች ድረስ የሚሰጡት መተኪያ የሌላትን ሕይወታቸውን ነው። ለሀገር ከዚህ በላይ ታላቅ ስጦታ የለም።
👉ሀገሬን ወገኔን እወዳለሁ የሚል ማንኛውም ዜጋ የሀገሩን ሰላም ጸጥታና ደህንነት ለመጠበቅና ለማስከበር ሁልግዜም ከሠራዊቱ ጎን መቆም መሰለፍ ይገባዋል ብለን እናምናለን።
👉በለውጡ መጀመሪያ አካባቢ ሲጻፉ የነበሩ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት የሚነኩ፤ መረጃን አሳልፈው ለጠላቶቻችን ሲሰጡ የነበሩ ለምሳሌነት የሠራዊቱ ሞራል ደካማ ነው ፤ ሠራዊቱ በጎሣ የተከፋፈለ ነው ብሎ መጻፍና መናገር ትልቅ ወንጀል ነው።
👉ሠራዊቱና አመራሩ እንዲጋጭ እንዳይግባባ መተማመን እንዳይኖረው ለሀገር ጠላት በር ለመክፈት ሆን ተብሎ ሲሰራ የነበረ ምናልባትም ከጀርባ በጠላቶቻችን ፋይናንስ የተደረገ በሀገር ክህደት ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው።
👉ከሠራዊቱ ውስጥ መረጃ አግኝቻለሁ በሚል የራሳቸውን መረጃ ፈጥረውና ፈብርከው ወይም ከሠራዊቱ የለቀቁና ቅሬታ የነበራቸው ሰዎች የሚሰጡትን የጥላቻ መረጃ ያለአንዳች የጎንዮሽ ማረጋገጥ እውነት አስመስለው በመጻፍ ለገንዘብ ማግኛ ሲጠቀሙበት የነበረ የሚዲያ እንቅስቃሴ አይተናል።
👉ምሁራን ለሀገራቸው የሚሰጡት ትልቁ ስጦታ እውቀታቸውን ነው። ከተራ ወታደር እስከ ጀነራል መኮንኖች ድረስ የሚሰጡት መተኪያ የሌላትን ሕይወታቸውን ነው። ለሀገር ከዚህ በላይ ታላቅ ስጦታ የለም።
👉ሀገሬን ወገኔን እወዳለሁ የሚል ማንኛውም ዜጋ የሀገሩን ሰላም ጸጥታና ደህንነት ለመጠበቅና ለማስከበር ሁልግዜም ከሠራዊቱ ጎን መቆም መሰለፍ ይገባዋል ብለን እናምናለን።
👉በለውጡ መጀመሪያ አካባቢ ሲጻፉ የነበሩ የሀገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት የሚነኩ፤ መረጃን አሳልፈው ለጠላቶቻችን ሲሰጡ የነበሩ ለምሳሌነት የሠራዊቱ ሞራል ደካማ ነው ፤ ሠራዊቱ በጎሣ የተከፋፈለ ነው ብሎ መጻፍና መናገር ትልቅ ወንጀል ነው።
👉ሠራዊቱና አመራሩ እንዲጋጭ እንዳይግባባ መተማመን እንዳይኖረው ለሀገር ጠላት በር ለመክፈት ሆን ተብሎ ሲሰራ የነበረ ምናልባትም ከጀርባ በጠላቶቻችን ፋይናንስ የተደረገ በሀገር ክህደት ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው።
👉ከሠራዊቱ ውስጥ መረጃ አግኝቻለሁ በሚል የራሳቸውን መረጃ ፈጥረውና ፈብርከው ወይም ከሠራዊቱ የለቀቁና ቅሬታ የነበራቸው ሰዎች የሚሰጡትን የጥላቻ መረጃ ያለአንዳች የጎንዮሽ ማረጋገጥ እውነት አስመስለው በመጻፍ ለገንዘብ ማግኛ ሲጠቀሙበት የነበረ የሚዲያ እንቅስቃሴ አይተናል።
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5274 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሃያ ዘጠኝ (129) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3759 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (11 ከጤና ተቋም እና 7 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ናሙና የለም። ከዚህ ባለፈ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ስልሳ ሶስት (63) ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት አንድ መቶ አስራ አንድ (111) ሰዎች (109 ከአዲስ አበባ እና 2 ከድሬዳዋ) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 849 ነው።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (11 ከጤና ተቋም እና 7 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት ናሙና የለም። ከዚህ ባለፈ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ስልሳ ሶስት (63) ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት አንድ መቶ አስራ አንድ (111) ሰዎች (109 ከአዲስ አበባ እና 2 ከድሬዳዋ) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 849 ነው።