Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ኢዜማ የምርጫ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሲያካሂድ የነበረውን የምርጫ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።
ፓርቲው ለዝግጅት ክፍሉ ትናንት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ምርጫ ቦርድ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ምርጫው ላይ በንቃት ለመሳተፍ እና ምርጫው ሰላማዊ፣ ነፃ እና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሲያደርግ የነበራቸውን ዝግጅቶች አጠናቆ ወደትግበራ እየገባ ነው።
ለምርጫው ሲያደርግባቸው ከቆየባቸው ዝግጅ ቶች መካከል አባላት እና ደጋፊዎች በምርጫ እንቅስቃሴ ወቅት ሊመሩበት የሚገባ የምርጫ ሥነ-ምግባር መመሪያ ይፋ መሆኑን አመልክቷል።
ይህ መመሪያ ቀጣዩ ምርጫ ለሀገራችን ሰላም እና መረጋጋት እንዲሁም ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፋይዳ ከግምት በማስገባት የተዘጋጀ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፣ መመሪያው ለአባላት እና ደጋፊዎች ታትሞ እንደሚሰራጭ አስታውቋል፡፡ በመመሪያው ዙሪያ ሥልጠናም እንደሚሰጥ ጠቁሟል።
https://www.press.et/Ama/?p=39158
የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በጅግናው የሀገር መከላከያና የጸጥታ ሃይሎች ትብብር መያዛቸው ትላንት መገለጹ ይታወቃል። ከእነዚህ መካከል ስብሀት ነጋ፣ ቅዱሳን ነጋና ሌሎች የጁንታው አመራሮች ከላይ በምስሉ የሚታዩት ናቸው።
ስብሃት ነጋን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉ ዘጠኝ የጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገቡ
*********************
(ኢ.ፕ.ድ)

የጥፋት ስትራቴጂስቱና ዋነኛው የጁንታ መሪ ስብሃት ነጋን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉ ዘጠኝ የጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገብተዋል።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት የጥፋት ስትራቴጂስቱና ዋነኛው የጁንታ መሪ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች የጥፋት ቡድኑ አመራሮች በቁጥጥር ስር ማዋሉን መግለጹ ይታወሳል።

የጁንታው አመራሮች የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስና ሌሎች የፌደራል ጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ፍተሻና አሰሳ ከተደበቁበት ለሰው ልጅ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ሰርጥ ውስጥ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

የጥፋት ቡድኑ አመራሮችን ለመከላከል በአካባቢው ጥበቃ ላይ የነበረ የጁንታው ታጣቂ ሀይል መደምሰሱም በወቅቱ ተገልጿል።



በዚሁ መሰረት


1.የጁንታው ቁንጮ አመራርና የጥፋት ስትራቴጂስት፣ ስብሃት ነጋ

2.ቅዱሳን ነጋ -የትግራይ ክልል አፈ ጉባኤ የነበረች

3. ቴዎድሮስ ሀጎስ-የመለስ አመራር አካዳሚ ፕሬዚዳንትና የኢፈርት ቦርድ ሃላፊ የነበረ፣

4. አባዲ ዘሙ-በሱዳን የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የነበረና የጁንታውን ፖለቲካ ክንፍ የተቀላቀለ፣

5. ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔ -የቀድሞ የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

6. ገብረመድህን ተወልደ-የክልሉ ንግድ ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

7. ወልደጊዮርጊስ ደስታ-የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበረ፣

8. ተክለወይኒ አሰፋ-የማረት ስራ አስፈጻሚ የነበረ፤

9. ወይዘሮ ምህረት ተክላይ - የክልሉ ምክር ቤት ህግ አማካሪ የነበረች፤ ሁሉም በዛሬው እለት አዲስ አበባ ገብተዋል።

የምዕራብ እዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል መሰለ መሰረት ለኢዜአ እንዳሉት፤ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ የጁንታውን ሃይል ድል አድርጎ አሁን ደግሞ የቡድኑን አመራሮች በቁጥጥር ስር እያወለ መሆኑን ተናግረዋል።

ሰራዊቱ በህግ ማስከበርና ህልውና ዘመቻ አንፀባራቂ ድሎችን ያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የጥፋት ስትራቴጂስቱና ዋነኛው የጁንታ መሪ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች የጥፋት ቡድኑ አመራሮች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ነው የተናገሩት።

እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የ24ኛ ክፍለጦር አዛዥ ኮሎኔል አማረ በዓታ በበኩላቸው፣ ሰራዊቱ ሌት ተቀን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ቀሪ የጁንታው ቡድን አመራሮች ከያሉበት እያደነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
የዳግማዊ አፄ ምኒልክ መታሰቢያ ሙዚየምና የባሕል ማዕከል
እየተመረቀ ነው
***************************
(ኢ ፕ ድ)
የዳግማዊ አፄ ምኒልክ መታሰቢያ ሙዚየምና የባሕል ማዕከል የሚገኘው በጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ከተማ በአንኮበር ነው፡፡
በ333 ዓ.ም የተመሠረተችው አንኮበር ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የበርካታ ነገሥታት መቀመጫ እንደነበረችና ሌሎች ነገሥታትም ከሌላ አካባቢ ወደ አንኮበር መጥተው ንግሥናቸዉን ሲቀበሉ እንደነበረ የአንኮበር ወረዳ ባሕልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡
አንኮበር ከተቆረቆረች ጊዜ ጀምሮ ለበርካታ የሸዋ ነገሥታት መቀመጫ በመሆን አገልግላለች። 38 ነገሥታትም ነግሰውባታል። ከ15ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህም አምሀየሱስ፣ አስፋው ወሰን፣ ወሰን ሰገድ፣ ሳኅለስላሴ፣ ኀይለመለኮትና ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ነግሰውባታል። መቀመጫቸው አድርገዋትም ሀገር አስተዳድረዋል።
ይህች የጥንታዊ ነገሥታት መቀመጫ የበርካታ ባሕላዊ ትውፊቶችና ታሪካዊ እንዲሁም ሃይማኖታዊ ቅርሶች መገኛ ናት።
የወረዳው ባሕልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኀላፊ ፈለቀ ምሕረት ለአብመድ እንደተናገሩት ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት፣ የወርቅ ጽናጽል፣ የብር ከበሮ እና መቋሚያን ጨምሮ በወቅቱ የነገሥታቱ መገልገያ የነበሩ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶች መገኛ ናት።
እነዚህን ቅርሶች በተደራጀ ቦታ ለማስቀመጥና ለጉብኝት ክፍት አልነበሩም፣ ይልቁንም የተቀመጡት በወረዳው በሚገኙ 97 ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ተበታትነው ነበር። በዚህም ምክንያት ቅርሶችን ከነታሪካቸው በሚፈለገው ደረጃ ለትውልድ ማስተዋወቅ አልተቻለም ብለዋል።
ወረዳውም በቱሪዝም ተጠቃሚ መሆን አልቻለም ነው ያሉት። አሁን አንኮበር ታሪኳን የምታስተዋውቅበትና ቅርሶቿንም የምታድስበት ዘመናዊ ቤተመዘክር እንደተገነባላት አስረድተዋል።
እንደ ኀላፊው ገለጻ ወረዳው ለቤተ መዘክሩ ግንባታ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጎበታል። ቤተ መዘክሩ የደኀንነት ካሜራዎች ተገጥመውለታል። የክልሉ መንግሥትም ቅርሶች ከሰው ንክኪ ነፃ ሆነው እንዲጎበኙ የሚያስችል መስተዋት አሠርቷል።
ይህም ቅርሶች ለጉብኝት ክፍት እንዲሆኑ ከማስቻል ጀምሮ ደኀንነታቸው በአስተማማኝ መልኩ እንዲጠበቅ ያደርጋል ብለዋል። የወረዳውን የቱሪዝም እንቅስቃሴም በከፍተኛ ደረጃ ያነቃቃል ተብሎ ታምኖበታል።
ወረዳውም ቱሪዝሙን ይበልጥ ለማነቃቃት በቤተ መዘክሩ አጠገብ ደረጃውን የጠበቀ የእንግዶች ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ ጀምሯል።
የዳግማዊ አፄ ምኒልክ መታሰቢያ ሙዚየምና የባሕል ማዕከልም በዛሬው ቀን እየተመረቀ መሆኑን አብመድ ዘግቧል።
የ2013 ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ
***************************
(ኢ ፕ ድ)
ዛሬ መነሻውን መስቀል አደባባይ መዳርሻውን አክሱም ህንፃ አካባቢ ያደረገው ታላቁ ሩጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ለ20ኛ ጊዜ በተደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር የውጭ ሀገር ዜጎችን ጨምሮ በርካታ የከተማችን ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡
ለውድድሩ በሰላም መጠናቀቅ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የፌዴራል ፖሊስና ሌሎች የፀጥታ አካላት፤ እንዲሁም የፕሮግራሙ አዘጋጆች እና የተሳታፊዎች ቀና ትብብር ለስነስርዓቱ በስኬት መጠናቀቅ አስተዋፅዖ የላቀ በመሆኑ ለሁሉም አካላት ኮሚሽኑ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
የ20ኛው የ2013 ዓ.ም የታላቁ ሩጫ የወንዶች አሸናፊዎች
1ኛ. አቤ ጋሻሁን - ከአማራ ማረሚያ
2ኛ. ታደሰ ወርቁ - ደቡብ ፓሊስ
3ኛ. ሚልኬሳ መንገሻ - ከሰበታ ክለብ
የ20ኛው የ2013 ዓ.ም የታላቁ ሩጫ የሴቶች አሸናፊዎች
1ኛ. ፅጌ ገ/ሰላማ - ከኢትዮ አትሌትክስ
2ኛ. መድን ገ/ስላሴ - ከንግድ ባንክ
3ኛ. ገበያነሽ አያሌው - ከመከላከያ
አቶ ተፈራ ዋልዋ ከሁለት አመት በፊት ስለ ለውጡና ስለ ጁንታው እንዲህ ብለው ነበር
👉 አብይ እና አብይን የመሳሰሉ ጭንቅላቶች ለሀገራችን የዘመኑ ጭንቅላቶች ናቸው፤
👉 ፈጥኖ መሄድ የሚችል ጭንቅላቶች ለውጥ ፈላጊ ጭንቅላቶች ናቸው፤ ለውጡ ደግሞ ዝም ብሎ ተነካኪ ለውጥ አይደለም፤ ተሻግሮ የሚሄዱ ለውጦችን ማምጣት የሚፈልጉ ጭንቅላቶች ናቸው፤
👉 ታዲያ ይሄ ኢትዮጵያን ማሸጋገር አይችልም ብሎ ማሳብ እንዴት ይቻላል፤
👉 ይሄ ኢትዮጵያን ያበላሻል ብለው የሚያስቡ እዛው ድሮ የነበረ ቦታ ላይ ቆሞ የቀረ አስትሳሰብ የያዘ ሰው ብቻ ነው፤ ወይም ደግሞ እኛ ያለፍንበትን ረስተዋል ማለት ነው፤
👉 እኛ ስንታገል በትልልቅ ሰዎች “ተማሪ ጠግቦ፤ አይ የልጅ ነገር” ይባል ነበር፤ ግን እድላቸውን የሚወስን ጉዞ ውስጥ ነበር የምንጓዘው፤ አሁንም የሆነው ይሄው ነው፤
👉 የዝምባብዌው ሙጋቤ በ90 አመታቸው አገር ለመምራት እኔ ነኝ ብለው ነበር፤ የእኔው ባልደረቦች እኛ በምናስበው መንገድ ነው ሁሉ ነገር መሄድ ያለበት ብለው ሲያስቡ የኢትዮጵያ ሙጋቤዎች ነው ያልኳቸው፤
👉 አሁን እነ አብይ የሚራመዱትን ጉዞ የዘመኑ ጉዞ ነው፤ የዘመኑ ሀይል ነው፤ ተገቢ ነው ይሄ ነው የበለጠ ይሄን አገር የሚያራምደው ብሎ ማሰብ ከተሳነን እኛ ራሳችን ያለፍንበትን መርሳት ነው፤
በመከላከያ ሠራዊት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ያደረጉ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ያደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ከአገር መከላከያ ሠራዊቱን በማስከዳት ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩና በጦርነቱ ከሠራዊቱ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀሉ ጄኔራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ መኮንኖች፣ መስመራዊ መኮንኖችና የግል ጥበቃዎቻቸው ላይ እርምጃ መወሰዱንም የመከላከያ ሠራዊት ሃይል ስምሪት መምሪያ ሃላፊ ብርጋዴል ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።
በዚሁ መሰረት እርምጃ የተወሰደባቸው
1ኛ- ሜጀር ጄኔራል ኢብራሂም አብዱልጀሊል፡- ቀደም ሲል የመከላከያ ሎጂስቲክ ሃላፊ የነበረና አሁን የጁንታው ሎጂስቲክ ሃላፊ የነበረ
2ኛ- ብርጋዴል ጄኔራል ገብረኪዳን ገብረማርያም፡- የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ሃላፊ የነበረና በጡረታ ከተሰናበተ በኋላ ጁንታውን የተቀላቀለ
3ኛ- አስር ከፍተኛ መኮንኖች
4ኛ - ሁለት መስመራዊ መኮንኖች
5ኛ- አንድ የክልሉ ረዳት ኮሚሽነር የነበረና ከፖሊስ ከድቶ ወደ ጁንታው የተቀላቀለ ናቸው።
በተጨማሪም የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩ የጁንታው አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል
እነዚህም
1ኛ- አቶ አባይ ወልዱ፡- የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበረ
2ኛ- ዶክተር አብርሃም ተከስተ- የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበረ
3ኛ- ዶክተር ረዳኢ በርሄ፡- የክልሉ ኦዲተር ሃላፊ የነበረ
4ኛ ዶክተር ሙሉጌታ ይርጋ፡- የክልሉ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሃላፊ የነበረ
5ኛ- አቶ ዕቁባይ በርሄ- የሃይማኖት ጉዳይ ክትትል ሃላፊ የነበረ
6ኛ- አቶ ጌታቸው ተፈሪ፡- የክልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤትና የሠላምና ደህንነት ሃላፊ የነበረ
7ኛ- ወይዘሮ ኪሮስ ሃጎስ፡- የክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ የነበረች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ሁለት ከመከላከያ ከድተው ጁንታውን የተቀላቀሉ ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን እነሱም ኮሎኔል ገብረእግዚአብሄር አምባዬና ኮሎኔል ትርፏ አሰፋ መሆናቸውን ብርጋዴል ጄኔራሉ ገልፀዋል።
በእጸገነት አክሊሉ
ኢፋ ሊበን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሊበን ጭቋላ ወረዳ በ20 ሚሊዩን ብር ወጪ የተገነባው ኢፋ ሊበን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ፡፡
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ለተማሪዎቹ ዩኒፎርም ፣ቦርሳና የሙቀት መለኪያ መሳሪያዎች ለትምህርት ቤቱ በስጦታ ተበርክተዋል፡፡
ትምህርት ቤቱ በዉስጡ የአስተዳደር ህንጻ፤የመማሪያ ክፍሎች ፤ላብራቶሪ፤ ቤተ መጽሀፍት፣ የኮምፕዩተር ላብራቶሪና የመጸዳጃ ህንጻዎችን ያካተተ ነው፡፡
ጽ/ቤቱ ካሰራቸዉ 20 ትምህርት ቤቶች ዉስጥ በዛሬዉ እለት ያስመረቀዉ የኢፋ ሊበን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታቸዉ ተጠናቆ ከተመረቁት አምስተኛዉ ሲሆን ቀሪዎቹን ትምህርት ቤቶችን በቅርቡ በሁሉም ክልሎች ያስመርቃል፡፡
ትምህርት ቤቱ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በአንድ ፈረቃ 1300 ተማሪዎችን የመቀበል አቅም አለዉ፡፡ የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በትምህርት ቤት እርቀትና እጥረት ምክንያት ልጆቻቸዉን ወደ ትምህርት ገበታ ላልላኩ የሊበን ጭቋላ፣ አዱላላ፣ቆቃ እና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤቱ በመላክ እድሉን እንዲጠቀሙ ጥሪ ማስተላለፉን ከቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
አምባገነኖች ሌላውን መግደል ያረካቸዋል፤ የራሳቸው ሕይወት ግን ያሳሳቸዋል!
********************
(ኢ ፕ ድ)
ዓለማችን በየዘመኑ በርካታ አምባገነን መሪዎችና በየደረጃው በአመራር ላይ ያሉ አረመኔ ገዳዮችን አስተናግዳለች ። ለአብነትም በዓለም ላይ ከስድስት ሚሊዮን በላይ አይሁዳውያን እንዲጨፈጨፉ ያደረገው ቁጥር አንድ አምባገነን አዶልፍ ሂትለር፣ በአረመኔነቱ አቻ የማይገኝለት ጆሴፍ ስታሊን፣ የኡጋንዳው ሰው በላይ ኢዲ አሚን ዳዳ፣ የኢራቁ አምባገነን መሪ ሳዳም ሁሴን፣ የሊቢያው ሙአመር ጋዳፊና ሌሎች ተጠቃሽ ናቸው።
እነዚህ መሪዎች ከላይ ዋናውን መንበር ይቆጣጠሩ እንጂ ከነሱ ስር በመሆን የራሳቸው መረብ የዘረጉና ሕዝባቸውን የጨፈጨፉ አምባገነኖች መኖራቸውም በየዘመኑ የታየ እውነታ ነው ።ለምሳሌ ከአዶልፍ ሂትለር ጀርባ በመሆን በርካታ አይሁዳውያንን ሲያስጨፈጭፍ የነበረው ጆሴፍ ጎብልስ እና በሶቪየት ህብረት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ለብዙ ዜጎች እልቂት መንስኤ የነበረው ሌቪሪየንቲ ብሪያ ተጠቃሽ ናቸው ።
እነዚህና መሰል አምባገነኖች ታዲያ በዘመናቸው ሰዎችን ለማይገባ ሞትና እንግልት በመዳረግ አቻ የሌላቸው ናቸው ። አብዛኛውን ጊዜ የሚጠቀሙትም ሰዎች ወደሞት እንዲሄዱ የሚያነሳሳና የሚገፋፋ ፕሮፓጋንዳ ነው ።ነገር ግን እነሱ ሌሎች ወደሞት እንዲሄዱና የነሱን ዕድሜ እንዲያራዝሙላቸው ያደርጋሉ እንጂ ራሳቸው ለመሞት ዝግጁ አይደሉም ።ለነሱ መግደል እንጂ መሞት ፈጽሞ አይታሰብም ።
እነሳዳም ሁሴን እና ሙአመር ጋዳፊ ያንን ሁሉ ሕዝብ ካስጨፈጨፉ በኋላ በዚያ መልኩ በአሳፋሪ ሁኔታ በቁጥጥር ስር የዋሉበትና የተገደሉበት መንገድም ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው ።
ለ17 ዓመታት በትጥቅ ትግል ወቅት በርካታ ወጣቶችን ሲያስፈጁ የነበሩትና ከዚያም በኋላ በ27 ዓመታት የመንግሥታዊ አስተዳደር ሥልጣናቸው አገር ሲመሩ የቆዩት የጁንታው አመራሮችም በነዚህ ጊዜያት ሁሉ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች የሕይወት መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ከፍተኛ ሥራ ሰርተዋል ።ከበርካቶች ሞት በስተጀርባም ስማቸው ይነሳል።
እነሱ ግን እስከመጨረሻዋ ሰዓት ድረስ የሕይወት መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ አይደሉም ።ለዚህ ደግሞ የሴራው አውራ ስብሃት ነጋ ትልቅ ምሳሌ ነው ።
አቶ ስብሃት ነጋ ህወሓትን ከመሰረቱ ጥቂት ታጋዮች ግንባር ቀደሙ ነው። በትጥቅ ትግሉ የመጀመሪያ ጊዜያትም ድርጅቱን ከፊት ሲመራ ቆይቷል ።ድርጅቱ ባሳለፋቸው የ17 ዓመታት የትግል ወቅቶችም ይህ ሰው ትልቅ ሚና ነበረው። በተለይ በድርጅቱ ውስጥ ለተፈፀሙት ልዩ ልዩ ሴራዎችና ለተሰዉ ንፁሃን ዜጎች ይህ ሰው በቀጥታ እጁ እንዳለበት በተደጋጋሚ ይነሳል ። የትግሉ አንድ አካል የነበሩት አቶ ገብሩ አስራት ከዓመታት በፊት በፃፉት መጽሐፋቸው ላይ እንደጠቀሱት ድርጅቱ በትጥቅ ትግሉ ወቅት የመብት ጥያቄ ያነሱ በርካታ አባሎቹን እየበላ የመጣ ነው።
በዚህ ውስጥ ደግሞ ይህ ሰው ግንባር ቀደም ሚና ነበረው ።ከዚህም በተጨማሪ ኢዲዩን የመሳሰሉ ድርጅቶችን በሴራ በማጥፋትና መሪዎቻቸውን በግፍ በማስገደል እንዲገደሉ በማድረግ ለተሰራው ግፍ የዚህ ሰው እጅ ረጅም እንደነበር ገልፀዋል፡፡
ከዚያ በኋላም ቢሆን በ27 ዓመታት የኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን አቶ ስብሃት ነጋ እጅ የማይፈነቅለው ድንጋይ የማይሰራው ሃጢያት እንዳልነበር ብዙዎች የሚመሰክሩት ሃቅ ነው።
ለአብነትም በ1993 በህወሓት ውስጥ በተፈጠረው ልዩነት ውስጥ አቶ ስብሃት ነጋ የሴራው አካል በመሆንና አምባገነንነት ይበልጥ ስር እንዲሰድ በማድረግ ያበረከተው አስተዋጽኦ ቀላል አልነበረም፡፡
ቀንደኞቹ የህወሓት ጁንታ አመራሮች ላለፉት 46 ዓመታት ከወጣቱ ጀርባ አልጠፉም ።በነዚህ ጊዜያት ሁሉ ጥይት የሚመታው ከነሱ ፊት ያሉትን ንፁሃን ዜጎች እንጂ እነሱን አይደለም።
በነዚያ የደርግ የትግል ዘመናትም የትግራይ ሕዝብ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ልጆቹን ለጦርነት ሲገብር እነዚህ የጁንታ አመራሮች ከኋላ ሆነው ሌላውን ለጦርነት ከመማገድ በዘለለ አንዳችም ጭረት አልገጠማቸውም ።
እነዚህ የጁንታው አመራሮች በ27 ዓመታት የሥልጣን ዘመናቸው ያገኙትን ሁሉ ለእኔ በሚል ስግብግብ ስሜት ከታገሉለት ዓላማ ውጪ በዘረፋና በግድያ የኖሩ ናቸው ።የማይጠረቃው ሆዳቸው እና ለግፍ የማይቦዝነው እጃቸው ማብቂያ በሌለው ዘረፋና ግድያ ተሰማርቶ እንታገልልሃለን ያሉትን ሕዝብ ጭምር ሲያስከፉና ሲረግጡ ኖሩ። ነገር ግን የግፍ ጊዜው ሲደርስ እነሱ በተራቸው ፅዋቸው ሞልቶ ፈሰሰ።
እነዚህ የጁንታው አመራሮች ከ46 ዓመታት በኋላም ሞትን እንደሸሹ ናቸው ።ዛሬ ግን ትናንት አይደለምና በሕዝብ ውስጥ መደበቅ አይቻልም ።ምክንያቱም ትናንት በደል ያንገበገበው ሕዝብ ከጎናቸው ሆኖ ወደሥልጣን ቢያወጣቸውም ሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላ የሰሩት ግፍና መከራ ግን አጋልጦ እንዲሰጣቸው እያደረጋቸው ነው።
እነሆ የአምባገነኖች መጨረሻም ተይዞ ለፍርድ መቅረብ ነው ።
አዲስ ዘመን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም
አባይ ወልዱ እና ዶ/ር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገቡ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)

አባይ ወልዱ እና ዶ/ር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ በቁጥጥር ስር ዋነኛ የጁንታው አመራሮች የነበሩ በቁጥጥር ስር ውለው ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

አዲስ አበባ ከገቡትና አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ካደረጉ ከሀዲዎች ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል፦

የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበረው አቶ አባይ ወልዱ
እና ዶክተር አብርሃም ተከስተ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበረውን ጨምሮ ሌሎች የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች አዲስ አበባ ገብተዋል።

እነዚህ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌዴራል ፓሊስና ሌሎች የጸጥታ አካላት አማካኝነት ተይዘው አዲስ አበባ ገብተዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሜጀር ጄኔራል ኢብራሂም አብዱልጀሊል ቀደም ሲል የመከላከያ ሎጂስቲክ ሃላፊ የነበረና አሁን የጁንታው ሎጂስቲክ ሃላፊ የነበረ፣ ብርጋዴል ጄኔራል ገብረኪዳን ገብረማርያም የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ሃላፊ የነበረና በጡረታ ከተሰናበተ በኋላ ጁንታውን የተቀላቀለ፣ አስር ከፍተኛ መኮንኖች፣ ሁለት መስመራዊ መኮንኖች እና አንድ የክልሉ ረዳት ኮሚሽነር የነበረና ከፖሊስ ከድቶ ወደ ጁንታው የተቀላቀለ ላይ እርምጃ መወሰዱ መገለጹ ይታወሳል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን

በእጸገነት አክሊሉ
ሰበር ዜና ‼️
አባይ ወልዱ እና ዶ/ር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች አዲስ አበባ ገቡ
👉"ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው" የምስራቅ ዕዝ 25ኛ
ክፍለ ጦር 3ኛ ብርጌድ ሃላፊ
**************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አባይ ወልዱ እና ዶ/ር አብረሀም ተከስተን ጨምሮ ዋነኛ የጁንታው አመራሮች የነበሩ በቁጥጥር ስር ውለው ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።
አዲስ አበባ ከገቡትና አገርን ለመበታተን አቅደው በመከላከያ ሠራዊት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ካደረጉ አሸባሪዎችና ዋነኛ የጁንታው አመራሮች መካከል
አቶ አባይ ወልዱ የቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበረ
ዶክተር አብርሃም ተከስተ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበረ
ዶክተር ረዳኢ በርሄ የክልሉ ኦዲተር ሃላፊ የነበረ
ዶክተር ሙለታ ይርጋ የክልሉ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሃላፊ የነበረ
አቶ ዕቁባይ በርሄ- የሃይማኖት ጉዳይ ክትትል ሃላፊ የነበረ
አቶ ጌታቸው ተፈሪ የክልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤትና የሠላምና ደህንነት ሃላፊ የነበረ
ወይዘሮ ኪሮስ ሃጎስ የክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ የነበረች
ንጋቱ አንገሶም
አምደማርያም ተሰማ
እነዚህ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌዴራል ፓሊስና ሌሎች የጸጥታ አካላት አማካኝነት ተይዘው አዲስ አበባ ገብተዋል።
በተመሳሳይ እነዚህን የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች "ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው" ሲሉ የምስራቅ ዕዝ 25ኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ብርጌድ ሃላፊ መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ ተናግረዋል።
አሁን አዲስ አበባ የገቡትን ከፍተኛ የጁንታው አመራሮች በቁጥጥር ስር ለማዋል የትግራይ ህዝብ መረጃ በመስጠትና መንገድ በመምራት ከፍተኛ ትብብር በማድረጉ መቶ አለቃ ስዩም አመስግነዋል።
በእጸገነት አክሊሉ