ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተገለጸ
- በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸው ተገለፀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸውን የመከላከያ ሐይል ሥምሪት መምሪያ ሐላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው አስታወቁ።
በውጭ የሚገኙ የጁንታው ሚዲያዎች የሐሰት ኘሮፓጋንዳ ቢያናፍሱም፣ የመከላከያ ሐይልና ፌዴራል ፓሊስ በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ፣ በርካቶች መማረካቸው ተገልጿል። እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑትም ተደምስሰዋል ብለዋል።
የተቀሩትም በየእምነት ተቋማትና ገዳማት፣ ዋሻና ሸለቆዎች እራሳቸውን ደብቀው እንደሚገኙ መረጃ እንዳላቸው የገለፁት ጄኔራሉ፣ ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል።
የጁንታ ሐይል ተደምስሷል፣ በየሸለቆው የደበቃቸው የህዝብና የመንግስት ንብረት ተይዟል ያሉት ሐላፊው በአንዳንድ አካላት ከውጭ የሚነዛው ኘሮፖጋንዳ ፍፁም ሐሳት መሆኑን አስረድተዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።
- በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸው ተገለፀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸውን የመከላከያ ሐይል ሥምሪት መምሪያ ሐላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው አስታወቁ።
በውጭ የሚገኙ የጁንታው ሚዲያዎች የሐሰት ኘሮፓጋንዳ ቢያናፍሱም፣ የመከላከያ ሐይልና ፌዴራል ፓሊስ በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ፣ በርካቶች መማረካቸው ተገልጿል። እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑትም ተደምስሰዋል ብለዋል።
የተቀሩትም በየእምነት ተቋማትና ገዳማት፣ ዋሻና ሸለቆዎች እራሳቸውን ደብቀው እንደሚገኙ መረጃ እንዳላቸው የገለፁት ጄኔራሉ፣ ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል።
የጁንታ ሐይል ተደምስሷል፣ በየሸለቆው የደበቃቸው የህዝብና የመንግስት ንብረት ተይዟል ያሉት ሐላፊው በአንዳንድ አካላት ከውጭ የሚነዛው ኘሮፖጋንዳ ፍፁም ሐሳት መሆኑን አስረድተዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ"
- አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ
የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር
(ኢ ፕ ድ)
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ እንደሚችሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ገለፁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ከሶማሌ ክልል ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲ በፍትህ ተቋማት፣በዲሞክራሲ ግንባታና በሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ጥሩ ስራዎች ቢሰሩም መሻሻል ያለባቸው ስራዎች እንዳሉም ጠቅሰው እንደ ክልል በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሩ ጤናማና ህዝብንና መንግስትን በተሻለ መንገድ ያቀራረበ መሆኑን ገልፀዋል ።
የክልሉ የለውጥ አመራር በሐሳብ ብዝሐነትና ልዕልና የሚያምን የዜጎችን የመናገር ነፃነት የሚያከብር ነው ያሉት አቶ ህዝብም የተሰማውን በሰለጠነ መንገድ መንግስትን የመጠየቅ የዲሞክራሲ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና የክልሉ መንግስትም የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ተግቶ ይሰራል ብለዋል።
ካለፉት አመታት የተሻለ የፖለቲካ ምህዳር መኖሩን ጠቅሰው ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ መንገድ ፣የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ ብለዋል ።
- አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ
የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር
(ኢ ፕ ድ)
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ እንደሚችሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ገለፁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ከሶማሌ ክልል ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲ በፍትህ ተቋማት፣በዲሞክራሲ ግንባታና በሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ጥሩ ስራዎች ቢሰሩም መሻሻል ያለባቸው ስራዎች እንዳሉም ጠቅሰው እንደ ክልል በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሩ ጤናማና ህዝብንና መንግስትን በተሻለ መንገድ ያቀራረበ መሆኑን ገልፀዋል ።
የክልሉ የለውጥ አመራር በሐሳብ ብዝሐነትና ልዕልና የሚያምን የዜጎችን የመናገር ነፃነት የሚያከብር ነው ያሉት አቶ ህዝብም የተሰማውን በሰለጠነ መንገድ መንግስትን የመጠየቅ የዲሞክራሲ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና የክልሉ መንግስትም የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ተግቶ ይሰራል ብለዋል።
ካለፉት አመታት የተሻለ የፖለቲካ ምህዳር መኖሩን ጠቅሰው ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ መንገድ ፣የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ ብለዋል ።
በአዳማ ከተማ የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር ተከፈተ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በአዳማ ከተማ በአባገዳ አዳራሽ ተከፈተ፡፡
በአውደ ርዕይና ባዛር ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልሉ አመራሮች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በአውደ ርዕይ እና ባዛሩ ላይም የተለያዩ የግብርና ምርቶችና ውጤቶች ቀርበዋል፡፡
የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ በአውደ ርዕይ እና ባዛር ላይ እንድገለጹት የፕሮግራሙ ዓላማ በግብርና ምርት ውጤቶችና ቴክኖሎጂዎች ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ ለዘርፉ ዕድገት ድጋፍ ላበረከቱ ምሁራን እና ባለሀብቶች ዕውቅና መስጠታቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በአዳማ ከተማ በአባገዳ አዳራሽ ተከፈተ፡፡
በአውደ ርዕይና ባዛር ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልሉ አመራሮች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በአውደ ርዕይ እና ባዛሩ ላይም የተለያዩ የግብርና ምርቶችና ውጤቶች ቀርበዋል፡፡
የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ በአውደ ርዕይ እና ባዛር ላይ እንድገለጹት የፕሮግራሙ ዓላማ በግብርና ምርት ውጤቶችና ቴክኖሎጂዎች ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ ለዘርፉ ዕድገት ድጋፍ ላበረከቱ ምሁራን እና ባለሀብቶች ዕውቅና መስጠታቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
“የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት የሱዳን መንግሥትና ህዝብ ፍላጎት አይደለም”አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመለከተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በግጭቱ ዙሪያ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር 100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም በሌሎችም የአፍሪካ አገራት እንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ባትገዛም ሱዳን በቅኝ ግዥዎች ስር ስለነበረች፣ ድንበሩ ምንም እንኳ ምልክቶች ቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ በትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ በሁለቱም አገሮች የድንበር አካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ ብለዋል፡፡
አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።
አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት ከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን ለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች መጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ግጭቱ የሱዳን ህዝብና መንግሥት ፍላጎት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ እንዳልደረሰ ገልጸዋል።
ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል።
ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ ከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ወደ ግጭት አንገባም” የሚሉ ድምፆች እየጨሩ መምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፣ ከበስተጀረባው ግን የተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ወዳዱ የሱዳን ህዝብ እና ባለስልጣናት ፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል።
አንዳንድ የሱዳን ወታደሮችና ሚሊሻዎች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው በመግባት የሰው ህይወት ማጥፋታቸውና ንብረት ማውደማቸውን አመልክተው፣ መንግሥትም ጸጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ችግሩ በድርድር እንዲፈታ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመለከተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በግጭቱ ዙሪያ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር 100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም በሌሎችም የአፍሪካ አገራት እንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ባትገዛም ሱዳን በቅኝ ግዥዎች ስር ስለነበረች፣ ድንበሩ ምንም እንኳ ምልክቶች ቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ በትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ በሁለቱም አገሮች የድንበር አካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ ብለዋል፡፡
አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።
አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት ከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን ለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች መጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ግጭቱ የሱዳን ህዝብና መንግሥት ፍላጎት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ እንዳልደረሰ ገልጸዋል።
ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል።
ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ ከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ወደ ግጭት አንገባም” የሚሉ ድምፆች እየጨሩ መምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፣ ከበስተጀረባው ግን የተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ወዳዱ የሱዳን ህዝብ እና ባለስልጣናት ፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል።
አንዳንድ የሱዳን ወታደሮችና ሚሊሻዎች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው በመግባት የሰው ህይወት ማጥፋታቸውና ንብረት ማውደማቸውን አመልክተው፣ መንግሥትም ጸጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ችግሩ በድርድር እንዲፈታ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ 311 ሺህ 421 ተማሪዎች ተመዝግበዋል
-500 ሺህ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል።
በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈታኞች ምዝገባና ውጤት ጥንቅር ዳይሬክተር አቶ ዩሴፍ አበራ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የአጠቃላይ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ከጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ ለመስጠት መርሐግብር ተይዟል።
በዚህ መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ መደረጉን ገልጸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።
ምዝገባው ከትግራይ ክልል እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በስተቀር በሁሉ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካሄዱን የገለጹት ኃላፊው፣ በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ካጋጠመው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዳልተቻለ አመልክተዋል።
በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ቀደም ሲል ምዝገባ የተጀምረ ቢሆንም ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ መቋረጡን አስታውሰው፤ በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስችል ሁኔታ ለመፍጠር እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
በትግራይ ክልል 80 ያህል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በመተከል ደግሞ እስከ 14 ትምህርት ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል፣ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ምዝገባ ከተደረገ ቁጥሩ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38751
-500 ሺህ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል።
በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈታኞች ምዝገባና ውጤት ጥንቅር ዳይሬክተር አቶ ዩሴፍ አበራ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የአጠቃላይ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ከጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ ለመስጠት መርሐግብር ተይዟል።
በዚህ መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ መደረጉን ገልጸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።
ምዝገባው ከትግራይ ክልል እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በስተቀር በሁሉ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካሄዱን የገለጹት ኃላፊው፣ በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ካጋጠመው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዳልተቻለ አመልክተዋል።
በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ቀደም ሲል ምዝገባ የተጀምረ ቢሆንም ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ መቋረጡን አስታውሰው፤ በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስችል ሁኔታ ለመፍጠር እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
በትግራይ ክልል 80 ያህል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በመተከል ደግሞ እስከ 14 ትምህርት ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል፣ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ምዝገባ ከተደረገ ቁጥሩ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38751
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በዛሬው ዕለት በበይነ-መረብ ስብሰባ አካሂደዋል
**************
- ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው ገልጻለች፤
- የሱዳን ወገን ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል፤
- የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው አስታውቋል
(ኢ.ፕ.ድ)
ስብሰባው በደቡብ አፍሪካ የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሰብሳቢነት ተካሂዷል።
ሚኒስትሮቹ የሕዳሴው ግድብ ድርድር በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ያደረጉ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሰየሟቸው ባለሙያዎች ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ ላይ በማተኮር ምክክር ተደርጓል፡፡
በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው እና በቀጣይ በሚካሄደው ድርድር ሰነዱን እንደግብዓት ለመጠቀም ፈቃደኛ መሆኗን ገልጣለች፡፡
የሱዳን ወገን በበኩሉ ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው እና በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት ባለሙያዎች ተጨማሪ ሚና ላይ ቢጋር በማጽደቅ ድርድሩን መቀጠል እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡
የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው ገልጧል፡፡
የሕዳሴው ግድብ ሙሌት እና ዓመታዊ አስተዳደርን የሚመለከተው ሰነድ ላይ የሚደረገው ድርድር በአመዛኙ መግባባት የተደረሰበት ቢሆንም፣ ወደፊት በዓባይ ተፋሰስ ላይ በሚገነቡ የውሃ ልማት ሥራዎች ጋር የሚኖረው ቁርኝት ዋነኛ የልዩነት ሃሳብ ነው፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ፍጆታ የሌለው የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደመሆኑ በግድቡ ላይ የሚደረሰው ስምምነት ይህንኑ ከግምት ያስገባ እና የተሟላ የውሃ ስምምነት በሌለበት እና ኢፍትሃዊ አጠቃቀም በሰፈነበት ተፋሰስ የኢትዮጵያን የመጠቀም መብት የሚያቅብ እንዲሆን ኢትዮጵያ አትፈቅድም፡፡
ይህን መሰረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ አሞላል እና ዓመታዊ አስተደዳር የሚመለከተውን ደንብ በጋራ ስምምነት ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ ናት፡፡
በዚህም መሰረት የስምምነት አማራጮችን ለግብጽ እና ሱዳን ወገን ያቀረበች ሲሆን የሃገራቱ ምላሽ ቀና እንደሚሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡
በቀጣይ የሃገራቱ ባለሙያዎች በውሃ ሚኒስትሮች አመራር ስር ስብሰባቸውን በመቀጠል ስምምነት የተደረሰባቸውን እና የልዩነት ሃሳቦችን በመለየት በቀጣይ ዕሁድ ጥር 01 ቀን 2013 ለሚካሄደው የስድስት ሚኒስትሮች ስብሰባ ውጤቱን ያቀርባሉ፡፡
**************
- ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው ገልጻለች፤
- የሱዳን ወገን ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል፤
- የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው አስታውቋል
(ኢ.ፕ.ድ)
ስብሰባው በደቡብ አፍሪካ የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሰብሳቢነት ተካሂዷል።
ሚኒስትሮቹ የሕዳሴው ግድብ ድርድር በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ያደረጉ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሰየሟቸው ባለሙያዎች ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ ላይ በማተኮር ምክክር ተደርጓል፡፡
በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው እና በቀጣይ በሚካሄደው ድርድር ሰነዱን እንደግብዓት ለመጠቀም ፈቃደኛ መሆኗን ገልጣለች፡፡
የሱዳን ወገን በበኩሉ ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው እና በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት ባለሙያዎች ተጨማሪ ሚና ላይ ቢጋር በማጽደቅ ድርድሩን መቀጠል እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡
የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው ገልጧል፡፡
የሕዳሴው ግድብ ሙሌት እና ዓመታዊ አስተዳደርን የሚመለከተው ሰነድ ላይ የሚደረገው ድርድር በአመዛኙ መግባባት የተደረሰበት ቢሆንም፣ ወደፊት በዓባይ ተፋሰስ ላይ በሚገነቡ የውሃ ልማት ሥራዎች ጋር የሚኖረው ቁርኝት ዋነኛ የልዩነት ሃሳብ ነው፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ፍጆታ የሌለው የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደመሆኑ በግድቡ ላይ የሚደረሰው ስምምነት ይህንኑ ከግምት ያስገባ እና የተሟላ የውሃ ስምምነት በሌለበት እና ኢፍትሃዊ አጠቃቀም በሰፈነበት ተፋሰስ የኢትዮጵያን የመጠቀም መብት የሚያቅብ እንዲሆን ኢትዮጵያ አትፈቅድም፡፡
ይህን መሰረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ አሞላል እና ዓመታዊ አስተደዳር የሚመለከተውን ደንብ በጋራ ስምምነት ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ ናት፡፡
በዚህም መሰረት የስምምነት አማራጮችን ለግብጽ እና ሱዳን ወገን ያቀረበች ሲሆን የሃገራቱ ምላሽ ቀና እንደሚሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡
በቀጣይ የሃገራቱ ባለሙያዎች በውሃ ሚኒስትሮች አመራር ስር ስብሰባቸውን በመቀጠል ስምምነት የተደረሰባቸውን እና የልዩነት ሃሳቦችን በመለየት በቀጣይ ዕሁድ ጥር 01 ቀን 2013 ለሚካሄደው የስድስት ሚኒስትሮች ስብሰባ ውጤቱን ያቀርባሉ፡፡
በቡሬ ከተማ የተቋቋመው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩ ተገለጸ
********************************
(ኢ ፕ ድ)
በቡሬ ከተማ የተቋቋመውንና ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል በቡሬ ከተማ የተቋቋመውን የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ምርት ለማምረት ላበቁት አካላት በትዊተር ገጻቸው ምስጋና አቅርበዋል::
በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ለተገነባው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ስኬታማነት አስተዋጽዖ ለነበራቸውና ፕሮጀክቱ ሥራ እንዲጀምር ጥረት ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል” ብለዋል፡፡
የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን አቶ መላኩ በትዊተር ገጻቸው ጠቅሰዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከዚህ በፊትም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር ለገበያ እንደሚያቀርብ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
በቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሪችላንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው የአኩሪ አተር ፕሮቲንና የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ወደ ሙከራ ምርት መግባቱን ገልጸው ነበር፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባም 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት ለሀገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል።
ለውጪ ገበያ ከሚያቀርበው የምግብ ዘይትም 61 ሚሊዮን 680 ሺህ ዶላር እንደሚያስገኝ ሚኒስትሩ መናገራቸው አብመድ ዘግቧል፡፡
********************************
(ኢ ፕ ድ)
በቡሬ ከተማ የተቋቋመውንና ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል በቡሬ ከተማ የተቋቋመውን የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ምርት ለማምረት ላበቁት አካላት በትዊተር ገጻቸው ምስጋና አቅርበዋል::
በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ለተገነባው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ስኬታማነት አስተዋጽዖ ለነበራቸውና ፕሮጀክቱ ሥራ እንዲጀምር ጥረት ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል” ብለዋል፡፡
የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን አቶ መላኩ በትዊተር ገጻቸው ጠቅሰዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከዚህ በፊትም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር ለገበያ እንደሚያቀርብ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
በቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሪችላንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው የአኩሪ አተር ፕሮቲንና የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ወደ ሙከራ ምርት መግባቱን ገልጸው ነበር፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባም 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት ለሀገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል።
ለውጪ ገበያ ከሚያቀርበው የምግብ ዘይትም 61 ሚሊዮን 680 ሺህ ዶላር እንደሚያስገኝ ሚኒስትሩ መናገራቸው አብመድ ዘግቧል፡፡
“አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሠረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ ነው” አቶ ጊደና መድህን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ
******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሰረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አስታወቁ።
ዋና ፀሐፊው አቶ ጊደና መድህን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም ማህበራዊ መሰረታችን ትግራይ ላይ የሆንን ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ታስረናል። ተመርዘናል። ተገርፈናል፤ አሁን ግን ኑ ሃሳብ አላችሁ ተብለን ወደ ሥራ ገብተናል። እኔ እንኳን በሙያዬ ክልሉን እንዳገለግል የውሃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በመሆን ተሹሜያለሁ።
አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉንም ሃሳብ ያላቸውን የክልሉን ተወላጆች ወደ አመራርነት በማምጣት ፣ በሌላም መንገድ በልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን እንዲሳተፉ በማስቻል በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ውስጥ የተለየ ሃሳብ ያለው የሚታሰርበት ፣የሚገረፍበት እና የሚገደልበት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጊደና ፤ አሁን ግን ጊዜያዊ አስተዳደሩ ህዝቡ ችግር ውስጥ ነው ታስፈልጉታላችሁ፤ የዴሞክራሲ ምህዳሩንም እናሰፋለን በማለት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ላይ እንድንገባ ተደርጓል። ይህ ደግሞ ለትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን ለመላ አገሪቱ ትልቅ እመርታ ነው ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38804
******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሰረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አስታወቁ።
ዋና ፀሐፊው አቶ ጊደና መድህን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም ማህበራዊ መሰረታችን ትግራይ ላይ የሆንን ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ታስረናል። ተመርዘናል። ተገርፈናል፤ አሁን ግን ኑ ሃሳብ አላችሁ ተብለን ወደ ሥራ ገብተናል። እኔ እንኳን በሙያዬ ክልሉን እንዳገለግል የውሃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በመሆን ተሹሜያለሁ።
አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉንም ሃሳብ ያላቸውን የክልሉን ተወላጆች ወደ አመራርነት በማምጣት ፣ በሌላም መንገድ በልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን እንዲሳተፉ በማስቻል በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ውስጥ የተለየ ሃሳብ ያለው የሚታሰርበት ፣የሚገረፍበት እና የሚገደልበት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጊደና ፤ አሁን ግን ጊዜያዊ አስተዳደሩ ህዝቡ ችግር ውስጥ ነው ታስፈልጉታላችሁ፤ የዴሞክራሲ ምህዳሩንም እናሰፋለን በማለት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ላይ እንድንገባ ተደርጓል። ይህ ደግሞ ለትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን ለመላ አገሪቱ ትልቅ እመርታ ነው ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38804
ዞኑ ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የመተከል ዞን ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የዞኑ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል ከመተከል ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሄዷል።
መንግስት ወንጀለኞችን አድኖ ለሀግ ለማቅረብ እያከናወነ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
የመተከል ዞን በርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ የሚኖሩበት ሲሆን በማህበረሰቡ ዘንድ መተሳሰብና አብሮነት መኖሩንም የሀገር ሽማግሌዎቹ አንስተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ጥቃት ፈጻሚዎቹ የጉሙዝን ብሔረሰብ የማይወክሉ ‘የተደራጁ ሽፍቶች’ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህ ሽፍቶች ችግሩ እንዳይከሰት ሲጥሩ በነበሩ የሀገር ሽማግሌዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንም ተናግረዋል።
በጉሙዝ ማህበረሰብ ግጭትን በመፍታት ረገድ ትልቅ ሚና ባላቸው እናቶች ላይ ጭምር ጉዳት ማድረሳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
በእርሻ ኢንቨስትመንት ስም በአካባቢው የተሰማሩ የጽንፈኛው የህወሃት ጁንታ አባላቶች ወጣቶችን ሰብስበው ለጥፋት ተልኮ ሲያሰለጥኑ እንደነበርም ነው የሀገር ሽማግሌዎቹ የተናገሩት።
ይህንን እያወቁ ምንም አይነት ምላሽ ያልሰጡ አመራሮች መኖራቸውንም አንስተዋል። በመሆኑም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቀዋል።
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የመተከል ዞን ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የዞኑ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል ከመተከል ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሄዷል።
መንግስት ወንጀለኞችን አድኖ ለሀግ ለማቅረብ እያከናወነ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
የመተከል ዞን በርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ የሚኖሩበት ሲሆን በማህበረሰቡ ዘንድ መተሳሰብና አብሮነት መኖሩንም የሀገር ሽማግሌዎቹ አንስተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ጥቃት ፈጻሚዎቹ የጉሙዝን ብሔረሰብ የማይወክሉ ‘የተደራጁ ሽፍቶች’ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህ ሽፍቶች ችግሩ እንዳይከሰት ሲጥሩ በነበሩ የሀገር ሽማግሌዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንም ተናግረዋል።
በጉሙዝ ማህበረሰብ ግጭትን በመፍታት ረገድ ትልቅ ሚና ባላቸው እናቶች ላይ ጭምር ጉዳት ማድረሳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
በእርሻ ኢንቨስትመንት ስም በአካባቢው የተሰማሩ የጽንፈኛው የህወሃት ጁንታ አባላቶች ወጣቶችን ሰብስበው ለጥፋት ተልኮ ሲያሰለጥኑ እንደነበርም ነው የሀገር ሽማግሌዎቹ የተናገሩት።
ይህንን እያወቁ ምንም አይነት ምላሽ ያልሰጡ አመራሮች መኖራቸውንም አንስተዋል። በመሆኑም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቀዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4ሺ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበረከተ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4 ሽህ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በዛሬው እለት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበርክቷል::
በስጦታ መርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም ታደሰ: የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌና ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እንዲሁም የሃይኖት ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል::
የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌ የስጦታ መርሐ ግብሩን በንግግር ሲከፍቱ በዛሬው እለትም የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ኑሮ ከሚመሩ ነዋሪዎች ጋር በዓሉን ለማክበር ታቅዶ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በተሰራው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሐብት በ12ቱም ወረዳዎች በማሰባሰብ ለ4500 ወገኖች ተደራሽ ተደርጏል ብልዋል::
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች : አመራሮች : በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና በበጎ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሐብቶች ለዚህ ስራ ስኬታማነት ለተረባረቡ ሁሉ አቶ አስፋው ምስጋና አቅርበዋል::
በተናጠል ተጉዘን ከሰራናቸው ብዙ ተግባራት ይልቅ ህብረትን ፈጥረን በምክክርና በጋራ የተረባረብንባቸው ጥቂት ስራዎች ፍሬያማ ነበሩ ያሉት አቶ አስፋው፤ ድህነትን ለመቅረፍም ችግረኞችን ከማገዝ ባሻገር ዘላቂ ኑሯቸውን ለማሻሻል የተነደፉ የመንግስት ፕሮግራሞችን በመተግበር ሃገርንም ወገንንም ወደ ለውጥ ምህዋር ውስጥ ማስገባትና ለምናልመው ብልፅግና መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል ነው ያሉት።
በዓሉን በደስታና በፍቅር ከማክበሩ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ለኮሮና ቫይረስ ትኩረት በመስጠትና የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ እንዲሁም ለተቸገሩ ስጦታ በማበርከት እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል::
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው አስተዳደሩ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገዝ ያሳየውን ውጤታማ ተግባር አድንቀው ለዚህ በጎ ስራ የተባበሩና ያስተባበሩ አካላትን አመስግነዋል::
በዓሉን አስመልክቶም በእለቱ ለ149 ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የገንዘብና የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርቷክል::
ከ40 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ታድሰው የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት ተመርቀው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች መሰል የስጦታ መርሐ ግብሮች እስከ በአሉ ዋዜማ ድረስ እንደሚቀጥል አስተዳደሩ አስታውቋል።
********************
(ኢ ፕ ድ)
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4 ሽህ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በዛሬው እለት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበርክቷል::
በስጦታ መርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም ታደሰ: የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌና ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እንዲሁም የሃይኖት ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል::
የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌ የስጦታ መርሐ ግብሩን በንግግር ሲከፍቱ በዛሬው እለትም የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ኑሮ ከሚመሩ ነዋሪዎች ጋር በዓሉን ለማክበር ታቅዶ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በተሰራው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሐብት በ12ቱም ወረዳዎች በማሰባሰብ ለ4500 ወገኖች ተደራሽ ተደርጏል ብልዋል::
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች : አመራሮች : በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና በበጎ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሐብቶች ለዚህ ስራ ስኬታማነት ለተረባረቡ ሁሉ አቶ አስፋው ምስጋና አቅርበዋል::
በተናጠል ተጉዘን ከሰራናቸው ብዙ ተግባራት ይልቅ ህብረትን ፈጥረን በምክክርና በጋራ የተረባረብንባቸው ጥቂት ስራዎች ፍሬያማ ነበሩ ያሉት አቶ አስፋው፤ ድህነትን ለመቅረፍም ችግረኞችን ከማገዝ ባሻገር ዘላቂ ኑሯቸውን ለማሻሻል የተነደፉ የመንግስት ፕሮግራሞችን በመተግበር ሃገርንም ወገንንም ወደ ለውጥ ምህዋር ውስጥ ማስገባትና ለምናልመው ብልፅግና መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል ነው ያሉት።
በዓሉን በደስታና በፍቅር ከማክበሩ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ለኮሮና ቫይረስ ትኩረት በመስጠትና የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ እንዲሁም ለተቸገሩ ስጦታ በማበርከት እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል::
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው አስተዳደሩ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገዝ ያሳየውን ውጤታማ ተግባር አድንቀው ለዚህ በጎ ስራ የተባበሩና ያስተባበሩ አካላትን አመስግነዋል::
በዓሉን አስመልክቶም በእለቱ ለ149 ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የገንዘብና የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርቷክል::
ከ40 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ታድሰው የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት ተመርቀው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች መሰል የስጦታ መርሐ ግብሮች እስከ በአሉ ዋዜማ ድረስ እንደሚቀጥል አስተዳደሩ አስታውቋል።
“አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም”አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል እንደማያስኬድ ዓለምአቀፍ ሕግም እንደማይፈቅድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ።
አምባሳደር ዲና የሳምንቱን አበይት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የዲፕሎማቲክ ክንውኖች አስመል ክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የታላቁን ህዳሴ ግድብ አስመልክተው ፣አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም። ዓለምአቀፍ ሕጉም አይፈቅድም። እንዲህ አይነት ነገሮች ላይ ልዩነቶች አሉ ብለዋል።
የታችኛው ተፋሰስ አገራት በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚያሳዩት የእግር መጎተት ግድቡ ስለሚጎዳቸው ሳይሆን ግድቡን የማስተጓጎል ወይም የማስቆም ዓላማ ስላላቸው እንደሆነም አስታወቀዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከአንድ ወር መቋረጥ በኋላ ባለፈው እሁድ በሶስቱ አገራት የውጭ ጉዳይና የውሃ ሚኒስትሮች አማካኝነት ዳግም መጀመሩን ከሳምንቱ አበይት ዲፕሎማሲያዊ ክንውኖች መካከል አንዱ እንደ ነበርም ጠቁመዋል።
በድርድሩ በደቡብ አፍሪካ አስተባባሪነት በአፍሪካ ኅብረት በተሰየሙ የባለሙያዎች ቡድን የቀረበውን የድርድር ሰነድ ኢትዮጵያና ሱዳን ሲቀበሉት ግብፅ እንዳልተቀበለችው አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38957
**************************
(ኢ ፕ ድ)
አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል እንደማያስኬድ ዓለምአቀፍ ሕግም እንደማይፈቅድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ።
አምባሳደር ዲና የሳምንቱን አበይት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የዲፕሎማቲክ ክንውኖች አስመል ክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የታላቁን ህዳሴ ግድብ አስመልክተው ፣አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም። ዓለምአቀፍ ሕጉም አይፈቅድም። እንዲህ አይነት ነገሮች ላይ ልዩነቶች አሉ ብለዋል።
የታችኛው ተፋሰስ አገራት በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚያሳዩት የእግር መጎተት ግድቡ ስለሚጎዳቸው ሳይሆን ግድቡን የማስተጓጎል ወይም የማስቆም ዓላማ ስላላቸው እንደሆነም አስታወቀዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከአንድ ወር መቋረጥ በኋላ ባለፈው እሁድ በሶስቱ አገራት የውጭ ጉዳይና የውሃ ሚኒስትሮች አማካኝነት ዳግም መጀመሩን ከሳምንቱ አበይት ዲፕሎማሲያዊ ክንውኖች መካከል አንዱ እንደ ነበርም ጠቁመዋል።
በድርድሩ በደቡብ አፍሪካ አስተባባሪነት በአፍሪካ ኅብረት በተሰየሙ የባለሙያዎች ቡድን የቀረበውን የድርድር ሰነድ ኢትዮጵያና ሱዳን ሲቀበሉት ግብፅ እንዳልተቀበለችው አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38957
የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
******************************
(ኢ ፕ ድ)
የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡
ባንኩ በመግለጫው እንዳስታወቀወ አዲስ የብር ኖት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማሳተም ሥራ ላይ አውሏል። ከመስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በመላ አገሪቱ የብር ኖት ቅያሪ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡
በመሆኑም፣ የብር ኖቱ ረጅም ጊዜ እንዲያገለግል በማስብ፡
1) በብር ኖቱ ላይ መፃፍ፣ መቅደድና በቀለም ማበላሸት፣ የትኛውንም ዓይነት ጉዳት ማድረስና ምልክቶቹን ያለፈቃድ ማባዛት የተከለከለና በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን፣
2)ለማስታወቂያ ሥራ ከተፈለገ ግን ለማባዛት የባንኩን ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን፣
3) በጣም የተጎዱ የብር ኖቶች ሲያጋጥሙ ከዝውውር ስለሚወጡበት ሁኔታ ዝርዝር መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
******************************
(ኢ ፕ ድ)
የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡
ባንኩ በመግለጫው እንዳስታወቀወ አዲስ የብር ኖት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማሳተም ሥራ ላይ አውሏል። ከመስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በመላ አገሪቱ የብር ኖት ቅያሪ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡
በመሆኑም፣ የብር ኖቱ ረጅም ጊዜ እንዲያገለግል በማስብ፡
1) በብር ኖቱ ላይ መፃፍ፣ መቅደድና በቀለም ማበላሸት፣ የትኛውንም ዓይነት ጉዳት ማድረስና ምልክቶቹን ያለፈቃድ ማባዛት የተከለከለና በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን፣
2)ለማስታወቂያ ሥራ ከተፈለገ ግን ለማባዛት የባንኩን ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን፣
3) በጣም የተጎዱ የብር ኖቶች ሲያጋጥሙ ከዝውውር ስለሚወጡበት ሁኔታ ዝርዝር መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን የገና በዓልን አስመልክተው ለክርስትና እምነት ተከታዮች የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላለፉ
*******************^
(ኢ.ፕ.ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የገና በዓልን አስመልክተው ለክርስትና እምነት ተከታዮች የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡
"በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የገና በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ" ሲሉ ነው አቶ ደመቀ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት የበአል መልዕክት ምኞታቸውን የገለጹት።
*******************^
(ኢ.ፕ.ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የገና በዓልን አስመልክተው ለክርስትና እምነት ተከታዮች የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል፡፡
"በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የገና በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ" ሲሉ ነው አቶ ደመቀ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት የበአል መልዕክት ምኞታቸውን የገለጹት።
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በቃሊቲ ጊዜያዊ ማቆያ ከሚገኙ ከጎዳና ከተነሱ ዜጎች ጋር የገና በዓልን አከበሩ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ጋር በመሆ ን በቃሊቲ ጊዜያዊ ማቆያ ከሚገኙ ከጎዳና ከተነሱ ዜጎች ጋር ማዕድ በማጋራት የገና በዓልን አክብረዋል።
በመርሐግብሩ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በተያዘዉ በጀት ዓመት 8 ሺህ 286 በጎዳና ይኖሩ የነበሩ ዜጎችን በማንሳት የሙያ ክህሎት እና የስነ-ልቦና ስልጠናዎች ተሰጥቷል።
በዚህም እስካሁን በሰባት ክፍለ ከተሞች እና በአቃቂ ጊዜያዊ ማቆሚያ ማዕከል 3 ሺህ 966 የሚሆኑት ወጣቶች ተገቢዉን የሙያ እና የስነ-ልቦና ስልጠና አጠናቀው በደረቅ ቆሻሻ፣ አረንጓዴ ልማት እና መንገድ ጥርጊያ ላይ የስራ እድል ለመፍጠር ወደ ተግባር መገባቱን ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል።
ጎዳና ጊዜያዊ የህይወት ማቆያችሁ ሆኖ ቆይቷል ያሉት ምክትል ከንቲባዋ አሁን ያ ጊዜ አልፎ በሌላ የህይወት ምዕራፍ ላይ ተገኝታችኋል ብለዋል።
አያይዘውም ፈተና ለእናንተ አዲስ አይደለም፤ በጎዳናም ብዙ ፈተና አልፋችሁ መጥታችኋል፤ ስለሆነም የወሰዳችሁትን ስልጠና ወደ ተግባር ቀይራችሁ ወደ ስራ አለም ስትገቡ ለሚገጥማችሁ ፈተና እጅ ሳትሰጡ ራሳችሁንና ሀገራችሁን እንድትለውጡ ሲሉ ወ/ሮ አዳነች የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በማዕከሉ የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ ላይ የሚገኙ ወጣቶች በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ከአስከፊው የጎዳና ህይወት አንስቶ የህይወት ክህሎት ስልጠና በመሰጠት የስራ እድል ስለተፈጠረላቸው አመስግነዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም በአቃቂ ክፍለ ከተማ ለሚገኘው የአረጋውያን መርጃ ማዕከል ለገና በዓል ማክበሪያ የሚሆን የዕርድ ሰንጋ በስጦታ ማበርከቱን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬተሪ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ጋር በመሆ ን በቃሊቲ ጊዜያዊ ማቆያ ከሚገኙ ከጎዳና ከተነሱ ዜጎች ጋር ማዕድ በማጋራት የገና በዓልን አክብረዋል።
በመርሐግብሩ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በተያዘዉ በጀት ዓመት 8 ሺህ 286 በጎዳና ይኖሩ የነበሩ ዜጎችን በማንሳት የሙያ ክህሎት እና የስነ-ልቦና ስልጠናዎች ተሰጥቷል።
በዚህም እስካሁን በሰባት ክፍለ ከተሞች እና በአቃቂ ጊዜያዊ ማቆሚያ ማዕከል 3 ሺህ 966 የሚሆኑት ወጣቶች ተገቢዉን የሙያ እና የስነ-ልቦና ስልጠና አጠናቀው በደረቅ ቆሻሻ፣ አረንጓዴ ልማት እና መንገድ ጥርጊያ ላይ የስራ እድል ለመፍጠር ወደ ተግባር መገባቱን ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል።
ጎዳና ጊዜያዊ የህይወት ማቆያችሁ ሆኖ ቆይቷል ያሉት ምክትል ከንቲባዋ አሁን ያ ጊዜ አልፎ በሌላ የህይወት ምዕራፍ ላይ ተገኝታችኋል ብለዋል።
አያይዘውም ፈተና ለእናንተ አዲስ አይደለም፤ በጎዳናም ብዙ ፈተና አልፋችሁ መጥታችኋል፤ ስለሆነም የወሰዳችሁትን ስልጠና ወደ ተግባር ቀይራችሁ ወደ ስራ አለም ስትገቡ ለሚገጥማችሁ ፈተና እጅ ሳትሰጡ ራሳችሁንና ሀገራችሁን እንድትለውጡ ሲሉ ወ/ሮ አዳነች የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በማዕከሉ የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ ላይ የሚገኙ ወጣቶች በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ከአስከፊው የጎዳና ህይወት አንስቶ የህይወት ክህሎት ስልጠና በመሰጠት የስራ እድል ስለተፈጠረላቸው አመስግነዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም በአቃቂ ክፍለ ከተማ ለሚገኘው የአረጋውያን መርጃ ማዕከል ለገና በዓል ማክበሪያ የሚሆን የዕርድ ሰንጋ በስጦታ ማበርከቱን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬተሪ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የጀግኖች አምባ እና ህፃናት አምባ በተጠናከረ መልኩ እንዲቋቋሙ ይደረጋል - ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ
- የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የአገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ከጦር አካል ጉዳተኞች ጋር የገና በአልን አከበሩ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የጀግኖች አምባ እና ህፃናት አምባ በተጠናከረ መልኩ እንዲቋቋሙ የሚደረግ መሆኑን የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ አስታወቁ፡፡
የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የአገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ከጦር አካል ጉዳተኞች ጋር የገና በአልን አክብረዋል።
የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ "የጦር ጉዳተኞቹ ለአገርና ለህዝብ ሲሉ ህይወታቸውንና አካላቸውን የሰጡ በመሆናቸው ልናከብራቸው ይገባል" ብለዋል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ዘላቂ እንክብካቤ ያገኙበትና በስሙ ይኮሩበት የነበረው ጀግኖች አምባ “ከኛ በፊት ጀግንነትም ጀግናም የለም” ይሉ በነበሩ ጽንፈኞች መዘጋቱን አስታውሰው፤ በቀጣይ የጀግኖች አምባ እና ህፃናት አምባ በተጠናከረ መንገድ እንደገና እንዲቋቋሙ የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የትናንቱን የጀግንነት ተግባር መካድ የዛሬን ጀግንነት መካድና ለነገም የማይጠቅም ፍፁም የተሳሳተ ድርጊት መሆኑንም ጠቅሰው፤ እነዚህ ተቋማት ከወደቁበት ተነስተው አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ገልጸዋል።
መንግሥት የአካል ጉዳተኞችን መብት፣ ክብር፣ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል፡፡
ሚኒስቴሩ የአካል ጉዳተኞችን እንዲሁም የጦር አካል ጉዳተኛ ጀግኖችን ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው "ጀግንነት የትውልድ ቅብብሎሽ በመሆኑ በዚሁ ሂደት ኢትዮጵያና ህዝቦቿ ተከብረው ዘልቀዋል" ብለዋል።
ለዚህ ክብር የጦር ጉዳተኞቹ ታላላቅ ጀብድ የሰሩና ለአገርና ለህዝብ ህይወታቸውንና አካላቸውን መስዋዕት ያደረጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
"በመሆኑም ከጦር ጉዳተኞች ጋር በዓል ማክበር ብቻ ሳይሆን ማዕከሉ ለትውልድ እንዲያገለግል ብዙዎች የሚማሩበትና የዜጎች ኩራት ሆኖ እንዲቀጥል ይደረጋል" ብለዋል።
በየመስኩ የትውልድ ጀግንነት እንደሚቀጥል አውስተው፤ "ጀግንነት ሊከበር፣ ሊወደስና ቦታ ሊሰጠው ይገባል" ብለዋል።
ምክትል ከንቲባዋ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተለገሱትን 30 በጎችም በእለቱ አስረክበዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ በደቡብ ሱዳን ቆንስላ ጽህፈት ቤት የሚገኙ አንድ ኢትዮጵያዊም ለማህበሩ 300 ሺህ ብር መለገሳቸውን በፕሮግራሙ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ እንዲሁም ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተገኝተዋል።
- የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የአገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ከጦር አካል ጉዳተኞች ጋር የገና በአልን አከበሩ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የጀግኖች አምባ እና ህፃናት አምባ በተጠናከረ መልኩ እንዲቋቋሙ የሚደረግ መሆኑን የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ አስታወቁ፡፡
የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የአገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ከጦር አካል ጉዳተኞች ጋር የገና በአልን አክብረዋል።
የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ "የጦር ጉዳተኞቹ ለአገርና ለህዝብ ሲሉ ህይወታቸውንና አካላቸውን የሰጡ በመሆናቸው ልናከብራቸው ይገባል" ብለዋል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ዘላቂ እንክብካቤ ያገኙበትና በስሙ ይኮሩበት የነበረው ጀግኖች አምባ “ከኛ በፊት ጀግንነትም ጀግናም የለም” ይሉ በነበሩ ጽንፈኞች መዘጋቱን አስታውሰው፤ በቀጣይ የጀግኖች አምባ እና ህፃናት አምባ በተጠናከረ መንገድ እንደገና እንዲቋቋሙ የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የትናንቱን የጀግንነት ተግባር መካድ የዛሬን ጀግንነት መካድና ለነገም የማይጠቅም ፍፁም የተሳሳተ ድርጊት መሆኑንም ጠቅሰው፤ እነዚህ ተቋማት ከወደቁበት ተነስተው አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ገልጸዋል።
መንግሥት የአካል ጉዳተኞችን መብት፣ ክብር፣ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል፡፡
ሚኒስቴሩ የአካል ጉዳተኞችን እንዲሁም የጦር አካል ጉዳተኛ ጀግኖችን ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው "ጀግንነት የትውልድ ቅብብሎሽ በመሆኑ በዚሁ ሂደት ኢትዮጵያና ህዝቦቿ ተከብረው ዘልቀዋል" ብለዋል።
ለዚህ ክብር የጦር ጉዳተኞቹ ታላላቅ ጀብድ የሰሩና ለአገርና ለህዝብ ህይወታቸውንና አካላቸውን መስዋዕት ያደረጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
"በመሆኑም ከጦር ጉዳተኞች ጋር በዓል ማክበር ብቻ ሳይሆን ማዕከሉ ለትውልድ እንዲያገለግል ብዙዎች የሚማሩበትና የዜጎች ኩራት ሆኖ እንዲቀጥል ይደረጋል" ብለዋል።
በየመስኩ የትውልድ ጀግንነት እንደሚቀጥል አውስተው፤ "ጀግንነት ሊከበር፣ ሊወደስና ቦታ ሊሰጠው ይገባል" ብለዋል።
ምክትል ከንቲባዋ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተለገሱትን 30 በጎችም በእለቱ አስረክበዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ በደቡብ ሱዳን ቆንስላ ጽህፈት ቤት የሚገኙ አንድ ኢትዮጵያዊም ለማህበሩ 300 ሺህ ብር መለገሳቸውን በፕሮግራሙ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ እንዲሁም ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተገኝተዋል።
የአሜሪካ ምክር ቤቶች የጆባይደንን የምርጫ ውጤት አረጋገጡ
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
የሁለቱ ምክር ቤት እንደራሴዎች የተሰጡትን የውክልና ድምጾች (ኤሌክቶራል ቮት) በመቁጠር ጆ ባይደን ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን አረጋግጧል።
ኮንግረስ ጆባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሀሪስን የቀጣዮቹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት በማድረግ ያገኙትን ድምጽ አጽድቋል።
የተሰጡት የውክልና ድምጾች የጸደቁት የሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች በፔንሰልቫንያ እና አሪዞና ግዛቶች የቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ካደረጉ በኋላ ነው ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
የሁለቱ ምክር ቤት እንደራሴዎች የተሰጡትን የውክልና ድምጾች (ኤሌክቶራል ቮት) በመቁጠር ጆ ባይደን ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን አረጋግጧል።
ኮንግረስ ጆባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሀሪስን የቀጣዮቹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት በማድረግ ያገኙትን ድምጽ አጽድቋል።
የተሰጡት የውክልና ድምጾች የጸደቁት የሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች በፔንሰልቫንያ እና አሪዞና ግዛቶች የቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ካደረጉ በኋላ ነው ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
በመተከል ዞን የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች በመተከል ዞን ህግ በማስከበር ስራ ላይ ለሚገኘው የፀጥታ ሃይል አባላት ሰንጋዎችን አበረከቱ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች በዞኑ ህግ በማስከበር ስራ ላይ ለሚገኘው የፀጥታ ሃይል አባላት ለገና በዓል 210 ሺህ ብር ወጪ የተደረገባቸው ስድስት የእርድ ሰንጋዎችን አበረከቱ።
በፌዴራል መንግስት የተቋቋመው ግብረ ሃይል በመተከል ዞን ፀረ ሰላም ሃይሎችን በማደንና በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
ግብረ ሃይሉ ከዞን እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በተንኮልና ሴራ ውስጥ የገቡ አመራሮችን የማጥራት፣ ህዝባዊ አንድነትን የማጠናከርና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን የመፍታት ስራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በአካባቢው በዜጎች ላይ ጥቃት በመፈፀም በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ሽፍቶችን በማደን ለህግ የማቅረብ ስራም በማከናወን ላይ ነው።
ግብረ ሃይሉ ባከናወነው ተግባር በርካታ አካባቢዎች ወደ ቀደመ ሰላማቸው እየተመለሱ ሲሆን ህዝባዊ የውይይት መድረኮችም በመካሄድ ላይ ናቸው።
በዚህም ደስተኞች ነን ሲሉ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በዞኑ ዳንጉር ወረዳ የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ ለፀጥታ ሃይሉ ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት የበዓል መዋያውን ማበርከታቸውን ገልጸዋል።
ግብረ ሃይሉ በአካባቢው ስላመጣው አንፃራዊ ሰላም ደስተኞች መሆናቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ ድጋፋቸው እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዳንጉር ወረዳ ህዝቡ ባደረገው ውይይት ህዝብን ከህዝብ የማጋጨትና ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲፈጸም ያደረጉ አካላት ተለይተው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቀዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ ማንኛውንም በዓል በጋራ የማክበርና የአብሮነት ልምድ እንዳለው የገለጹት የአካባቢቅው ሽማግሌዎች "የገና በዓልን በለመድነው አብሮነት እያከበርን ነው" ብለዋል።
ማህበረሰቡ የለገሰውን ስጦታ የተረከቡት ሻለቃ ፍቃዱ ጃፍራ ለተደረገው ድጋፍ ሁሉ በሰራዊቱ ስም አመስግነዋል።
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች በዞኑ ህግ በማስከበር ስራ ላይ ለሚገኘው የፀጥታ ሃይል አባላት ለገና በዓል 210 ሺህ ብር ወጪ የተደረገባቸው ስድስት የእርድ ሰንጋዎችን አበረከቱ።
በፌዴራል መንግስት የተቋቋመው ግብረ ሃይል በመተከል ዞን ፀረ ሰላም ሃይሎችን በማደንና በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
ግብረ ሃይሉ ከዞን እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በተንኮልና ሴራ ውስጥ የገቡ አመራሮችን የማጥራት፣ ህዝባዊ አንድነትን የማጠናከርና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን የመፍታት ስራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በአካባቢው በዜጎች ላይ ጥቃት በመፈፀም በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ሽፍቶችን በማደን ለህግ የማቅረብ ስራም በማከናወን ላይ ነው።
ግብረ ሃይሉ ባከናወነው ተግባር በርካታ አካባቢዎች ወደ ቀደመ ሰላማቸው እየተመለሱ ሲሆን ህዝባዊ የውይይት መድረኮችም በመካሄድ ላይ ናቸው።
በዚህም ደስተኞች ነን ሲሉ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በዞኑ ዳንጉር ወረዳ የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ ለፀጥታ ሃይሉ ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት የበዓል መዋያውን ማበርከታቸውን ገልጸዋል።
ግብረ ሃይሉ በአካባቢው ስላመጣው አንፃራዊ ሰላም ደስተኞች መሆናቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ ድጋፋቸው እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዳንጉር ወረዳ ህዝቡ ባደረገው ውይይት ህዝብን ከህዝብ የማጋጨትና ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲፈጸም ያደረጉ አካላት ተለይተው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቀዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ ማንኛውንም በዓል በጋራ የማክበርና የአብሮነት ልምድ እንዳለው የገለጹት የአካባቢቅው ሽማግሌዎች "የገና በዓልን በለመድነው አብሮነት እያከበርን ነው" ብለዋል።
ማህበረሰቡ የለገሰውን ስጦታ የተረከቡት ሻለቃ ፍቃዱ ጃፍራ ለተደረገው ድጋፍ ሁሉ በሰራዊቱ ስም አመስግነዋል።
"የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት እስካሁን ውጤታማ ሆኗል። ባገኘናቸው ውጤቶች ላይ፣ ፈጠራ የታከለባቸውን ጥረቶች በማከል ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሕልማችንን እውን እናደርጋለን"
-የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
-የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ