‹‹ቀድሞ በነበረው የበሰበሰ ርዕዮተ ዓለም መገለባበጥና መዋሸት የለመዱ አካላት እውነተኛ ፌዴራሊዝም እንዳይተገበር እንቅፋት እየሆኑ ነው›› አቶ አባተ ኪሾ የቀድሞው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
***************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢህአዴግ ዘመን በነበረው የበሰበሰ ርዕዮተ ዓለም መገለባበጥና መዋሸት የለመዱ አካላት እውነተኛ ፌዴራሊዝም እንዳይተገበር እንቅፋት እየሆኑ ነው ሲሉ የቀድሞ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ ገለጹ። እውነተኛ ፌዴራሊዝም ባለመኖሩ ለ30 ዓመታት ክልል ከክልል ብቻ ሳይሆን ቀበሌ ከቀበሌም እርስበእርስ እንዲጠራጠሩ ማድረጉንም አመልክተዋል።
አቶ አባተ ኪሾ፣ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚታየው ቀውስ እውነተኛ ፌዴራሊዝም ካለመተግበሩ ጋር ተያይዞ የመጣ ነው። አሁንም ትክክለኛ ፌዴራሊዝም እንዳይተገበር የሚያደርጉት ቀድሞ በነበረውና በበሰበሰው የኢህአዴግ ርዕዮተ ዓለም ውስጥ ሲገለባበጡና ሲዋሹ በነበሩ አካላት ናቸው።
ችግሩ ያለው በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በሌሎቹም የአገሪቱ ክፍሎች በመኖሩ ሊታዩና ሊፈተሹ የሚገባቸው ብዙ ናቸው ያሉት አቶ አባተ፣ በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለው የቀድሞውን የፖለቲካ ድፍድፍ በአግባቡ ሳይጠራ የጠጣ ኃይል እንዳለ ነው ብለዋል።
ያ ስካር እስካሁን ያለቀቀው እንዳለ ጠቁመው፣ ይህ ሃይል የሚሰራውን እንደማያውቅ አስታውቀዋል። የበሰበሰው ርዕዮተ ዓለም አሁንም ድረስ አገሪቱን በማመስ ላይ የሚገኘውም በዚሁ ምክንያት እንደሆነ አመልክተዋል።
የዚህ ርዕዮተ ዓለም ተከታዮችና የበሰበሰውን ሃሳብ ለማሳካት የሚንገታገቱ ቡድኖች በየቦታው መኖራቸውን የሚናገሩት አቶ አባተ፤ ስለዚህም መመልከት ያለብን አንድን አካባቢ ብቻ ሳይሆን በየአቅጣጫው ነው ብለዋል። የበሰበሰው ርዕዮተ ዓለም ቫይረሱ በብዙ ቦታ የተዳረሰ ከመሆኑ አኳያ ሁሉንም ቦታ በአግባቡ በመፈተሽ ቫይረሱን ማምከን የግድ እንደሚልም ተናግረዋል። ይህ ካልሆነ ግን የታለመው እውነተኛ ፌዴራሊዝም ተተግብሮ ማየት የማይቻል መሆኑን ገልጸዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38453
***************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢህአዴግ ዘመን በነበረው የበሰበሰ ርዕዮተ ዓለም መገለባበጥና መዋሸት የለመዱ አካላት እውነተኛ ፌዴራሊዝም እንዳይተገበር እንቅፋት እየሆኑ ነው ሲሉ የቀድሞ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ ገለጹ። እውነተኛ ፌዴራሊዝም ባለመኖሩ ለ30 ዓመታት ክልል ከክልል ብቻ ሳይሆን ቀበሌ ከቀበሌም እርስበእርስ እንዲጠራጠሩ ማድረጉንም አመልክተዋል።
አቶ አባተ ኪሾ፣ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚታየው ቀውስ እውነተኛ ፌዴራሊዝም ካለመተግበሩ ጋር ተያይዞ የመጣ ነው። አሁንም ትክክለኛ ፌዴራሊዝም እንዳይተገበር የሚያደርጉት ቀድሞ በነበረውና በበሰበሰው የኢህአዴግ ርዕዮተ ዓለም ውስጥ ሲገለባበጡና ሲዋሹ በነበሩ አካላት ናቸው።
ችግሩ ያለው በትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን በሌሎቹም የአገሪቱ ክፍሎች በመኖሩ ሊታዩና ሊፈተሹ የሚገባቸው ብዙ ናቸው ያሉት አቶ አባተ፣ በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለው የቀድሞውን የፖለቲካ ድፍድፍ በአግባቡ ሳይጠራ የጠጣ ኃይል እንዳለ ነው ብለዋል።
ያ ስካር እስካሁን ያለቀቀው እንዳለ ጠቁመው፣ ይህ ሃይል የሚሰራውን እንደማያውቅ አስታውቀዋል። የበሰበሰው ርዕዮተ ዓለም አሁንም ድረስ አገሪቱን በማመስ ላይ የሚገኘውም በዚሁ ምክንያት እንደሆነ አመልክተዋል።
የዚህ ርዕዮተ ዓለም ተከታዮችና የበሰበሰውን ሃሳብ ለማሳካት የሚንገታገቱ ቡድኖች በየቦታው መኖራቸውን የሚናገሩት አቶ አባተ፤ ስለዚህም መመልከት ያለብን አንድን አካባቢ ብቻ ሳይሆን በየአቅጣጫው ነው ብለዋል። የበሰበሰው ርዕዮተ ዓለም ቫይረሱ በብዙ ቦታ የተዳረሰ ከመሆኑ አኳያ ሁሉንም ቦታ በአግባቡ በመፈተሽ ቫይረሱን ማምከን የግድ እንደሚልም ተናግረዋል። ይህ ካልሆነ ግን የታለመው እውነተኛ ፌዴራሊዝም ተተግብሮ ማየት የማይቻል መሆኑን ገልጸዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38453
በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ በድጋሚ ተጀመረ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው ከ1ዐዐ ሺህ ብር በታች የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ ድጋሚ መጀመሩን ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።
ባንኩ እንዳስታወቀው፤ መንግስት በክልሉ በወሰደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ምክንያት የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬው ተቋርጦ እንደነበር አስታውሶ አሁን ላይ በተወሰኑ የክልሉ ከተሞች የመብራትና የኢንተርኔት አገልግሎት በመጀመሩ በእነዚሁ አካባቢዎች ባንኮች ሥራ እንዲጀምሩ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህ መሰረት ተቋርጦ የነበረውን የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ ባንኮች ሥራ ከጀመሩበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በ14 ቀናት ውስጥ አሮጌ ብር እንዲቀይሩ ከዛሬ ታህሳስ 21 ቀን 2ዐ13 ዓ.ም ጀምሮ መወሰኑንም ነው ባንኩ ያስታወቀው።
ባንኮችም ይህንኑ ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ እና ተግባራዊ እንዲያደርጉ በመጠቆም በብር መቀየሩ ሂደት የነበሩ መመሪያዎችና አሠራሮች እንደተጠበቁ መሆናቸውንም ገልጿል።
ከባንክ በጥሬ ገንዘብ የሚወጣው የገንዘብ መጠን ላይ በተሻሻለው መመሪያ ላይ በተቀመጠው መሠረት ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን ከ1ዐዐ ሺህ እስከ 1.5 ሚሊየን አሮጌ ብር ያላቸው የመቀየሪያው የጊዜ ገደብ የህግ ማስከበሩ ከመጀመሩ በፊት የተጠናቀቀ በመሆኑ ብር መቀየር የሚችሉት ከ1ዐዐ ሺህ ብር በታች ያላቸው መሆናቸውን ባንኩ አስታውቋል።
ባንኮችም ይህንኑ ሥራ የሚከታተል ግብረ ኃይል በማቋቋም መመሪያን በጠበቀ መልኩ እንዲሠሩ እና በእያንዳንዱ የባንክ ቅርንጫፍ የብር መቀየር ሥራ የተጀመረበትንና የተጠናቀቀበት ቀን እና የተለወጠ የብር መጠን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሳምንቱ ሪፖርት እንዲያደርጉም አሳስቧል።
ከመስከረም 6 ቀን 2ዐ13 ዓ.ም. ጀምሮ ለሶስት ወራት በመላ ሀገሪቱ አሮጌ ብር በአዲስ ብር የመቀየር ሥራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል።
በትግራይ ክልል ባንኮች ስራ ከጀመሩበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በ14 ቀናት ውስጥ አሮጌ ብርን እንዲቀይሩ ከዛሬ ታህሳስ 21 ቀን ጀምሮ መወሰኑን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
**************************
(ኢ ፕ ድ)
በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው ከ1ዐዐ ሺህ ብር በታች የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ ድጋሚ መጀመሩን ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።
ባንኩ እንዳስታወቀው፤ መንግስት በክልሉ በወሰደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ምክንያት የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬው ተቋርጦ እንደነበር አስታውሶ አሁን ላይ በተወሰኑ የክልሉ ከተሞች የመብራትና የኢንተርኔት አገልግሎት በመጀመሩ በእነዚሁ አካባቢዎች ባንኮች ሥራ እንዲጀምሩ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህ መሰረት ተቋርጦ የነበረውን የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ ባንኮች ሥራ ከጀመሩበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በ14 ቀናት ውስጥ አሮጌ ብር እንዲቀይሩ ከዛሬ ታህሳስ 21 ቀን 2ዐ13 ዓ.ም ጀምሮ መወሰኑንም ነው ባንኩ ያስታወቀው።
ባንኮችም ይህንኑ ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ እና ተግባራዊ እንዲያደርጉ በመጠቆም በብር መቀየሩ ሂደት የነበሩ መመሪያዎችና አሠራሮች እንደተጠበቁ መሆናቸውንም ገልጿል።
ከባንክ በጥሬ ገንዘብ የሚወጣው የገንዘብ መጠን ላይ በተሻሻለው መመሪያ ላይ በተቀመጠው መሠረት ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን ከ1ዐዐ ሺህ እስከ 1.5 ሚሊየን አሮጌ ብር ያላቸው የመቀየሪያው የጊዜ ገደብ የህግ ማስከበሩ ከመጀመሩ በፊት የተጠናቀቀ በመሆኑ ብር መቀየር የሚችሉት ከ1ዐዐ ሺህ ብር በታች ያላቸው መሆናቸውን ባንኩ አስታውቋል።
ባንኮችም ይህንኑ ሥራ የሚከታተል ግብረ ኃይል በማቋቋም መመሪያን በጠበቀ መልኩ እንዲሠሩ እና በእያንዳንዱ የባንክ ቅርንጫፍ የብር መቀየር ሥራ የተጀመረበትንና የተጠናቀቀበት ቀን እና የተለወጠ የብር መጠን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሳምንቱ ሪፖርት እንዲያደርጉም አሳስቧል።
ከመስከረም 6 ቀን 2ዐ13 ዓ.ም. ጀምሮ ለሶስት ወራት በመላ ሀገሪቱ አሮጌ ብር በአዲስ ብር የመቀየር ሥራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል።
በትግራይ ክልል ባንኮች ስራ ከጀመሩበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በ14 ቀናት ውስጥ አሮጌ ብርን እንዲቀይሩ ከዛሬ ታህሳስ 21 ቀን ጀምሮ መወሰኑን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይል በህግ ማስከበር ዘመቻው የፈጸመው ግዳጅ ውጤታማ እንደነበር ተገለጸ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይል ከእዞችና ከሌሎች የሠራዊት አሀዶች ጋር በመጣመር በህግ ማስከበር ዘመቻው የፈጸመው ግዳጅ ውጤታማ እንደነበር የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ በቀለ ገለጹ፡፡
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ በተለይም በራያና በምዕራብ ግንባሮች በጁንታው ላይ ከባድ ጉዳት በማድረስ ሀያልነቱን አስመስክሯል ብለዋል፡፡
አዲቀይህ አካባቢ በነበረው ፈታኝ ግዳጅ የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ የኮማንዶ ዩኒት በጁንታው ጀርባ በኩል ምሽግ ሰብሮ በመግባት የፈጸመው ጀብዱ ለወገን አኩሪ እንደነበር የገለጹት ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ፣ እስከ መቀሌ በነበረው ተልዕኮም ውጤታማ ግዳጅ መፈጸሙን አስረድተዋል ፡፡
በምዕራቡ ግንባርም ከሁመራ እስከ ዳንሻ የሚሸሸውን የጁንታ ተዋጊ የማገትና የመቆጣጠር ስራ ተሰርቷል ፡፡ በአሁኑ ወቅትም የተንጠባጠበውን የህወሀት ታጣቂ በማደን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ ከህግ ማስከበር ዘመቻው በተጓዳኝ ፣ በምዕራብ ወለጋና በመተከል ሽፍቶችን የመደምሰስ ተልዕኮውን በተሳካ መንገድ በመፈጸም ላይ ይገኛልም ብለዋል ፡፡
የተካሄደው የህግ ማስከበርና የህልውና ዘመቻው ፍትሀዊ ስለነበረ እግረኛው ፣ ሜካናይዝዱ ፣ ልዩ ሀይሉ ፣ አየር ሀይሉ እና ሌሎች የጸጥታ አካላት በጥምረትና በቁርጠኝነት እንዲሁም በብልህ የጦር አመራር የተፈጸመ ዘመቻ በመሆኑ የኢትዮጵያን ህዝብ ያኮራ ተግባር ተፈጽሟል ያሉት ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ፣ ህዝባችን እስካሁን እያደረገ ያለው ድጋፍ ለውጤቱ መሰረታዊ ድርሻ እንደነበረው መግለጻቸውን ከመከላኬ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይል ከእዞችና ከሌሎች የሠራዊት አሀዶች ጋር በመጣመር በህግ ማስከበር ዘመቻው የፈጸመው ግዳጅ ውጤታማ እንደነበር የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ በቀለ ገለጹ፡፡
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ በተለይም በራያና በምዕራብ ግንባሮች በጁንታው ላይ ከባድ ጉዳት በማድረስ ሀያልነቱን አስመስክሯል ብለዋል፡፡
አዲቀይህ አካባቢ በነበረው ፈታኝ ግዳጅ የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ የኮማንዶ ዩኒት በጁንታው ጀርባ በኩል ምሽግ ሰብሮ በመግባት የፈጸመው ጀብዱ ለወገን አኩሪ እንደነበር የገለጹት ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ፣ እስከ መቀሌ በነበረው ተልዕኮም ውጤታማ ግዳጅ መፈጸሙን አስረድተዋል ፡፡
በምዕራቡ ግንባርም ከሁመራ እስከ ዳንሻ የሚሸሸውን የጁንታ ተዋጊ የማገትና የመቆጣጠር ስራ ተሰርቷል ፡፡ በአሁኑ ወቅትም የተንጠባጠበውን የህወሀት ታጣቂ በማደን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሪፐብሊካን ጥበቃ ሀይሉ ከህግ ማስከበር ዘመቻው በተጓዳኝ ፣ በምዕራብ ወለጋና በመተከል ሽፍቶችን የመደምሰስ ተልዕኮውን በተሳካ መንገድ በመፈጸም ላይ ይገኛልም ብለዋል ፡፡
የተካሄደው የህግ ማስከበርና የህልውና ዘመቻው ፍትሀዊ ስለነበረ እግረኛው ፣ ሜካናይዝዱ ፣ ልዩ ሀይሉ ፣ አየር ሀይሉ እና ሌሎች የጸጥታ አካላት በጥምረትና በቁርጠኝነት እንዲሁም በብልህ የጦር አመራር የተፈጸመ ዘመቻ በመሆኑ የኢትዮጵያን ህዝብ ያኮራ ተግባር ተፈጽሟል ያሉት ሜጀር ጀነራል ብርሀኑ፣ ህዝባችን እስካሁን እያደረገ ያለው ድጋፍ ለውጤቱ መሰረታዊ ድርሻ እንደነበረው መግለጻቸውን ከመከላኬ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
“አሁን በየቦታው የምናየው ግጭቶችና አለመግባባቶች ጁንታው ለአገራችን ያስቀመጣቸው አደገኛ የቤት ስራዎች ናቸው” አቶ ሌንጮ ለታ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
አሁን በየቦታው የምናየው ግጭቶችና አለመግባባቶች የህወሀት ጁንታ ባለፉት 27 ዓመታት ለአገራችን ያስቀመጣቸው አደገኛ የቤት ስራዎች መሆናቸውን የቀድሞ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ አስታወቁ። ህዝቡ እውነታውን በአግባቡ በመገንዘብ ለአገሩ ከልብ በመስራት ሰላም እንዲያወርድ ጥሪ አቀረቡ።
አቶ ሌንጮ ለታ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉትቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ መላው ህዝባችን ለዘመናት የታገለለት የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ በአምባገነኑ የሕወሓት ጁንታ እጅ በመውደቁ ሲመኝ የነበረው ራስን በራስ የማስተዳደር ተስፋው መክኖ ቆይቷል።
በአገራችን የዴሞክራሲ ስርዓት ታይቶ በመጥፋቱ በህገ መንግስቱ የተደረደሩት የራስን ዕድል በራስ መወሰን የሚሉና ሌሎችም የዴሞክራሲ መርሆዎች በጁንታው በሀይል መታፈናቸውን ጠቁመው፣ ዛሬ ላይ ህዝቡ በተወሰነ መልኩ መብቱንና ግዴታውን መለማመድ መጀመሩን አስታውቀዋል።
አሁን በየቦታው የምናየው ግጭቶችና አለመግባባቶች ጁንታው ባለፉት 27 ዓመታት ለአገራችን ያስቀመጣቸው አደገኛ የቤት ስራዎች መሆናቸውን ያመለከቱት አቶ ሌንጮ፣ ህዝቡ እውነታውን በአግባቡ በመገንዘብ ለአገሩ ከልብ በመስራት ሰላም እንዲያወርድ ጠይቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38543
*****************
(ኢ ፕ ድ)
አሁን በየቦታው የምናየው ግጭቶችና አለመግባባቶች የህወሀት ጁንታ ባለፉት 27 ዓመታት ለአገራችን ያስቀመጣቸው አደገኛ የቤት ስራዎች መሆናቸውን የቀድሞ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ አስታወቁ። ህዝቡ እውነታውን በአግባቡ በመገንዘብ ለአገሩ ከልብ በመስራት ሰላም እንዲያወርድ ጥሪ አቀረቡ።
አቶ ሌንጮ ለታ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉትቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ መላው ህዝባችን ለዘመናት የታገለለት የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ በአምባገነኑ የሕወሓት ጁንታ እጅ በመውደቁ ሲመኝ የነበረው ራስን በራስ የማስተዳደር ተስፋው መክኖ ቆይቷል።
በአገራችን የዴሞክራሲ ስርዓት ታይቶ በመጥፋቱ በህገ መንግስቱ የተደረደሩት የራስን ዕድል በራስ መወሰን የሚሉና ሌሎችም የዴሞክራሲ መርሆዎች በጁንታው በሀይል መታፈናቸውን ጠቁመው፣ ዛሬ ላይ ህዝቡ በተወሰነ መልኩ መብቱንና ግዴታውን መለማመድ መጀመሩን አስታውቀዋል።
አሁን በየቦታው የምናየው ግጭቶችና አለመግባባቶች ጁንታው ባለፉት 27 ዓመታት ለአገራችን ያስቀመጣቸው አደገኛ የቤት ስራዎች መሆናቸውን ያመለከቱት አቶ ሌንጮ፣ ህዝቡ እውነታውን በአግባቡ በመገንዘብ ለአገሩ ከልብ በመስራት ሰላም እንዲያወርድ ጠይቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38543
የክልሎች ሕገመንግሥት የዜጎችን በአገራቸው የመኖር መብት የነፈገ መሆኑ ተገለጸ
👉በሀገሪቱ እየተፈጠሩ ላሉ ግጭቶች መሰረት መሆኑም ተጠቆመ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የክልሎች ሕገመንግሥት የዜጎች በአገራቸው የመኖር መብት የነፈገ በመሆኑ በየቦታው ግጭቶች እንዲበራከቱ ማድረጉን የሕግና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራን ገለጹ።
በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ታሪክ መምህሩ ዶክተር አልማው ክፍሌ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ የኢትዮጵያ ሕገመንግስት መልካም ነገሮች እንዳሉት ሁሉ ክፋት ያዘሉ ሕጎችም የተካተቱበት ነው። በተለይም ከክልሎች አወቃቀር ጀምሮ ያለው የብሔር፣ የቋንቋ አስተሳሰብ ብዙ ነገሮችን አዛብቷል።
ከእነዚህ መካከል ክልሎች ሕገመንግስት ሲያረቁ አግላይ እንጂ አቃፊና አሳታፊ እንዲሆን አድርገው እንዳልሆነ ያመለከቱት ዶክተር አልማው ፣ ልዩነቱ ገዝፎ አንድ ብሔር በአንድ ክልል ላይ ፈላጭ ቆራጭ እንዲሆን ማድረጉን አስታውቀዋል ።
አገሪቱ ስትሰራ በሕዝቦች መስተጋብር፣ በሕዝቦች ትግል፣ በሕዝቦች ተሳትፎ እንጂ በአንድ ብሔር ማንነትና ብልጽግና እንዳልሆነ የሚያነሱት ዶክተር አልማው፤ የክልሎች ሕገመንግሥት አቀራረጽ ግን ከዚህ የተለየ እንደሆነ አመልክተዋል ።
“የክልሎች ሕገመንግሥት ሲቀረጽ ልዩነቶችን አግዝፎ ሕብረ ብሔራዊነትን አክስቶ ያቀርባል። በሕግ የተሰጠን የባለቤትነት መብት የእኛ ብቻ ነው በሚል በውጣልኝ አስተሳሰብ ተገንብቷል። ይህ ደግሞ ዜጎች በፈለጋቸው ቦታ የመኖር መብታቸውን ከመንፈጉም በላይ ያፈሩትን ሀብት ጭምር ለዚያ ክልል እንዲያስረክቡና ባዷቸውን እንዲሰደዱ ያደርጋል። ግጭቶችም ቢሆኑ የአገር ይገባኛል ባይነት ጥያቄዎች የፈጠሯቸው ናቸው” ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38522
👉በሀገሪቱ እየተፈጠሩ ላሉ ግጭቶች መሰረት መሆኑም ተጠቆመ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የክልሎች ሕገመንግሥት የዜጎች በአገራቸው የመኖር መብት የነፈገ በመሆኑ በየቦታው ግጭቶች እንዲበራከቱ ማድረጉን የሕግና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራን ገለጹ።
በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ታሪክ መምህሩ ዶክተር አልማው ክፍሌ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ የኢትዮጵያ ሕገመንግስት መልካም ነገሮች እንዳሉት ሁሉ ክፋት ያዘሉ ሕጎችም የተካተቱበት ነው። በተለይም ከክልሎች አወቃቀር ጀምሮ ያለው የብሔር፣ የቋንቋ አስተሳሰብ ብዙ ነገሮችን አዛብቷል።
ከእነዚህ መካከል ክልሎች ሕገመንግስት ሲያረቁ አግላይ እንጂ አቃፊና አሳታፊ እንዲሆን አድርገው እንዳልሆነ ያመለከቱት ዶክተር አልማው ፣ ልዩነቱ ገዝፎ አንድ ብሔር በአንድ ክልል ላይ ፈላጭ ቆራጭ እንዲሆን ማድረጉን አስታውቀዋል ።
አገሪቱ ስትሰራ በሕዝቦች መስተጋብር፣ በሕዝቦች ትግል፣ በሕዝቦች ተሳትፎ እንጂ በአንድ ብሔር ማንነትና ብልጽግና እንዳልሆነ የሚያነሱት ዶክተር አልማው፤ የክልሎች ሕገመንግሥት አቀራረጽ ግን ከዚህ የተለየ እንደሆነ አመልክተዋል ።
“የክልሎች ሕገመንግሥት ሲቀረጽ ልዩነቶችን አግዝፎ ሕብረ ብሔራዊነትን አክስቶ ያቀርባል። በሕግ የተሰጠን የባለቤትነት መብት የእኛ ብቻ ነው በሚል በውጣልኝ አስተሳሰብ ተገንብቷል። ይህ ደግሞ ዜጎች በፈለጋቸው ቦታ የመኖር መብታቸውን ከመንፈጉም በላይ ያፈሩትን ሀብት ጭምር ለዚያ ክልል እንዲያስረክቡና ባዷቸውን እንዲሰደዱ ያደርጋል። ግጭቶችም ቢሆኑ የአገር ይገባኛል ባይነት ጥያቄዎች የፈጠሯቸው ናቸው” ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38522
ግብጾች በአምባሳደር ዲና ገለጻ 'አንድ አንድ ሃይሎች' በሚል የተገለጽነው እኛ ነን ካሉ ኢትዮጵያ ግብፅን ወክላ መከራከር አይቻላትም ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮቻችን ገለጹ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሳምንታዊው የሚኒስቴሩ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ "አንዳንድ ሃይሎች ሱዳንን ከወዳጅ ሀገር ኢትዮጵያ በድንበር ውዝግብ ሰበብ ግጭት ውስጥ እንድትገባ በመገፋፋት፣ ቀጣናውን በማተራመስ የውስጥ ችግሮቻቸውን አቅጣጫ ለማሳት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው" በሚል ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር አሕመድ ሀፊዝ “ግብፅ የግድቡን ግንባታ የምትቃወመው በሀገሪቱ ያለባትን ቀውስ ለማቀዝቀዝ ነው ማለታቸው ተገቢ አስተያየት አይደለም” ሲሉ መግለጫ ሰጥተዋል፤ በዚሁ መግለጫቸው አምባሳደር ዲና ሙፍቲን ጠቅሰው ወቀሳ ሰንዝረዋል።
በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጉዳዩን ለማጣራት ጥረት አድርጓል።
በዚህም መሰረት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮቻን ያገኘው መረጃ አምባሳደር ዲና በመግለጫቸው የማንንም አገር ስም ያልጠቀሱ ሲሆን፤ የእርሳቸውን ማብራሪያ ተከትሎ ኬንያ ፣ ጂቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን ወይም ሶማሊያ እኛን ይሆን ብለው እንዳልተጨነቁ እና ማብራሪያም እንዳልጠየቁ አረጋግጠናል።
በተቃራኒው ከግብፅ በኩል የአምባሳደሩ ማብራሪያ በርግጠኝነት እኛን ማለት ነው የሚሉ ድምፆች በይፋ እየተደመጡ ነው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮቻችን፤ ግብፆች ስም ባንጠቅስም የምንሰራውን እናውቃለንና በትክክል እኛ ነን ካሉ ኢትዮጵያ ግብፅን ወክላ መከራከር አይቻላትም ሲሉ ጉዳዩን አጣጥለውታል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሳምንታዊው የሚኒስቴሩ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ "አንዳንድ ሃይሎች ሱዳንን ከወዳጅ ሀገር ኢትዮጵያ በድንበር ውዝግብ ሰበብ ግጭት ውስጥ እንድትገባ በመገፋፋት፣ ቀጣናውን በማተራመስ የውስጥ ችግሮቻቸውን አቅጣጫ ለማሳት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው" በሚል ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር አሕመድ ሀፊዝ “ግብፅ የግድቡን ግንባታ የምትቃወመው በሀገሪቱ ያለባትን ቀውስ ለማቀዝቀዝ ነው ማለታቸው ተገቢ አስተያየት አይደለም” ሲሉ መግለጫ ሰጥተዋል፤ በዚሁ መግለጫቸው አምባሳደር ዲና ሙፍቲን ጠቅሰው ወቀሳ ሰንዝረዋል።
በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጉዳዩን ለማጣራት ጥረት አድርጓል።
በዚህም መሰረት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮቻን ያገኘው መረጃ አምባሳደር ዲና በመግለጫቸው የማንንም አገር ስም ያልጠቀሱ ሲሆን፤ የእርሳቸውን ማብራሪያ ተከትሎ ኬንያ ፣ ጂቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን ወይም ሶማሊያ እኛን ይሆን ብለው እንዳልተጨነቁ እና ማብራሪያም እንዳልጠየቁ አረጋግጠናል።
በተቃራኒው ከግብፅ በኩል የአምባሳደሩ ማብራሪያ በርግጠኝነት እኛን ማለት ነው የሚሉ ድምፆች በይፋ እየተደመጡ ነው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮቻችን፤ ግብፆች ስም ባንጠቅስም የምንሰራውን እናውቃለንና በትክክል እኛ ነን ካሉ ኢትዮጵያ ግብፅን ወክላ መከራከር አይቻላትም ሲሉ ጉዳዩን አጣጥለውታል።
በደብረ ማርቆስ ከተማ የንባብ ሳምንት ጉባዔ እየተካሄደ ነው
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻህፍት ኤጀንሲ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሀዲስ አለማየሁ ተቋምና ከአማራ ክልል ባህል ቱሪዝምና ፓርኮች ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር " መጻህፍት የእውቀት ገበታ፤ መዛግብት የዘመን ትውስታ" በሚል መሪ ቃል የንባብ ሳምንት የፓናል ውይይትና አውደ ርዕይ በደብረ ማርቆስ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
ሁነቱ ለትውልድ የንባብ ባህል በማካፈልና አንባቢ ትውልድ በመፍጠር እንዲሁም ለአገሩ የሚጠቅም ዜጋ ለማፍራት እንደሚረዳ ተመላክቷል።
በተለይም የመረጃ ቋት የሆኑት ቤተ መጻፍትና ቤተ መዛግብት የዘመኑን ቴክኖሎጂ እንዲዋጁ አቅጣጫ ለማስቀመጥም መልካም አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ኤጀንሲው ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ ከክልሎችና ከከተማ መስተዳድር ባህልና ቱሪዝም ቢሮዎችና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የንባብ ሳምንት ማዘጋጀት ነው።
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻህፍት ኤጀንሲ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሀዲስ አለማየሁ ተቋምና ከአማራ ክልል ባህል ቱሪዝምና ፓርኮች ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር " መጻህፍት የእውቀት ገበታ፤ መዛግብት የዘመን ትውስታ" በሚል መሪ ቃል የንባብ ሳምንት የፓናል ውይይትና አውደ ርዕይ በደብረ ማርቆስ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
ሁነቱ ለትውልድ የንባብ ባህል በማካፈልና አንባቢ ትውልድ በመፍጠር እንዲሁም ለአገሩ የሚጠቅም ዜጋ ለማፍራት እንደሚረዳ ተመላክቷል።
በተለይም የመረጃ ቋት የሆኑት ቤተ መጻፍትና ቤተ መዛግብት የዘመኑን ቴክኖሎጂ እንዲዋጁ አቅጣጫ ለማስቀመጥም መልካም አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ኤጀንሲው ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ ከክልሎችና ከከተማ መስተዳድር ባህልና ቱሪዝም ቢሮዎችና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የንባብ ሳምንት ማዘጋጀት ነው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ 888 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገለጸ
👉56 ሽልማቶችን ለባለ ዕድለኛ ደንበኞቹ አስረከበ
***********************
( ኢ ፕ ድ)
የ‹‹ይቆጥቡ ይሸለሙ›› ፕሮግራም ከተጀመረበት ከ2004 ዓ.ም ወዲህ በየዓመቱ በአማካኝ ከ2 ሚሊዮን በላይ አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት የባንኩን ጠቅላላ ሀብት 888 ቢሊዮን ብር ማድረስ መቻሉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የ‹‹ይቆጥቡ ይሸለሙ›› የ10ኛ ዙር የሽልማት መርሐ ግብር ላይ ለባለ ዕድለኛ ደንበኞቹ ሽልማታቸውን ባስረከቡበት ዕለት እንደገለጹት፤ ባንኩ ይህን ሽልማት ከመጀመሩ በፊት የነበረው ጠቅላላ ሀብት 74 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ ሽልማቱን በጀመረ በአስር ዓመት ውስጥ 888 ቢሊዮን ብር መድረስ ችሏል ብለዋል።
እንዲሁም ከአስር ዓመት በፊት 2 ነጥብ 2 የነበረውን የቁጠባ ሂሳብ ብዛት ከ26 ሚሊዮን በላይ በማሳደግ 56 ቢሊዮን ብር የነበረውን ጠቅላላ የባንኩን ተቀማጭ ገንዘብ ወደ 670 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።
ባንካችን የውጭና የሀገር ውስጥ ገንዘብ ለማሰባሰብ ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል አንዱ የ‹‹ይቆጥቡ፤ ይሸለሙ›› እና ‹‹ይቀበሉ፤ ይመንዝሩ፤ ይሸለሙ›› ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ይህ ስልት ህብረተሰቡ የቁጠባ ባህሉን እንዲያሳድግ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38593
👉56 ሽልማቶችን ለባለ ዕድለኛ ደንበኞቹ አስረከበ
***********************
( ኢ ፕ ድ)
የ‹‹ይቆጥቡ ይሸለሙ›› ፕሮግራም ከተጀመረበት ከ2004 ዓ.ም ወዲህ በየዓመቱ በአማካኝ ከ2 ሚሊዮን በላይ አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት የባንኩን ጠቅላላ ሀብት 888 ቢሊዮን ብር ማድረስ መቻሉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የ‹‹ይቆጥቡ ይሸለሙ›› የ10ኛ ዙር የሽልማት መርሐ ግብር ላይ ለባለ ዕድለኛ ደንበኞቹ ሽልማታቸውን ባስረከቡበት ዕለት እንደገለጹት፤ ባንኩ ይህን ሽልማት ከመጀመሩ በፊት የነበረው ጠቅላላ ሀብት 74 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ ሽልማቱን በጀመረ በአስር ዓመት ውስጥ 888 ቢሊዮን ብር መድረስ ችሏል ብለዋል።
እንዲሁም ከአስር ዓመት በፊት 2 ነጥብ 2 የነበረውን የቁጠባ ሂሳብ ብዛት ከ26 ሚሊዮን በላይ በማሳደግ 56 ቢሊዮን ብር የነበረውን ጠቅላላ የባንኩን ተቀማጭ ገንዘብ ወደ 670 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።
ባንካችን የውጭና የሀገር ውስጥ ገንዘብ ለማሰባሰብ ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል አንዱ የ‹‹ይቆጥቡ፤ ይሸለሙ›› እና ‹‹ይቀበሉ፤ ይመንዝሩ፤ ይሸለሙ›› ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ይህ ስልት ህብረተሰቡ የቁጠባ ባህሉን እንዲያሳድግ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38593
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን የህውሓት ጁንታ በሚነዛው የሐሰት መረጃ ተሸብበው በሀሰት ዘገባ ላይ ተጠምደው እንደነበር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን በትግራይ ክልል የተወሰደውን ህግ የማስከበር ዘመቻ ትክክለኛ ገጽታ ወደጎን በመተው የህውሓት ጁንታ በሚነዛው የሐሰት መረጃ ተጠምደው የሀሰት ዘገባ ሲያሰራጩ እንደነበር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን የፈረንጆቹን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በኩል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ሚዲያው የህውሓት ጁንታ በሚነዛው የሐሰት መረጃ ተሸብቦ የሀሰት ዘገባ ሲያሰራጭ እንደነበር በግልጽ የታየበት ሁኔታን መመልከት ተችሏል።
ይህ የሚዲያዎች ሁኔታ ትምህርት የተወሰደበት ነው ያሉት አቶ ደመቀ፤ በፕሮፓጋንዳ የተደገፈውን የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ አስተሳሰብ ለመለወጥ ራሱን የቻለ ስራ እንደበነረም አብራርተዋል።
"ሁኔታው ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን በጁንታው የሐሰት መረጃ ተሸንፈው የፌዴራል መንግስት በትግራይ ህዝብ ላይ ጥቃት እያደረሰ እንደሆነ መዘገባቸውን ያየንበትና ትምህርት የውስድንበት ነው" ብለዋል አቶ ደመቀ፡፡
የዓለም አቀፍ ሚዲያው መሬት ላይ ለው እውነት ከመፈለግ ይልቅ የጁንታውን የሐሰት ወሬ በማራገብ የህግ ማስከበር እርምጃው ቡድኑን ለማጥቃት እንጂ ህግን ለማስከበር አይደለም በማለት የሀስት መረጃ ሲያሰራጩ እንደነበርም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት፡፡https://www.press.et/english/?p=27767#
********************
(ኢ ፕ ድ)
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን በትግራይ ክልል የተወሰደውን ህግ የማስከበር ዘመቻ ትክክለኛ ገጽታ ወደጎን በመተው የህውሓት ጁንታ በሚነዛው የሐሰት መረጃ ተጠምደው የሀሰት ዘገባ ሲያሰራጩ እንደነበር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን የፈረንጆቹን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በኩል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ሚዲያው የህውሓት ጁንታ በሚነዛው የሐሰት መረጃ ተሸብቦ የሀሰት ዘገባ ሲያሰራጭ እንደነበር በግልጽ የታየበት ሁኔታን መመልከት ተችሏል።
ይህ የሚዲያዎች ሁኔታ ትምህርት የተወሰደበት ነው ያሉት አቶ ደመቀ፤ በፕሮፓጋንዳ የተደገፈውን የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ አስተሳሰብ ለመለወጥ ራሱን የቻለ ስራ እንደበነረም አብራርተዋል።
"ሁኔታው ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን በጁንታው የሐሰት መረጃ ተሸንፈው የፌዴራል መንግስት በትግራይ ህዝብ ላይ ጥቃት እያደረሰ እንደሆነ መዘገባቸውን ያየንበትና ትምህርት የውስድንበት ነው" ብለዋል አቶ ደመቀ፡፡
የዓለም አቀፍ ሚዲያው መሬት ላይ ለው እውነት ከመፈለግ ይልቅ የጁንታውን የሐሰት ወሬ በማራገብ የህግ ማስከበር እርምጃው ቡድኑን ለማጥቃት እንጂ ህግን ለማስከበር አይደለም በማለት የሀስት መረጃ ሲያሰራጩ እንደነበርም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት፡፡https://www.press.et/english/?p=27767#
ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተገለጸ
- በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸው ተገለፀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸውን የመከላከያ ሐይል ሥምሪት መምሪያ ሐላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው አስታወቁ።
በውጭ የሚገኙ የጁንታው ሚዲያዎች የሐሰት ኘሮፓጋንዳ ቢያናፍሱም፣ የመከላከያ ሐይልና ፌዴራል ፓሊስ በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ፣ በርካቶች መማረካቸው ተገልጿል። እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑትም ተደምስሰዋል ብለዋል።
የተቀሩትም በየእምነት ተቋማትና ገዳማት፣ ዋሻና ሸለቆዎች እራሳቸውን ደብቀው እንደሚገኙ መረጃ እንዳላቸው የገለፁት ጄኔራሉ፣ ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል።
የጁንታ ሐይል ተደምስሷል፣ በየሸለቆው የደበቃቸው የህዝብና የመንግስት ንብረት ተይዟል ያሉት ሐላፊው በአንዳንድ አካላት ከውጭ የሚነዛው ኘሮፖጋንዳ ፍፁም ሐሳት መሆኑን አስረድተዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።
- በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸው ተገለፀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በርካታ የጁንታው ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች መማረካቸውን እና መደምሰሳቸውን የመከላከያ ሐይል ሥምሪት መምሪያ ሐላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው አስታወቁ።
በውጭ የሚገኙ የጁንታው ሚዲያዎች የሐሰት ኘሮፓጋንዳ ቢያናፍሱም፣ የመከላከያ ሐይልና ፌዴራል ፓሊስ በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ፣ በርካቶች መማረካቸው ተገልጿል። እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑትም ተደምስሰዋል ብለዋል።
የተቀሩትም በየእምነት ተቋማትና ገዳማት፣ ዋሻና ሸለቆዎች እራሳቸውን ደብቀው እንደሚገኙ መረጃ እንዳላቸው የገለፁት ጄኔራሉ፣ ጁንታው የሞቱበትን ከፍተኛ አመራሮቹን ከሰብአዊ ርህራሄ ውጭ በሆነ መልኩ እንዳይታወቁ አንገታቸውን ቆርጦ ለየብቻ ስለሚቀብራቸው ለመለየት አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል።
የጁንታ ሐይል ተደምስሷል፣ በየሸለቆው የደበቃቸው የህዝብና የመንግስት ንብረት ተይዟል ያሉት ሐላፊው በአንዳንድ አካላት ከውጭ የሚነዛው ኘሮፖጋንዳ ፍፁም ሐሳት መሆኑን አስረድተዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ"
- አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ
የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር
(ኢ ፕ ድ)
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ እንደሚችሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ገለፁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ከሶማሌ ክልል ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲ በፍትህ ተቋማት፣በዲሞክራሲ ግንባታና በሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ጥሩ ስራዎች ቢሰሩም መሻሻል ያለባቸው ስራዎች እንዳሉም ጠቅሰው እንደ ክልል በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሩ ጤናማና ህዝብንና መንግስትን በተሻለ መንገድ ያቀራረበ መሆኑን ገልፀዋል ።
የክልሉ የለውጥ አመራር በሐሳብ ብዝሐነትና ልዕልና የሚያምን የዜጎችን የመናገር ነፃነት የሚያከብር ነው ያሉት አቶ ህዝብም የተሰማውን በሰለጠነ መንገድ መንግስትን የመጠየቅ የዲሞክራሲ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና የክልሉ መንግስትም የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ተግቶ ይሰራል ብለዋል።
ካለፉት አመታት የተሻለ የፖለቲካ ምህዳር መኖሩን ጠቅሰው ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ መንገድ ፣የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ ብለዋል ።
- አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ
የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር
(ኢ ፕ ድ)
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ፣ የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ እንደሚችሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ገለፁ።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ከሶማሌ ክልል ቴሌቭዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ከለውጡ ወዲ በፍትህ ተቋማት፣በዲሞክራሲ ግንባታና በሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ጥሩ ስራዎች ቢሰሩም መሻሻል ያለባቸው ስራዎች እንዳሉም ጠቅሰው እንደ ክልል በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሩ ጤናማና ህዝብንና መንግስትን በተሻለ መንገድ ያቀራረበ መሆኑን ገልፀዋል ።
የክልሉ የለውጥ አመራር በሐሳብ ብዝሐነትና ልዕልና የሚያምን የዜጎችን የመናገር ነፃነት የሚያከብር ነው ያሉት አቶ ህዝብም የተሰማውን በሰለጠነ መንገድ መንግስትን የመጠየቅ የዲሞክራሲ ባህልን ማዳበር እንደሚገባና የክልሉ መንግስትም የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ ተግቶ ይሰራል ብለዋል።
ካለፉት አመታት የተሻለ የፖለቲካ ምህዳር መኖሩን ጠቅሰው ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች አለኝ የሚሉትን ሐሳብ በሰላማዊ መንገድ ፣የህዝብና የሐገርን ሰላም በማያውክ መንገድ ሐሳቡን መሸጥ ይችላሉ ብለዋል ።
በአዳማ ከተማ የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር ተከፈተ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በአዳማ ከተማ በአባገዳ አዳራሽ ተከፈተ፡፡
በአውደ ርዕይና ባዛር ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልሉ አመራሮች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በአውደ ርዕይ እና ባዛሩ ላይም የተለያዩ የግብርና ምርቶችና ውጤቶች ቀርበዋል፡፡
የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ በአውደ ርዕይ እና ባዛር ላይ እንድገለጹት የፕሮግራሙ ዓላማ በግብርና ምርት ውጤቶችና ቴክኖሎጂዎች ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ ለዘርፉ ዕድገት ድጋፍ ላበረከቱ ምሁራን እና ባለሀብቶች ዕውቅና መስጠታቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በአዳማ ከተማ በአባገዳ አዳራሽ ተከፈተ፡፡
በአውደ ርዕይና ባዛር ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የክልሉ አመራሮች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በአውደ ርዕይ እና ባዛሩ ላይም የተለያዩ የግብርና ምርቶችና ውጤቶች ቀርበዋል፡፡
የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ በአውደ ርዕይ እና ባዛር ላይ እንድገለጹት የፕሮግራሙ ዓላማ በግብርና ምርት ውጤቶችና ቴክኖሎጂዎች ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ፣ ለዘርፉ ዕድገት ድጋፍ ላበረከቱ ምሁራን እና ባለሀብቶች ዕውቅና መስጠታቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
“የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት የሱዳን መንግሥትና ህዝብ ፍላጎት አይደለም”አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመለከተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በግጭቱ ዙሪያ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር 100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም በሌሎችም የአፍሪካ አገራት እንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ባትገዛም ሱዳን በቅኝ ግዥዎች ስር ስለነበረች፣ ድንበሩ ምንም እንኳ ምልክቶች ቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ በትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ በሁለቱም አገሮች የድንበር አካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ ብለዋል፡፡
አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።
አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት ከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን ለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች መጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ግጭቱ የሱዳን ህዝብና መንግሥት ፍላጎት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ እንዳልደረሰ ገልጸዋል።
ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል።
ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ ከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ወደ ግጭት አንገባም” የሚሉ ድምፆች እየጨሩ መምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፣ ከበስተጀረባው ግን የተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ወዳዱ የሱዳን ህዝብ እና ባለስልጣናት ፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል።
አንዳንድ የሱዳን ወታደሮችና ሚሊሻዎች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው በመግባት የሰው ህይወት ማጥፋታቸውና ንብረት ማውደማቸውን አመልክተው፣ መንግሥትም ጸጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ችግሩ በድርድር እንዲፈታ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮ – ሱዳን ድንበር ግጭት ሱዳን መንግሥትና ሰፊው የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ። ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ የኢትዮጵያ አቋም መሆኑንም አመለከተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በግጭቱ ዙሪያ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር 100 ዓመት ያስቆጠረ ቢሆንም በሌሎችም የአፍሪካ አገራት እንደሚታየው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሱ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ባትገዛም ሱዳን በቅኝ ግዥዎች ስር ስለነበረች፣ ድንበሩ ምንም እንኳ ምልክቶች ቢኖሩትም በዘመናዊ ዘዴ በትክክል ባለመካለሉ አንዳንዴ በሁለቱም አገሮች የድንበር አካባቢዎች መገፋፋቶች ይፈጠራሉ ብለዋል፡፡
አሁን ያለው ድንበር ባህላዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰሞኑን የሱዳን ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ የኢትዮጵያን መሬት መያዛቸው ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ አንዳንድ የሱዳን ሚዲዎችና ባለስልጣናት መሬታቸውን እንዳስመለሱ አድረገው በመግለጫ የሚያሰራጩት መረጃ ተቀባይነት የሌለውና ህገ ወጥ መሆኑ አስታውቀዋል።
አንዳንድ የሱዳን ባለስልጣናት ከኋላ ሆነዉ ጉዳዩን ለሚያቀጣጥሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች መጠቀሚያ ሆነው ቢያገለግሉም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ግጭቱ የሱዳን ህዝብና መንግሥት ፍላጎት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ እንዳልደረሰ ገልጸዋል።
ይልቁንስ መጠቀሚያ እየሆኑ ያሉ የሱዳን ባለስልጣናት ድርጊታቸው ሱዳንንም ሆነ ኢትዮጵያን በፍጹም ስለማይጠቅም ያሉትን ችግሮች በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት እያሳሰበ መሆኑን ገልጸዋል። ድንበሩም በድንበር ኮሚሽን መርሆዎች ብቻ እንዲፈታም የኢትዮጵያ አቋም እንደሆነም አስታውቀዋል።
ግጭቱ የሱዳን መንግሥትና የሱዳን ህዝብ ፍላጎት እንዳልሆነ የሚገልጹ “እኛ ከኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ወደ ግጭት አንገባም” የሚሉ ድምፆች እየጨሩ መምጣታቸውን የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፣ ከበስተጀረባው ግን የተለያዩ ኃይሎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
እነዚህ ኃይሎች ለዘመናት ያልጠቀሟትን ሱዳን ወዳጅ በማስመሰል የጥፋት አጀንዳቸውን ለማሳካት እየታተሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላም ወዳዱ የሱዳን ህዝብ እና ባለስልጣናት ፣ እንዲሁም ለሰላም ወዳዱ የአረቡ ማህበረሰብ ፣ ግጭቱ ለማንም እንደማይበጅ በተጨባጭ እያሳወቀች መሆኑን አመልክተዋል።
አንዳንድ የሱዳን ወታደሮችና ሚሊሻዎች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው በመግባት የሰው ህይወት ማጥፋታቸውና ንብረት ማውደማቸውን አመልክተው፣ መንግሥትም ጸጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ችግሩ በድርድር እንዲፈታ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ 311 ሺህ 421 ተማሪዎች ተመዝግበዋል
-500 ሺህ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል።
በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈታኞች ምዝገባና ውጤት ጥንቅር ዳይሬክተር አቶ ዩሴፍ አበራ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የአጠቃላይ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ከጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ ለመስጠት መርሐግብር ተይዟል።
በዚህ መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ መደረጉን ገልጸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።
ምዝገባው ከትግራይ ክልል እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በስተቀር በሁሉ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካሄዱን የገለጹት ኃላፊው፣ በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ካጋጠመው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዳልተቻለ አመልክተዋል።
በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ቀደም ሲል ምዝገባ የተጀምረ ቢሆንም ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ መቋረጡን አስታውሰው፤ በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስችል ሁኔታ ለመፍጠር እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
በትግራይ ክልል 80 ያህል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በመተከል ደግሞ እስከ 14 ትምህርት ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል፣ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ምዝገባ ከተደረገ ቁጥሩ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38751
-500 ሺህ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል።
በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈታኞች ምዝገባና ውጤት ጥንቅር ዳይሬክተር አቶ ዩሴፍ አበራ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የአጠቃላይ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ከጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ ለመስጠት መርሐግብር ተይዟል።
በዚህ መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ መደረጉን ገልጸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።
ምዝገባው ከትግራይ ክልል እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በስተቀር በሁሉ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካሄዱን የገለጹት ኃላፊው፣ በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ካጋጠመው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዳልተቻለ አመልክተዋል።
በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ቀደም ሲል ምዝገባ የተጀምረ ቢሆንም ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ መቋረጡን አስታውሰው፤ በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስችል ሁኔታ ለመፍጠር እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
በትግራይ ክልል 80 ያህል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በመተከል ደግሞ እስከ 14 ትምህርት ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል፣ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ምዝገባ ከተደረገ ቁጥሩ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38751
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በዛሬው ዕለት በበይነ-መረብ ስብሰባ አካሂደዋል
**************
- ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው ገልጻለች፤
- የሱዳን ወገን ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል፤
- የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው አስታውቋል
(ኢ.ፕ.ድ)
ስብሰባው በደቡብ አፍሪካ የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሰብሳቢነት ተካሂዷል።
ሚኒስትሮቹ የሕዳሴው ግድብ ድርድር በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ያደረጉ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሰየሟቸው ባለሙያዎች ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ ላይ በማተኮር ምክክር ተደርጓል፡፡
በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው እና በቀጣይ በሚካሄደው ድርድር ሰነዱን እንደግብዓት ለመጠቀም ፈቃደኛ መሆኗን ገልጣለች፡፡
የሱዳን ወገን በበኩሉ ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው እና በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት ባለሙያዎች ተጨማሪ ሚና ላይ ቢጋር በማጽደቅ ድርድሩን መቀጠል እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡
የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው ገልጧል፡፡
የሕዳሴው ግድብ ሙሌት እና ዓመታዊ አስተዳደርን የሚመለከተው ሰነድ ላይ የሚደረገው ድርድር በአመዛኙ መግባባት የተደረሰበት ቢሆንም፣ ወደፊት በዓባይ ተፋሰስ ላይ በሚገነቡ የውሃ ልማት ሥራዎች ጋር የሚኖረው ቁርኝት ዋነኛ የልዩነት ሃሳብ ነው፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ፍጆታ የሌለው የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደመሆኑ በግድቡ ላይ የሚደረሰው ስምምነት ይህንኑ ከግምት ያስገባ እና የተሟላ የውሃ ስምምነት በሌለበት እና ኢፍትሃዊ አጠቃቀም በሰፈነበት ተፋሰስ የኢትዮጵያን የመጠቀም መብት የሚያቅብ እንዲሆን ኢትዮጵያ አትፈቅድም፡፡
ይህን መሰረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ አሞላል እና ዓመታዊ አስተደዳር የሚመለከተውን ደንብ በጋራ ስምምነት ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ ናት፡፡
በዚህም መሰረት የስምምነት አማራጮችን ለግብጽ እና ሱዳን ወገን ያቀረበች ሲሆን የሃገራቱ ምላሽ ቀና እንደሚሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡
በቀጣይ የሃገራቱ ባለሙያዎች በውሃ ሚኒስትሮች አመራር ስር ስብሰባቸውን በመቀጠል ስምምነት የተደረሰባቸውን እና የልዩነት ሃሳቦችን በመለየት በቀጣይ ዕሁድ ጥር 01 ቀን 2013 ለሚካሄደው የስድስት ሚኒስትሮች ስብሰባ ውጤቱን ያቀርባሉ፡፡
**************
- ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው ገልጻለች፤
- የሱዳን ወገን ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል፤
- የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው አስታውቋል
(ኢ.ፕ.ድ)
ስብሰባው በደቡብ አፍሪካ የዓለምአቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሰብሳቢነት ተካሂዷል።
ሚኒስትሮቹ የሕዳሴው ግድብ ድርድር በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ያደረጉ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሰየሟቸው ባለሙያዎች ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ ላይ በማተኮር ምክክር ተደርጓል፡፡
በዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹ የቀረጹትን ሰነድ በበጎ እንደምትመለከተው እና በቀጣይ በሚካሄደው ድርድር ሰነዱን እንደግብዓት ለመጠቀም ፈቃደኛ መሆኗን ገልጣለች፡፡
የሱዳን ወገን በበኩሉ ሰነዱን ለሂደቱ ጠቃሚ አድርጎ እንደሚመለከተው እና በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት ባለሙያዎች ተጨማሪ ሚና ላይ ቢጋር በማጽደቅ ድርድሩን መቀጠል እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡
የግብጽ ወገን ሰነዱን ጨርሶ እንደማይቀበለው ገልጧል፡፡
የሕዳሴው ግድብ ሙሌት እና ዓመታዊ አስተዳደርን የሚመለከተው ሰነድ ላይ የሚደረገው ድርድር በአመዛኙ መግባባት የተደረሰበት ቢሆንም፣ ወደፊት በዓባይ ተፋሰስ ላይ በሚገነቡ የውሃ ልማት ሥራዎች ጋር የሚኖረው ቁርኝት ዋነኛ የልዩነት ሃሳብ ነው፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ፍጆታ የሌለው የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደመሆኑ በግድቡ ላይ የሚደረሰው ስምምነት ይህንኑ ከግምት ያስገባ እና የተሟላ የውሃ ስምምነት በሌለበት እና ኢፍትሃዊ አጠቃቀም በሰፈነበት ተፋሰስ የኢትዮጵያን የመጠቀም መብት የሚያቅብ እንዲሆን ኢትዮጵያ አትፈቅድም፡፡
ይህን መሰረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ አሞላል እና ዓመታዊ አስተደዳር የሚመለከተውን ደንብ በጋራ ስምምነት ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ ናት፡፡
በዚህም መሰረት የስምምነት አማራጮችን ለግብጽ እና ሱዳን ወገን ያቀረበች ሲሆን የሃገራቱ ምላሽ ቀና እንደሚሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡
በቀጣይ የሃገራቱ ባለሙያዎች በውሃ ሚኒስትሮች አመራር ስር ስብሰባቸውን በመቀጠል ስምምነት የተደረሰባቸውን እና የልዩነት ሃሳቦችን በመለየት በቀጣይ ዕሁድ ጥር 01 ቀን 2013 ለሚካሄደው የስድስት ሚኒስትሮች ስብሰባ ውጤቱን ያቀርባሉ፡፡
በቡሬ ከተማ የተቋቋመው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩ ተገለጸ
********************************
(ኢ ፕ ድ)
በቡሬ ከተማ የተቋቋመውንና ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል በቡሬ ከተማ የተቋቋመውን የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ምርት ለማምረት ላበቁት አካላት በትዊተር ገጻቸው ምስጋና አቅርበዋል::
በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ለተገነባው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ስኬታማነት አስተዋጽዖ ለነበራቸውና ፕሮጀክቱ ሥራ እንዲጀምር ጥረት ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል” ብለዋል፡፡
የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን አቶ መላኩ በትዊተር ገጻቸው ጠቅሰዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከዚህ በፊትም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር ለገበያ እንደሚያቀርብ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
በቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሪችላንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው የአኩሪ አተር ፕሮቲንና የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ወደ ሙከራ ምርት መግባቱን ገልጸው ነበር፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባም 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት ለሀገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል።
ለውጪ ገበያ ከሚያቀርበው የምግብ ዘይትም 61 ሚሊዮን 680 ሺህ ዶላር እንደሚያስገኝ ሚኒስትሩ መናገራቸው አብመድ ዘግቧል፡፡
********************************
(ኢ ፕ ድ)
በቡሬ ከተማ የተቋቋመውንና ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል በቡሬ ከተማ የተቋቋመውን የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ምርት ለማምረት ላበቁት አካላት በትዊተር ገጻቸው ምስጋና አቅርበዋል::
በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ከተማ ከ991 ሚሊዮን ብር በላይ ለተገነባው የአቶ በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ስኬታማነት አስተዋጽዖ ለነበራቸውና ፕሮጀክቱ ሥራ እንዲጀምር ጥረት ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል” ብለዋል፡፡
የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት መጀመሩን አቶ መላኩ በትዊተር ገጻቸው ጠቅሰዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከዚህ በፊትም ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር ለገበያ እንደሚያቀርብ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
በቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሪችላንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው የአኩሪ አተር ፕሮቲንና የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ ወደ ሙከራ ምርት መግባቱን ገልጸው ነበር፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባም 22 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት ለሀገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል።
ለውጪ ገበያ ከሚያቀርበው የምግብ ዘይትም 61 ሚሊዮን 680 ሺህ ዶላር እንደሚያስገኝ ሚኒስትሩ መናገራቸው አብመድ ዘግቧል፡፡
“አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሠረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ ነው” አቶ ጊደና መድህን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ
******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሰረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አስታወቁ።
ዋና ፀሐፊው አቶ ጊደና መድህን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም ማህበራዊ መሰረታችን ትግራይ ላይ የሆንን ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ታስረናል። ተመርዘናል። ተገርፈናል፤ አሁን ግን ኑ ሃሳብ አላችሁ ተብለን ወደ ሥራ ገብተናል። እኔ እንኳን በሙያዬ ክልሉን እንዳገለግል የውሃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በመሆን ተሹሜያለሁ።
አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉንም ሃሳብ ያላቸውን የክልሉን ተወላጆች ወደ አመራርነት በማምጣት ፣ በሌላም መንገድ በልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን እንዲሳተፉ በማስቻል በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ውስጥ የተለየ ሃሳብ ያለው የሚታሰርበት ፣የሚገረፍበት እና የሚገደልበት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጊደና ፤ አሁን ግን ጊዜያዊ አስተዳደሩ ህዝቡ ችግር ውስጥ ነው ታስፈልጉታላችሁ፤ የዴሞክራሲ ምህዳሩንም እናሰፋለን በማለት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ላይ እንድንገባ ተደርጓል። ይህ ደግሞ ለትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን ለመላ አገሪቱ ትልቅ እመርታ ነው ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38804
******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱ የትግራይ ክልል ካቢኔ ማህበራዊ መሰረታቸው ትግራይ ላይ የሆኑ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈ መሆኑን በተግባር ማረጋገጡን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አስታወቁ።
ዋና ፀሐፊው አቶ ጊደና መድህን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ ከዚህ ቀደም ማህበራዊ መሰረታችን ትግራይ ላይ የሆንን ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ታስረናል። ተመርዘናል። ተገርፈናል፤ አሁን ግን ኑ ሃሳብ አላችሁ ተብለን ወደ ሥራ ገብተናል። እኔ እንኳን በሙያዬ ክልሉን እንዳገለግል የውሃ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በመሆን ተሹሜያለሁ።
አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉንም ሃሳብ ያላቸውን የክልሉን ተወላጆች ወደ አመራርነት በማምጣት ፣ በሌላም መንገድ በልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን እንዲሳተፉ በማስቻል በኩል ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።
ከዚህ ቀደም በትግራይ ውስጥ የተለየ ሃሳብ ያለው የሚታሰርበት ፣የሚገረፍበት እና የሚገደልበት እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጊደና ፤ አሁን ግን ጊዜያዊ አስተዳደሩ ህዝቡ ችግር ውስጥ ነው ታስፈልጉታላችሁ፤ የዴሞክራሲ ምህዳሩንም እናሰፋለን በማለት ተፎካካሪ ፓርቲዎች በመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ላይ እንድንገባ ተደርጓል። ይህ ደግሞ ለትግራይ ክልል ብቻ ሳይሆን ለመላ አገሪቱ ትልቅ እመርታ ነው ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38804
ዞኑ ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የመተከል ዞን ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የዞኑ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል ከመተከል ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሄዷል።
መንግስት ወንጀለኞችን አድኖ ለሀግ ለማቅረብ እያከናወነ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
የመተከል ዞን በርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ የሚኖሩበት ሲሆን በማህበረሰቡ ዘንድ መተሳሰብና አብሮነት መኖሩንም የሀገር ሽማግሌዎቹ አንስተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ጥቃት ፈጻሚዎቹ የጉሙዝን ብሔረሰብ የማይወክሉ ‘የተደራጁ ሽፍቶች’ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህ ሽፍቶች ችግሩ እንዳይከሰት ሲጥሩ በነበሩ የሀገር ሽማግሌዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንም ተናግረዋል።
በጉሙዝ ማህበረሰብ ግጭትን በመፍታት ረገድ ትልቅ ሚና ባላቸው እናቶች ላይ ጭምር ጉዳት ማድረሳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
በእርሻ ኢንቨስትመንት ስም በአካባቢው የተሰማሩ የጽንፈኛው የህወሃት ጁንታ አባላቶች ወጣቶችን ሰብስበው ለጥፋት ተልኮ ሲያሰለጥኑ እንደነበርም ነው የሀገር ሽማግሌዎቹ የተናገሩት።
ይህንን እያወቁ ምንም አይነት ምላሽ ያልሰጡ አመራሮች መኖራቸውንም አንስተዋል። በመሆኑም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቀዋል።
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የመተከል ዞን ከሚታወቅበት የአብሮነት እሴት ባፈነገጠ መልኩ ንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ እጅግ እንዳሳዘናቸው የዞኑ የሀገር ሽማግሌዎች ገለጹ
በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል ከመተከል ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሄዷል።
መንግስት ወንጀለኞችን አድኖ ለሀግ ለማቅረብ እያከናወነ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
የመተከል ዞን በርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ የሚኖሩበት ሲሆን በማህበረሰቡ ዘንድ መተሳሰብና አብሮነት መኖሩንም የሀገር ሽማግሌዎቹ አንስተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ጥቃት ፈጻሚዎቹ የጉሙዝን ብሔረሰብ የማይወክሉ ‘የተደራጁ ሽፍቶች’ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህ ሽፍቶች ችግሩ እንዳይከሰት ሲጥሩ በነበሩ የሀገር ሽማግሌዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንም ተናግረዋል።
በጉሙዝ ማህበረሰብ ግጭትን በመፍታት ረገድ ትልቅ ሚና ባላቸው እናቶች ላይ ጭምር ጉዳት ማድረሳቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
በእርሻ ኢንቨስትመንት ስም በአካባቢው የተሰማሩ የጽንፈኛው የህወሃት ጁንታ አባላቶች ወጣቶችን ሰብስበው ለጥፋት ተልኮ ሲያሰለጥኑ እንደነበርም ነው የሀገር ሽማግሌዎቹ የተናገሩት።
ይህንን እያወቁ ምንም አይነት ምላሽ ያልሰጡ አመራሮች መኖራቸውንም አንስተዋል። በመሆኑም ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባልተወጡ አመራሮች ላይ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቀዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4ሺ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበረከተ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4 ሽህ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በዛሬው እለት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበርክቷል::
በስጦታ መርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም ታደሰ: የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌና ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እንዲሁም የሃይኖት ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል::
የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌ የስጦታ መርሐ ግብሩን በንግግር ሲከፍቱ በዛሬው እለትም የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ኑሮ ከሚመሩ ነዋሪዎች ጋር በዓሉን ለማክበር ታቅዶ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በተሰራው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሐብት በ12ቱም ወረዳዎች በማሰባሰብ ለ4500 ወገኖች ተደራሽ ተደርጏል ብልዋል::
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች : አመራሮች : በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና በበጎ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሐብቶች ለዚህ ስራ ስኬታማነት ለተረባረቡ ሁሉ አቶ አስፋው ምስጋና አቅርበዋል::
በተናጠል ተጉዘን ከሰራናቸው ብዙ ተግባራት ይልቅ ህብረትን ፈጥረን በምክክርና በጋራ የተረባረብንባቸው ጥቂት ስራዎች ፍሬያማ ነበሩ ያሉት አቶ አስፋው፤ ድህነትን ለመቅረፍም ችግረኞችን ከማገዝ ባሻገር ዘላቂ ኑሯቸውን ለማሻሻል የተነደፉ የመንግስት ፕሮግራሞችን በመተግበር ሃገርንም ወገንንም ወደ ለውጥ ምህዋር ውስጥ ማስገባትና ለምናልመው ብልፅግና መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል ነው ያሉት።
በዓሉን በደስታና በፍቅር ከማክበሩ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ለኮሮና ቫይረስ ትኩረት በመስጠትና የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ እንዲሁም ለተቸገሩ ስጦታ በማበርከት እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል::
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው አስተዳደሩ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገዝ ያሳየውን ውጤታማ ተግባር አድንቀው ለዚህ በጎ ስራ የተባበሩና ያስተባበሩ አካላትን አመስግነዋል::
በዓሉን አስመልክቶም በእለቱ ለ149 ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የገንዘብና የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርቷክል::
ከ40 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ታድሰው የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት ተመርቀው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች መሰል የስጦታ መርሐ ግብሮች እስከ በአሉ ዋዜማ ድረስ እንደሚቀጥል አስተዳደሩ አስታውቋል።
********************
(ኢ ፕ ድ)
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለ4 ሽህ 520 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በዛሬው እለት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገና ስጦታ አበርክቷል::
በስጦታ መርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም ታደሰ: የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌና ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እንዲሁም የሃይኖት ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል::
የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ተክሌ የስጦታ መርሐ ግብሩን በንግግር ሲከፍቱ በዛሬው እለትም የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ኑሮ ከሚመሩ ነዋሪዎች ጋር በዓሉን ለማክበር ታቅዶ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በተሰራው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 8 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሐብት በ12ቱም ወረዳዎች በማሰባሰብ ለ4500 ወገኖች ተደራሽ ተደርጏል ብልዋል::
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች : አመራሮች : በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና በበጎ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሐብቶች ለዚህ ስራ ስኬታማነት ለተረባረቡ ሁሉ አቶ አስፋው ምስጋና አቅርበዋል::
በተናጠል ተጉዘን ከሰራናቸው ብዙ ተግባራት ይልቅ ህብረትን ፈጥረን በምክክርና በጋራ የተረባረብንባቸው ጥቂት ስራዎች ፍሬያማ ነበሩ ያሉት አቶ አስፋው፤ ድህነትን ለመቅረፍም ችግረኞችን ከማገዝ ባሻገር ዘላቂ ኑሯቸውን ለማሻሻል የተነደፉ የመንግስት ፕሮግራሞችን በመተግበር ሃገርንም ወገንንም ወደ ለውጥ ምህዋር ውስጥ ማስገባትና ለምናልመው ብልፅግና መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል ነው ያሉት።
በዓሉን በደስታና በፍቅር ከማክበሩ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ለኮሮና ቫይረስ ትኩረት በመስጠትና የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ እንዲሁም ለተቸገሩ ስጦታ በማበርከት እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል::
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪና የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው አስተዳደሩ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገዝ ያሳየውን ውጤታማ ተግባር አድንቀው ለዚህ በጎ ስራ የተባበሩና ያስተባበሩ አካላትን አመስግነዋል::
በዓሉን አስመልክቶም በእለቱ ለ149 ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች የገንዘብና የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርቷክል::
ከ40 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ታድሰው የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት ተመርቀው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች መሰል የስጦታ መርሐ ግብሮች እስከ በአሉ ዋዜማ ድረስ እንደሚቀጥል አስተዳደሩ አስታውቋል።
“አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም”አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
**************************
(ኢ ፕ ድ)
አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል እንደማያስኬድ ዓለምአቀፍ ሕግም እንደማይፈቅድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ።
አምባሳደር ዲና የሳምንቱን አበይት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የዲፕሎማቲክ ክንውኖች አስመል ክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የታላቁን ህዳሴ ግድብ አስመልክተው ፣አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም። ዓለምአቀፍ ሕጉም አይፈቅድም። እንዲህ አይነት ነገሮች ላይ ልዩነቶች አሉ ብለዋል።
የታችኛው ተፋሰስ አገራት በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚያሳዩት የእግር መጎተት ግድቡ ስለሚጎዳቸው ሳይሆን ግድቡን የማስተጓጎል ወይም የማስቆም ዓላማ ስላላቸው እንደሆነም አስታወቀዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከአንድ ወር መቋረጥ በኋላ ባለፈው እሁድ በሶስቱ አገራት የውጭ ጉዳይና የውሃ ሚኒስትሮች አማካኝነት ዳግም መጀመሩን ከሳምንቱ አበይት ዲፕሎማሲያዊ ክንውኖች መካከል አንዱ እንደ ነበርም ጠቁመዋል።
በድርድሩ በደቡብ አፍሪካ አስተባባሪነት በአፍሪካ ኅብረት በተሰየሙ የባለሙያዎች ቡድን የቀረበውን የድርድር ሰነድ ኢትዮጵያና ሱዳን ሲቀበሉት ግብፅ እንዳልተቀበለችው አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38957
**************************
(ኢ ፕ ድ)
አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል እንደማያስኬድ ዓለምአቀፍ ሕግም እንደማይፈቅድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ አስታወቁ።
አምባሳደር ዲና የሳምንቱን አበይት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የዲፕሎማቲክ ክንውኖች አስመል ክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የታላቁን ህዳሴ ግድብ አስመልክተው ፣አስዋንን በግል የሚያስተዳድር አካል ሕዳሴ ግድብን ካንተ ጋር ላስተዳድር ቢል አያስኬድም። ዓለምአቀፍ ሕጉም አይፈቅድም። እንዲህ አይነት ነገሮች ላይ ልዩነቶች አሉ ብለዋል።
የታችኛው ተፋሰስ አገራት በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚያሳዩት የእግር መጎተት ግድቡ ስለሚጎዳቸው ሳይሆን ግድቡን የማስተጓጎል ወይም የማስቆም ዓላማ ስላላቸው እንደሆነም አስታወቀዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ከአንድ ወር መቋረጥ በኋላ ባለፈው እሁድ በሶስቱ አገራት የውጭ ጉዳይና የውሃ ሚኒስትሮች አማካኝነት ዳግም መጀመሩን ከሳምንቱ አበይት ዲፕሎማሲያዊ ክንውኖች መካከል አንዱ እንደ ነበርም ጠቁመዋል።
በድርድሩ በደቡብ አፍሪካ አስተባባሪነት በአፍሪካ ኅብረት በተሰየሙ የባለሙያዎች ቡድን የቀረበውን የድርድር ሰነድ ኢትዮጵያና ሱዳን ሲቀበሉት ግብፅ እንዳልተቀበለችው አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38957