ላለፉት 30 አመታት በኤምባሲ ውስጥ በተከለለ ቦታ ተገድበው የኖሩትን የቀድሞ የደርግ አመራሮችን ከዚህ በላይ ነጻነታቸወን ገድቦ ማቆየት የፍትህ ዓላማን ከማሳካት አንጻር የሚጨምረው ነገር ባለመኖሩ በአመክሮ እንዲፈቱ መደረጉ ተገለጸ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 30 አመታት በኤምባሲ ውስጥ በተከለለ ቦታ ተገድበው የኖሩትን የቀድሞ የደርግ አመራሮችን ከዚህ በላይ ነጻነታቸወን ገድቦ ማቆየት የፍትህ ዓላማን ከማሳካት አንጻር የሚጨምረው ነገር ባለመኖሩ በአመክሮ እንዲፈቱ መደረጉ ተገለጸ።
በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የሙስናና የተደራጁ ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ፍቃዱ ጸጋዬ እንዳስታወቁት፤ ግለሰቦቹ እስካሁን በኤምባሲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ነጻነታቸው ተገድቦ መቆየቱ አስተማሪነት ያለው መሆኑ ከግምት ገብቶ በአመክሮ እንዲለቀቁ ጥያቄውን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በጋራ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም የቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ ወስኖዋል።
እንደ አቶ ፍቃዱ ማብራሪያ፤ ከዚህ በላይ እነኚህን ሰዎች ነጻነታቸውን ገድቦ ማቆየት የፍትህ አላማን ከማሳካትም አንጻር የሚጨምረው ውጤት የማይኖር በመሆኑ፣ እንዲሁም ከፍርደኞቹ እድሜ እና የጤና ሁኔታ አንጻር የሰብዐዊነት እይታን ከግምት በማስገባት ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ ነው የተወሰነው።
በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ ቆይተው የነበሩ የቀድሞ ደርግ አመራሮችም ከ10 ዓመታት በፊት ከእስር ወጥተው ከማህበረሰቡ ጋር እየኖሩ ይገኛሉ ያለው ዓቃቤ ህግ፤ በተቃራኒው በጣልያን ኤምባሲ ውስጥ ተወስነው ለ30 ዓመታት የቆዩት እነኚህ ሰዎች ከመደበኛው የእርምት ስፍራ ባልተናነሰ በተወሰነ አነስተኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ወደ ህክምና ተቋማት እንኳን መውጣት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ መኖራቸው መረጋገጡን አቶ ፍቃዱ ገልጸዋል።
በኤምባሲው ውስጥ በቆዩባቸው አመታት ከመንግስትም ሆነ ከቆዩበት የኤምባሲ ቅጥር ግቢ አሰተዳዳሪ ምንም አይነት እንክብካቤ እና ድጋፍ ሳያገኙ መቆየታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በእስር ቢቆዩ ኖሮ ከሚፈጠርባቸው የመብት ገደብ አንጻር ቢበዛ እንጂ የሚያንስ አንዳልሆነ ግንዛቤ ተወስዶበታልም ነው ያሉት አቶ ፍቃዱ፡፡
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 30 አመታት በኤምባሲ ውስጥ በተከለለ ቦታ ተገድበው የኖሩትን የቀድሞ የደርግ አመራሮችን ከዚህ በላይ ነጻነታቸወን ገድቦ ማቆየት የፍትህ ዓላማን ከማሳካት አንጻር የሚጨምረው ነገር ባለመኖሩ በአመክሮ እንዲፈቱ መደረጉ ተገለጸ።
በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የሙስናና የተደራጁ ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ፍቃዱ ጸጋዬ እንዳስታወቁት፤ ግለሰቦቹ እስካሁን በኤምባሲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ነጻነታቸው ተገድቦ መቆየቱ አስተማሪነት ያለው መሆኑ ከግምት ገብቶ በአመክሮ እንዲለቀቁ ጥያቄውን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በጋራ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም የቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ ወስኖዋል።
እንደ አቶ ፍቃዱ ማብራሪያ፤ ከዚህ በላይ እነኚህን ሰዎች ነጻነታቸውን ገድቦ ማቆየት የፍትህ አላማን ከማሳካትም አንጻር የሚጨምረው ውጤት የማይኖር በመሆኑ፣ እንዲሁም ከፍርደኞቹ እድሜ እና የጤና ሁኔታ አንጻር የሰብዐዊነት እይታን ከግምት በማስገባት ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ ነው የተወሰነው።
በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ ቆይተው የነበሩ የቀድሞ ደርግ አመራሮችም ከ10 ዓመታት በፊት ከእስር ወጥተው ከማህበረሰቡ ጋር እየኖሩ ይገኛሉ ያለው ዓቃቤ ህግ፤ በተቃራኒው በጣልያን ኤምባሲ ውስጥ ተወስነው ለ30 ዓመታት የቆዩት እነኚህ ሰዎች ከመደበኛው የእርምት ስፍራ ባልተናነሰ በተወሰነ አነስተኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ወደ ህክምና ተቋማት እንኳን መውጣት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ መኖራቸው መረጋገጡን አቶ ፍቃዱ ገልጸዋል።
በኤምባሲው ውስጥ በቆዩባቸው አመታት ከመንግስትም ሆነ ከቆዩበት የኤምባሲ ቅጥር ግቢ አሰተዳዳሪ ምንም አይነት እንክብካቤ እና ድጋፍ ሳያገኙ መቆየታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በእስር ቢቆዩ ኖሮ ከሚፈጠርባቸው የመብት ገደብ አንጻር ቢበዛ እንጂ የሚያንስ አንዳልሆነ ግንዛቤ ተወስዶበታልም ነው ያሉት አቶ ፍቃዱ፡፡
በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ የሚፈጸምን ጥቃት አጥብቀን እናወግዛለን- ብልጽግና ፓርቲ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት በማድረግ እየተካሄደ ያለውን ጥቃት አጥብቆ ያወግዛል፡፡
ዜጎችን በማንነት ለይቶ በማጥቃት ምንም አይነት የፖለቲካ ትርፍ ሊገኝ አይችልም፡፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተደጋጋሚ በዜጎች ላይ እየተካሄደ ያለው ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት የትኛውንም የህዝብ ክፍል የማይወክልና ኃላፊነት የማይሰማቸው የግጭት ነጋዴዎች ሴራ መሆኑን መላው የሀገራችን ህዝቦች ሊገነዘቡ ይገባል፡፡
በጨካኝ አረመኔ የጥፋት ኃይሎች ጥቃት በንጹሃን ዜጎች ላይ እየደረሰው ላለው ጉዳት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸን ለዘመናት ተከባብሮ ክፉና ደጉን አብሮ ያሳለፈን ህዝብ በማጋጨት ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚጣጣሩ የውስጥም ሆነ የውጭ ኃይሎች የማይሳካላቸው መሆኑን አጥብቀን ልንገልጽላቸው እንወዳለን፡፡
በዜጎች ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት ውስጥ ተሳትፎ ያላቸውንና ችግሩ እንዲፈታ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ባልተወጡ የስራ ኃላፊዎች ላይ ጥብቅ ፖለቲካዊ፣ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ለፍቶ አዳሪ ንጹሃን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ለይቶ በማጥቃት ሀገርንና ህዝብን ወደ ትርምስ ለማስገባት ተቀናጅተው የሚንቀሳቀሱ የውስጥም ሆነ የውጭ ጨካኝ የጥፋት ኃይሎችን አጥብቆ የሚያወግዝና በእነዚህ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶ የዜጎች ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ ብልጽግና ፓርቲ አጥብቆ የሚታገል መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ብልጽግና ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ በንጹሃን ዜጎች ላይ ማንነትን መሰረት በማድረግ እየተካሄደ ያለውን ጥቃት አጥብቆ ያወግዛል፡፡
ዜጎችን በማንነት ለይቶ በማጥቃት ምንም አይነት የፖለቲካ ትርፍ ሊገኝ አይችልም፡፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተደጋጋሚ በዜጎች ላይ እየተካሄደ ያለው ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት የትኛውንም የህዝብ ክፍል የማይወክልና ኃላፊነት የማይሰማቸው የግጭት ነጋዴዎች ሴራ መሆኑን መላው የሀገራችን ህዝቦች ሊገነዘቡ ይገባል፡፡
በጨካኝ አረመኔ የጥፋት ኃይሎች ጥቃት በንጹሃን ዜጎች ላይ እየደረሰው ላለው ጉዳት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸን ለዘመናት ተከባብሮ ክፉና ደጉን አብሮ ያሳለፈን ህዝብ በማጋጨት ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚጣጣሩ የውስጥም ሆነ የውጭ ኃይሎች የማይሳካላቸው መሆኑን አጥብቀን ልንገልጽላቸው እንወዳለን፡፡
በዜጎች ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት ውስጥ ተሳትፎ ያላቸውንና ችግሩ እንዲፈታ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ባልተወጡ የስራ ኃላፊዎች ላይ ጥብቅ ፖለቲካዊ፣ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ለፍቶ አዳሪ ንጹሃን ዜጎችን በማንነታቸው ብቻ ለይቶ በማጥቃት ሀገርንና ህዝብን ወደ ትርምስ ለማስገባት ተቀናጅተው የሚንቀሳቀሱ የውስጥም ሆነ የውጭ ጨካኝ የጥፋት ኃይሎችን አጥብቆ የሚያወግዝና በእነዚህ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶ የዜጎች ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ ብልጽግና ፓርቲ አጥብቆ የሚታገል መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
ችግሩን ለመፍታት በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግሥት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጸመውን ጥቃት ከማስቆም እና ችግሩን ከመፍታት አንጻር በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግስት ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአከባቢው ያለውን ችግር ከመፍታት አኳያ በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግሥት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፣ “በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል፤ በወገኖቻችን ላይ በተፈጸመው ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ፤ ብለዋል።
ችግሩን በተለያየ መንገድ ለመፍታት ያደረግነው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የጠላቶቻችን ዓላማ በጁንታው ላይ የሠነዘርነውን ብርቱ ኃይል ለመበተን ነው፤ ይህ የሚሳካ አይደለም፣” ብለዋል።
መንግሥትም ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን በመግለጽም፤ “የምንፈልገውን ውጤት ለማግኘት ሁላችንም እንደ ከዚህ ቀደሙ በትኩረትና በኅብረት እንድንሠራ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊት በመተከል ዞን ተገኝተው ከክልሉ አመራሮች፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመወያየት የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫን በማስቀመጥ ለአካባቢው ሰላም ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ ማሳሰባቸው የሚታወስ ነው።
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጸመውን ጥቃት ከማስቆም እና ችግሩን ከመፍታት አንጻር በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግስት ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአከባቢው ያለውን ችግር ከመፍታት አኳያ በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግሥት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፣ “በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል፤ በወገኖቻችን ላይ በተፈጸመው ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ፤ ብለዋል።
ችግሩን በተለያየ መንገድ ለመፍታት ያደረግነው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የጠላቶቻችን ዓላማ በጁንታው ላይ የሠነዘርነውን ብርቱ ኃይል ለመበተን ነው፤ ይህ የሚሳካ አይደለም፣” ብለዋል።
መንግሥትም ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን በመግለጽም፤ “የምንፈልገውን ውጤት ለማግኘት ሁላችንም እንደ ከዚህ ቀደሙ በትኩረትና በኅብረት እንድንሠራ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊት በመተከል ዞን ተገኝተው ከክልሉ አመራሮች፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመወያየት የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫን በማስቀመጥ ለአካባቢው ሰላም ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ ማሳሰባቸው የሚታወስ ነው።
በመተከል እየተፈጸመ ያለው ግድያ በክልሉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እጅጉን መዳከሙን እንደሚያሳይ ኢሰመኮ ተናገረ
*******************************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተበራከተ የመጣው እና ከሰሞኑ ሌሊት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን የሚያሳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ። ኮሚሽኑ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ መሆኑንም ተናግሯል።
ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን ነው። በመሆኑም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ ነው።
በመግለጫው እንደተመላከተው፤ ኢሰመኮ የጥቃቱን ሂደት በተመለከተ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከሚመለከታቸው አካላት እና ከተጎጂዎች ጋር በመነጋገር ሲከታተልና ሲያጣራ ቆይቷል። በኩጂ ቀበሌ ከወረዳው መቀመጫ ከሆነችው ቡለን ከተማ 90 ኪ.ሜ. ርቃ የምትገኝ ሲሆን የሺናሻ፣ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ይኖሩባታል። ለቀበሌው የተመደበ የፖሊስ ወይም የፀጥታ ኃይል አለመኖሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ መሰረት ተረድቷል።
https://www.press.et/Ama/?p=38060
*******************************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተበራከተ የመጣው እና ከሰሞኑ ሌሊት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን የሚያሳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ። ኮሚሽኑ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ መሆኑንም ተናግሯል።
ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን ነው። በመሆኑም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ ነው።
በመግለጫው እንደተመላከተው፤ ኢሰመኮ የጥቃቱን ሂደት በተመለከተ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከሚመለከታቸው አካላት እና ከተጎጂዎች ጋር በመነጋገር ሲከታተልና ሲያጣራ ቆይቷል። በኩጂ ቀበሌ ከወረዳው መቀመጫ ከሆነችው ቡለን ከተማ 90 ኪ.ሜ. ርቃ የምትገኝ ሲሆን የሺናሻ፣ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ይኖሩባታል። ለቀበሌው የተመደበ የፖሊስ ወይም የፀጥታ ኃይል አለመኖሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ መሰረት ተረድቷል።
https://www.press.et/Ama/?p=38060
ፖርት ሱዳንን ለኢትዮጵያ የወጪ ገቢ ንግድ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ ለማድረግ ከፖርት ሱዳን ባለስልጣን መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና አጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ውይይት ተደረገ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ፖርት ሱዳንን ለኢትዮጵያ የወጪ ገቢ ንግድ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ ለማድረግ ከፖርት ሱዳን ባለስልጣን መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና አጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ውይይት መደረጉን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን ፖርት ሱዳንን ለአገራችን የወጪገቢ ንግድ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ በማድረግ ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ምርቶችን በዚሁ ወደብ በመጠቀም ለሰሜንና ምዕራቡ የአገራችን ክፍል ተደራሽ ለማድረግ መሻሻል ስለሚገባቸው ጉዳዮች ከፖርት ሱዳን ባለስልጣን መስሪያ ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም አጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ውይይት ተደርጓል።
በትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን ከሱዳን መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ሚኒስትር፣የማእድንና ኢነርጂ ሚኒስትር፣የሱዳን ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ኃላፊ፣ከሱዳን ባቡር ኮርፖሬሽን እና መንገድ ትራንስፖርት ባለሥልጣን፣ከንግድ ሚኒስቴር እና ጉምሩክ መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች በትራንስፖርት ዘርፍና በተለያዩ መስኮች በጋራና በትብብር ለመስራት ከስምምነት ደርሷል፡፡
ፖርት ሱዳንን ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ ለማድረግ፣በኢትዮጵያ-ሱዳን የምድር ባቡር መስመር ዝርጋታ የመጀመሪያ አዋጭነት ጥናት ሂደት፣በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማጠናከርና በአጋርነት መስራት፣ በየብስ ትራንስፖርት ዘርፍ ያጋጠሙ ማነቆዎችን በጋራ በመፈተሽ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከስምምነት መድረሳቸውን የትራንስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እና የሱዳን ትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ሚ/ር ሃሺም ኢብንኦፍ ሱሌይማን በኢትዮጵያና ሱዳን መካካል በትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት የተደረሰባቸውን ነጥቦች በአፋጣኝ ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያግዝ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ፖርት ሱዳንን ለኢትዮጵያ የወጪ ገቢ ንግድ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ ለማድረግ ከፖርት ሱዳን ባለስልጣን መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና አጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ውይይት መደረጉን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን ፖርት ሱዳንን ለአገራችን የወጪገቢ ንግድ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ በማድረግ ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ምርቶችን በዚሁ ወደብ በመጠቀም ለሰሜንና ምዕራቡ የአገራችን ክፍል ተደራሽ ለማድረግ መሻሻል ስለሚገባቸው ጉዳዮች ከፖርት ሱዳን ባለስልጣን መስሪያ ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም አጓጓዥ ድርጅቶች ጋር ውይይት ተደርጓል።
በትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን ከሱዳን መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ሚኒስትር፣የማእድንና ኢነርጂ ሚኒስትር፣የሱዳን ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ኃላፊ፣ከሱዳን ባቡር ኮርፖሬሽን እና መንገድ ትራንስፖርት ባለሥልጣን፣ከንግድ ሚኒስቴር እና ጉምሩክ መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች በትራንስፖርት ዘርፍና በተለያዩ መስኮች በጋራና በትብብር ለመስራት ከስምምነት ደርሷል፡፡
ፖርት ሱዳንን ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የወደብ አማራጭ ለማድረግ፣በኢትዮጵያ-ሱዳን የምድር ባቡር መስመር ዝርጋታ የመጀመሪያ አዋጭነት ጥናት ሂደት፣በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማጠናከርና በአጋርነት መስራት፣ በየብስ ትራንስፖርት ዘርፍ ያጋጠሙ ማነቆዎችን በጋራ በመፈተሽ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከስምምነት መድረሳቸውን የትራንስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እና የሱዳን ትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ሚ/ር ሃሺም ኢብንኦፍ ሱሌይማን በኢትዮጵያና ሱዳን መካካል በትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት የተደረሰባቸውን ነጥቦች በአፋጣኝ ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያግዝ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
መቐለ ያሉ የመንግስት መስርያቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል ሲሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
👉 ከማረሚያቤት ሆን ተብለው በተለቀቁ የህግ ታራሚዎች ምክንያት በከተማው የፀጥታ ችግር እንዲፈጠር ተደርጓል፤
👉 ጁንታው “ጦርነት አላለቀም” በሚል ወሬ እያስነዛ ህዝቡ ወደ ስራ እንዳይገባ አድርጎታል፤
****************
(ኢ ፕ ድ)
መቐለ ያሉ የመንግስት መስርያቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል ሲሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ዛሬ በሰማዕታት አደራሽ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር ውይይት እያደረጉ ነው።
የዚሁ ውይይት ተሳታፊዎች እንደተናገሩት፤ መቐለ ያሉ የመንግስት መስርያቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል፤ በዚህም ህብረተሰቡ እየተጉላላ ይገኛል።
በሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የደረሰው ክህደትና ጥቃት ያወገዙት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአጭር ጊዜ ህግ የማስከበሩን ስራ በማጠናቀቁ እናመሰግናለን ሲሉም ተናግረዋል።
የህወሓት ጁንታ በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ማረሚያቤቶች ውስጥ የነበሩ የህግ ታራሚዎችን ሆን ብሎ በመቐለ በትኖ ሄዷል ያሉት ተወያዮቹ፤ በእነዚህ ከማረሚያቤት ሆን ተብለው በተለቀቁ የህግ ታራሚዎች ምክንያት በከተማው የፀጥታ ችግር እንዲፈጠር ተደርጓል ሲሉም ነው ያስታወቁት።
የሀሰት ወሬ በመቐለ ከተማ እየተነዛ ህዝቡ እየተሸበረ ስለሆነ አስተዳደሩ ይሄን ያጥራልን ያሉት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ ነጋዴው ከመሃል ሃገር ሸቀጥ እንዳያመጣ “ጦርነት አላለቀም” በሚል ወሬ እየተነዛ ወደ ስራ እንዳይገባም አድርገውታል ነው ያሉት።
በአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ጊዚያዊ አስተዳደሩንም ሆነ ህዝቡን ማገዝ አለበት ያሉት ተወያዮቹ፤ በደቡብ ትግራይ እና ምዕራብ ትግራይ አካባቢ ያሉ ጉዳዮች በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
የሰሜን ዕዝ አዛዡ ጄነራል በላይ ስዩም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መከላከያ የአገር ዳር ድንበርን የሚያስከብር ሃይል ነው። ነገር ግን ጁንታው የገደለው ይሄንን ሃይል ነው በማለት የተፈጸመውን ክህደትና ግፍ ለተወያዮቹ አብራርተዋል።
“እንደመከላከያ ጓዶቻችን በጁንታው ተገድለዋል፣ የሰራዊቱ ንብረት ተዘርፏል፤ እንደ አገርም በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ የሆነ ተፅእኖ ተፈጥሯል” ያሉት ጄነራሉ፤ የዘጠና አመት አዛውንቶች መጥተው ይመሩናል ብላችሁ ተስፋ እንዳታደርጉ፤ በእርግጠኝነት የምነግራችሁ ጁንታው ከዚህ በሁዋላ አይመለስም፤ ስለዚህ ተረጋግታችሁ ጊዚያዊ አስተዳደሩን ማገዝ አለባችሁ” ሲሉም ለመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፣ የመቐለ ከንቲባ አቶ ኣታኽልቲ ሃይለስላሴ እና የሰሜን እዝ አዛዥ ጀነራል በላይ ስዩም መገኘታቸውን በመቀሌ ከተማ ያለው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ ያደረሰን መረጃ ያሳያል።
👉 ከማረሚያቤት ሆን ተብለው በተለቀቁ የህግ ታራሚዎች ምክንያት በከተማው የፀጥታ ችግር እንዲፈጠር ተደርጓል፤
👉 ጁንታው “ጦርነት አላለቀም” በሚል ወሬ እያስነዛ ህዝቡ ወደ ስራ እንዳይገባ አድርጎታል፤
****************
(ኢ ፕ ድ)
መቐለ ያሉ የመንግስት መስርያቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል ሲሉ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ዛሬ በሰማዕታት አደራሽ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር ውይይት እያደረጉ ነው።
የዚሁ ውይይት ተሳታፊዎች እንደተናገሩት፤ መቐለ ያሉ የመንግስት መስርያቤቶች ህዝብ እንዳያገለግሉ በህወሓት ጁንታ ሆን ተብለው እንዲዘረፉና እንዲወድሙ ተደርጓል፤ በዚህም ህብረተሰቡ እየተጉላላ ይገኛል።
በሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የደረሰው ክህደትና ጥቃት ያወገዙት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአጭር ጊዜ ህግ የማስከበሩን ስራ በማጠናቀቁ እናመሰግናለን ሲሉም ተናግረዋል።
የህወሓት ጁንታ በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ማረሚያቤቶች ውስጥ የነበሩ የህግ ታራሚዎችን ሆን ብሎ በመቐለ በትኖ ሄዷል ያሉት ተወያዮቹ፤ በእነዚህ ከማረሚያቤት ሆን ተብለው በተለቀቁ የህግ ታራሚዎች ምክንያት በከተማው የፀጥታ ችግር እንዲፈጠር ተደርጓል ሲሉም ነው ያስታወቁት።
የሀሰት ወሬ በመቐለ ከተማ እየተነዛ ህዝቡ እየተሸበረ ስለሆነ አስተዳደሩ ይሄን ያጥራልን ያሉት የከተማዋ ነዋሪዎች፤ ነጋዴው ከመሃል ሃገር ሸቀጥ እንዳያመጣ “ጦርነት አላለቀም” በሚል ወሬ እየተነዛ ወደ ስራ እንዳይገባም አድርገውታል ነው ያሉት።
በአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ጊዚያዊ አስተዳደሩንም ሆነ ህዝቡን ማገዝ አለበት ያሉት ተወያዮቹ፤ በደቡብ ትግራይ እና ምዕራብ ትግራይ አካባቢ ያሉ ጉዳዮች በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
የሰሜን ዕዝ አዛዡ ጄነራል በላይ ስዩም በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መከላከያ የአገር ዳር ድንበርን የሚያስከብር ሃይል ነው። ነገር ግን ጁንታው የገደለው ይሄንን ሃይል ነው በማለት የተፈጸመውን ክህደትና ግፍ ለተወያዮቹ አብራርተዋል።
“እንደመከላከያ ጓዶቻችን በጁንታው ተገድለዋል፣ የሰራዊቱ ንብረት ተዘርፏል፤ እንደ አገርም በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ የሆነ ተፅእኖ ተፈጥሯል” ያሉት ጄነራሉ፤ የዘጠና አመት አዛውንቶች መጥተው ይመሩናል ብላችሁ ተስፋ እንዳታደርጉ፤ በእርግጠኝነት የምነግራችሁ ጁንታው ከዚህ በሁዋላ አይመለስም፤ ስለዚህ ተረጋግታችሁ ጊዚያዊ አስተዳደሩን ማገዝ አለባችሁ” ሲሉም ለመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፣ የመቐለ ከንቲባ አቶ ኣታኽልቲ ሃይለስላሴ እና የሰሜን እዝ አዛዥ ጀነራል በላይ ስዩም መገኘታቸውን በመቀሌ ከተማ ያለው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ ያደረሰን መረጃ ያሳያል።
ምርጫ ቦርድ የመጪውን 6ተኛ አገራዊ የምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጪውን 6ተኛ አገራዊ የምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ።
በዚህም መሰረት ግንቦት 28 ቀን ምርጫው እንደሚካሄድ የጊዜ ሰሌዳው ያሳያል።
የአዲስ አበባ ከተማ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 05 ቀን 2013 ዓ.ም፤
ግንቦት 28 እና 29 ቀን 2013 ዓ.ም ለአገር አቀፍ ምርጫ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤት የሚገለጽባቸው ቀናት ናቸው ተብሏል፤
የምረጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ ከየካቲት 08 ቀን እስከ ግንቦት 23 ቀን 2013 ዓ.ም ይካሄዳል፤
የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 22 እስከ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም ይከናወናል፤
ግንቦት 29 እስከ ሴነ 21 ቀን 2013 ዓ.ም አጠቃላይ የምርጫ ውጤት በቦርዱ የሚገለጽበት ጊዜ ይሆናል፤
***********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጪውን 6ተኛ አገራዊ የምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ።
በዚህም መሰረት ግንቦት 28 ቀን ምርጫው እንደሚካሄድ የጊዜ ሰሌዳው ያሳያል።
የአዲስ አበባ ከተማ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 05 ቀን 2013 ዓ.ም፤
ግንቦት 28 እና 29 ቀን 2013 ዓ.ም ለአገር አቀፍ ምርጫ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤት የሚገለጽባቸው ቀናት ናቸው ተብሏል፤
የምረጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ ከየካቲት 08 ቀን እስከ ግንቦት 23 ቀን 2013 ዓ.ም ይካሄዳል፤
የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 22 እስከ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም ይከናወናል፤
ግንቦት 29 እስከ ሴነ 21 ቀን 2013 ዓ.ም አጠቃላይ የምርጫ ውጤት በቦርዱ የሚገለጽበት ጊዜ ይሆናል፤
የትግራይ ህዝብ የህወሓት ጁንታ ተመልሶ ይመጣል ከሚል ሃሳብ መውጣት እንዳለበት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር አብረሀም በላይ አስታወቁ
👉 ጃንሆይ ከወረዱ በኋላ ህዝቡ ይመለሳሉ ብሎ ሲጠብቅ ነበር፤ ደርግም ከወደቀ በኋላ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው ነበር፤ አሁንም እንደዛ እየጠበቀ ያለ ሰው አለ፤
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትግራይ ህዝብ የህወሓት ጁንታ ተመልሶ ይመጣል ከሚል ሃሳብ መውጣት እንዳለበት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር አብረሀም በላይ አስታወቁ።
የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በዛሬው እለት እያደረጉት ያለው ውይይት እንደቀጠለ ነው።
በዚሁ መድረክ ላይ ለተነሱ የከተማዋ ነዋሪዎች ምላሽ እየሰጡ ካሉት አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሩ ዶ/ር አብረሀም በላይ እንዳሉት፤ በከተማዋም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ላይ የህወሓት ጁንታን በተመለከተ “ተመልሰው ይመጣሉ” የሚል የሀሰት ወሬ እየተሰራጨ ይገኛል። ይህ የተሳሳተ መሆኑን ህዝቡ ማወቅ አለበት።
ህዝባችን በውሸት ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶ/ር አብረሃም፤ ድሮ ጃንሆይ ከወረዱ በኋላ ህዝቡ ይመለሳሉ ብሎ ሲጠብቅ ነበር፤ ደርግም ከወደቀ በኋላ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው ነበር። አሁንም እንደዛ እየጠበቀ ያለ ሰው አለ። ይህ መሆን የለበትም” ሲሉ ተወያዮቹ ላቀረቡት ጥያቄ መልስ ሰጥተዋል።
የመንግስት ሰራተኛ ማለት የህዝብ አገልጋይ ነው፤ ሁሉም ወደ ስራው ገብቶ ከልብ ማገልገል አለበት ያሉት ደግሞ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደ/ር ሙሉ ነጋ ናቸው።
“በፊት ህዝብ ያሰቃዩ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር የሌላቸው ማልያ ቀይረው ወደ አመራር እንዳይመጡ ህዝቡ ሊያግዘን ይገባል” ሲሉም ነው ዶ/ር ሙሉ ለተወያዮቹ የገለጹት።
ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችም በህግ አግባብ ምላሽ እንደሚያገኙ ዶ/ር ሙሉ አብራርተዋል።
ዶ/ር ሙሉ አያይዘውም፤ “የትግራይን ህዝብ ከምትናገረው ስትሰማው ብዙ ትምህርት ትወስዳለህ። እኛ እየሰራን ነው፤ የቀረውን ህዝቡ ሊያግዘን ይገባል። ህዝባችን ያለንን ልንሰማ፣ ራሱ የፈለገውንም ሊመርጥ ይገባል” ሲሉ ለተወያዮቹ ተናግረዋል።
👉 ጃንሆይ ከወረዱ በኋላ ህዝቡ ይመለሳሉ ብሎ ሲጠብቅ ነበር፤ ደርግም ከወደቀ በኋላ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው ነበር፤ አሁንም እንደዛ እየጠበቀ ያለ ሰው አለ፤
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትግራይ ህዝብ የህወሓት ጁንታ ተመልሶ ይመጣል ከሚል ሃሳብ መውጣት እንዳለበት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር አብረሀም በላይ አስታወቁ።
የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በዛሬው እለት እያደረጉት ያለው ውይይት እንደቀጠለ ነው።
በዚሁ መድረክ ላይ ለተነሱ የከተማዋ ነዋሪዎች ምላሽ እየሰጡ ካሉት አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሩ ዶ/ር አብረሀም በላይ እንዳሉት፤ በከተማዋም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ላይ የህወሓት ጁንታን በተመለከተ “ተመልሰው ይመጣሉ” የሚል የሀሰት ወሬ እየተሰራጨ ይገኛል። ይህ የተሳሳተ መሆኑን ህዝቡ ማወቅ አለበት።
ህዝባችን በውሸት ሊደናገር አይገባም ያሉት ዶ/ር አብረሃም፤ ድሮ ጃንሆይ ከወረዱ በኋላ ህዝቡ ይመለሳሉ ብሎ ሲጠብቅ ነበር፤ ደርግም ከወደቀ በኋላ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው ነበር። አሁንም እንደዛ እየጠበቀ ያለ ሰው አለ። ይህ መሆን የለበትም” ሲሉ ተወያዮቹ ላቀረቡት ጥያቄ መልስ ሰጥተዋል።
የመንግስት ሰራተኛ ማለት የህዝብ አገልጋይ ነው፤ ሁሉም ወደ ስራው ገብቶ ከልብ ማገልገል አለበት ያሉት ደግሞ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደ/ር ሙሉ ነጋ ናቸው።
“በፊት ህዝብ ያሰቃዩ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር የሌላቸው ማልያ ቀይረው ወደ አመራር እንዳይመጡ ህዝቡ ሊያግዘን ይገባል” ሲሉም ነው ዶ/ር ሙሉ ለተወያዮቹ የገለጹት።
ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችም በህግ አግባብ ምላሽ እንደሚያገኙ ዶ/ር ሙሉ አብራርተዋል።
ዶ/ር ሙሉ አያይዘውም፤ “የትግራይን ህዝብ ከምትናገረው ስትሰማው ብዙ ትምህርት ትወስዳለህ። እኛ እየሰራን ነው፤ የቀረውን ህዝቡ ሊያግዘን ይገባል። ህዝባችን ያለንን ልንሰማ፣ ራሱ የፈለገውንም ሊመርጥ ይገባል” ሲሉ ለተወያዮቹ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች መሰራታቸው የቱሪስት ፍሰቱን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምረው ተገለፀ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች መሰራታቸው የቱሪስት ፍሰቱን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምረው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ቴድሮስ ሀብታሙ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ መንግስት በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰራው ያለው አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች ወደ ፊት በከፍተኛ ሁኔታ የቱሪስት ፍስቱን ላይ ለውጥ ያመጣሉ።
የቱሪዝም ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፓለቲካዊ ጠቀሜታዎች ከሚያሳድጉ የልማት ዘርፎች አንዱና ዋንኛው ነው ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት እየተሻሻለ መምጣቱ ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋፆ አለውም ብለዋል፡፡
በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮና ቨይረስ ለቱሪዝም ዘርፉ ፈታኝ ሆኖበታል ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ አሁን ላይ ዘርፉ እንዲያገግም በሀገር ውስጥ ቱሪዝሙ ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝሙ በፍጥነት ማገገም ስለሚችል በዚህ ላይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ላይ ያለው ግንዛቤ አናሳ ነው ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ ይህንን እወነታ ለመቀየር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል፡፡
እንድ አቶ ሀብታሙ ገለጻ፤ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። ይህን በማሳደግ ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሀገሮች ተርታ ለመቀላቀል የምታደርገውን እንቅስቃሴ መደገፍ ይገባል፡፡
በተለይም አሁኑ ወቅት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የግንኙነት መሰረተ ልማቶች እና ሌሎች የዘርፉን መልካም አጋጣሚዎች በመጠቀም የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በመኖሪያ አካባቢዎች፣ በትምህርት ቤቶች እና በሥራ አካባቢዎች በስፋት በማስተዋወቅና የማህበረሰቡን የጉብኝት ባህል ማሳደግ የዘርፉን ጠቀሜታዎች ማሳደግ ከምን ጊዜው በላይ አስፈላጊ ነው ብለዋል አቶ ሀብታሙ፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚያዊ እድገት በማመጣጠን የማህበረሰብ ክፍሎችን የገቢ ምንጭ እና የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፆ አለውም ብለዋል፡፡
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች መሰራታቸው የቱሪስት ፍሰቱን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምረው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።
በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ቴድሮስ ሀብታሙ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ መንግስት በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰራው ያለው አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች ወደ ፊት በከፍተኛ ሁኔታ የቱሪስት ፍስቱን ላይ ለውጥ ያመጣሉ።
የቱሪዝም ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፓለቲካዊ ጠቀሜታዎች ከሚያሳድጉ የልማት ዘርፎች አንዱና ዋንኛው ነው ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት እየተሻሻለ መምጣቱ ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋፆ አለውም ብለዋል፡፡
በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮና ቨይረስ ለቱሪዝም ዘርፉ ፈታኝ ሆኖበታል ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ አሁን ላይ ዘርፉ እንዲያገግም በሀገር ውስጥ ቱሪዝሙ ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝሙ በፍጥነት ማገገም ስለሚችል በዚህ ላይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ላይ ያለው ግንዛቤ አናሳ ነው ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ ይህንን እወነታ ለመቀየር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል፡፡
እንድ አቶ ሀብታሙ ገለጻ፤ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። ይህን በማሳደግ ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሀገሮች ተርታ ለመቀላቀል የምታደርገውን እንቅስቃሴ መደገፍ ይገባል፡፡
በተለይም አሁኑ ወቅት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የግንኙነት መሰረተ ልማቶች እና ሌሎች የዘርፉን መልካም አጋጣሚዎች በመጠቀም የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በመኖሪያ አካባቢዎች፣ በትምህርት ቤቶች እና በሥራ አካባቢዎች በስፋት በማስተዋወቅና የማህበረሰቡን የጉብኝት ባህል ማሳደግ የዘርፉን ጠቀሜታዎች ማሳደግ ከምን ጊዜው በላይ አስፈላጊ ነው ብለዋል አቶ ሀብታሙ፡፡
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚያዊ እድገት በማመጣጠን የማህበረሰብ ክፍሎችን የገቢ ምንጭ እና የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፆ አለውም ብለዋል፡፡
“ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና የሚተገብሩት አንድ ሊሆን ይገባል” ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር
***************************
(ኢ ፕ ድ)
ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ለማድረግ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት አንድ አይነት ሊሆን ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ፡፡
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ባለው ሁኔታ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት ለየቅል ሆኖ ይታያል፡፡ ይህ ደግሞ አንዳንድ ፓርቲዎች ሲመቻቸው የሃይል አማራጭን በሌላ ጊዜ ደግሞ ሰላማዊ መስለው እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ሕጉን እና የሥነ ምግባር ደንቡን አክብሮ መንቀሳቀስ ይገባቸዋል፡፡ በዚህም ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ጊዜ እና በደህረ ምርጫ በሀገሪቱ ማንኛውም አይነት ግጭት እንዳይከሰት ከማድረግ አንፃር ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የራሳቸውን ሚና መጫወት ይገባቸዋል፡፡
ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን በመሸጥ ህዝቡን አሳምነውእንዲመረጡ ለማድረግ በምርጫ ሕጉ እና በምርጫ ሥነ ምግባሩ መሰረት ሊንቀሳቀሱ ይገባል የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ፤ በዚህም ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ ማድርግ እንደሚቻል ጠቁመዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38146
***************************
(ኢ ፕ ድ)
ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ለማድረግ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት አንድ አይነት ሊሆን ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ፡፡
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ባለው ሁኔታ ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚናገሩት እና በተጨባጭ የሚተገብሩት ለየቅል ሆኖ ይታያል፡፡ ይህ ደግሞ አንዳንድ ፓርቲዎች ሲመቻቸው የሃይል አማራጭን በሌላ ጊዜ ደግሞ ሰላማዊ መስለው እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ሕጉን እና የሥነ ምግባር ደንቡን አክብሮ መንቀሳቀስ ይገባቸዋል፡፡ በዚህም ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ጊዜ እና በደህረ ምርጫ በሀገሪቱ ማንኛውም አይነት ግጭት እንዳይከሰት ከማድረግ አንፃር ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የራሳቸውን ሚና መጫወት ይገባቸዋል፡፡
ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን በመሸጥ ህዝቡን አሳምነውእንዲመረጡ ለማድረግ በምርጫ ሕጉ እና በምርጫ ሥነ ምግባሩ መሰረት ሊንቀሳቀሱ ይገባል የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ፤ በዚህም ቀጣዩን ምርጫ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ ማድርግ እንደሚቻል ጠቁመዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38146
የ2013 በጀት ዓመት የችግኝ ተከላ ዝግጅት መርሀ ግብር ላይ ምክክር እየተደረገ ነው
***************************
(ኢ ፕ ድ)
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ውጤትና በቀጣይ ሊሰሩ በታቀዱ ስራዎችን አስመልክቶ በአዳማ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት ብቻ 9 ቢሊዮን ያህል ችግኞችን መትከል የተቻለ ሲሆን፤ እ.አ.አ እስከ 2022 ድረስ ሀያ ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተጥሎ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
በዚሁ አጠቃላይ ማዕቀፍ መሠረት እስካሁን በተተከሉ ችግኞች እንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎች ላይ የ2013 በጀት ዓመት የችግኝ ተከላ ዝግጅት መርሀ ግብር ላይ ምክክር እየተደረገ ነው።
የአካባቢ፣ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ፈቃዱ በየነ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ በተለይ የኮቪድ 19 ወሩርሽኝ ኢ-ተገማች ተጽእኖን በመቋቋም ችግኝ ተከላውን ተፈጻሚ ማድረግ ተችሏል። ይህም ራስን ከወረርሽኙ እየተከላከሉ ማምረት እንደሚቻል አመላክቷል።
በቀጣይም የማይበገር የተቀናጀ የአረንጓዴ ልማትን ለማስፋት ይሰራል።
በምክክር መድረኩ፤ ስራውን በአቢይና በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ የሚመሩና የሚያስተባብሩ፣ ከፌዴራልና ከክልል መንግስታት የዘርፍ መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
***************************
(ኢ ፕ ድ)
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ውጤትና በቀጣይ ሊሰሩ በታቀዱ ስራዎችን አስመልክቶ በአዳማ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት ብቻ 9 ቢሊዮን ያህል ችግኞችን መትከል የተቻለ ሲሆን፤ እ.አ.አ እስከ 2022 ድረስ ሀያ ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተጥሎ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
በዚሁ አጠቃላይ ማዕቀፍ መሠረት እስካሁን በተተከሉ ችግኞች እንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎች ላይ የ2013 በጀት ዓመት የችግኝ ተከላ ዝግጅት መርሀ ግብር ላይ ምክክር እየተደረገ ነው።
የአካባቢ፣ የደንና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ፈቃዱ በየነ በመድረኩ እንደተናገሩት፤ በተለይ የኮቪድ 19 ወሩርሽኝ ኢ-ተገማች ተጽእኖን በመቋቋም ችግኝ ተከላውን ተፈጻሚ ማድረግ ተችሏል። ይህም ራስን ከወረርሽኙ እየተከላከሉ ማምረት እንደሚቻል አመላክቷል።
በቀጣይም የማይበገር የተቀናጀ የአረንጓዴ ልማትን ለማስፋት ይሰራል።
በምክክር መድረኩ፤ ስራውን በአቢይና በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ የሚመሩና የሚያስተባብሩ፣ ከፌዴራልና ከክልል መንግስታት የዘርፍ መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ስኳር ኮርፖሬሽን እና ሜቴክን ያሽመደመደው የቀድሞው መንግሥት ደካማ አሠራር ታክሎበት ስለመሆኑ ተነገረ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ስኳር ኮርፖሬሽን እና ሜቴክን ያሽመደመደው የቀድሞው መንግሥት ደካማ አሠራር ጭምር መሆኑን በሜቴክ እና በስኳር ኮርፖሬሽን ቦርድ አባልነትና አማካሪነት ሲሰሩ የነበሩ ምሁር አስታወቁ፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ስኳር ለማምረት እያደረገችው ያለው ጥረት ከኋላቀርነት ያልተላቀቀ መሆኑም ተገልጿል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኬሚካል ምህንድስና መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር በላይ ወልደየስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በኢትዮጵያ ስኳር ለማምረት የሚያስችላት ሰፊ አቅም እንዲሁም ከ80 በመቶ በላይ አርሷደር የሚፈልገውን ማዳበሪያን ለማምረት የምትችልበት አቅም ያላት ቢሆንም፤ የስኳር ምርቱ ኋላ ቀር፣ ማዳበሪያ ለማምረት ያደረገችው ጥረትም በግንባታ ደረጃ መክኖ የቀረ ሆኗል፡፡ በመሆኑም የስኳር ምርቱም ሆነ የያዩ ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ለኪሣራ የተዳረገው ተገቢውን አሰራር መከተል ባለመቻሉ ነው፡፡
እንደ ፕሮፌሰር በላይ ገለፃ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሸንኮራ ተክልን ለማልማት የሚያስችል የአየር ፀባይና ሰፋፊ ተፋሰሶች ያሉባት ሀገር ናት፡፡ ይሁንና ካላት ምቹ ሁኔታ በጣም ባነሰ ከ50 ዓመት ጀምሮ ስኳርን ከሸንኮራ ተክል እያመረተች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ እያመረተች ያለው በዋናነት ስኳር ሲሆን፤ በሁለት ፋብሪካዎች በጣም በጥቂቱ ለተሽከርካሪ ነዳጅ የሚሆነው ‹‹ኤታኖል›› ይመረታል፡፡ ሆኖም ይህ አሠራር ወደ ኋላ የቀረ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=38171
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ስኳር ኮርፖሬሽን እና ሜቴክን ያሽመደመደው የቀድሞው መንግሥት ደካማ አሠራር ጭምር መሆኑን በሜቴክ እና በስኳር ኮርፖሬሽን ቦርድ አባልነትና አማካሪነት ሲሰሩ የነበሩ ምሁር አስታወቁ፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ስኳር ለማምረት እያደረገችው ያለው ጥረት ከኋላቀርነት ያልተላቀቀ መሆኑም ተገልጿል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኬሚካል ምህንድስና መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር በላይ ወልደየስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በኢትዮጵያ ስኳር ለማምረት የሚያስችላት ሰፊ አቅም እንዲሁም ከ80 በመቶ በላይ አርሷደር የሚፈልገውን ማዳበሪያን ለማምረት የምትችልበት አቅም ያላት ቢሆንም፤ የስኳር ምርቱ ኋላ ቀር፣ ማዳበሪያ ለማምረት ያደረገችው ጥረትም በግንባታ ደረጃ መክኖ የቀረ ሆኗል፡፡ በመሆኑም የስኳር ምርቱም ሆነ የያዩ ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ለኪሣራ የተዳረገው ተገቢውን አሰራር መከተል ባለመቻሉ ነው፡፡
እንደ ፕሮፌሰር በላይ ገለፃ፤ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሸንኮራ ተክልን ለማልማት የሚያስችል የአየር ፀባይና ሰፋፊ ተፋሰሶች ያሉባት ሀገር ናት፡፡ ይሁንና ካላት ምቹ ሁኔታ በጣም ባነሰ ከ50 ዓመት ጀምሮ ስኳርን ከሸንኮራ ተክል እያመረተች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ እያመረተች ያለው በዋናነት ስኳር ሲሆን፤ በሁለት ፋብሪካዎች በጣም በጥቂቱ ለተሽከርካሪ ነዳጅ የሚሆነው ‹‹ኤታኖል›› ይመረታል፡፡ ሆኖም ይህ አሠራር ወደ ኋላ የቀረ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=38171
«የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር» -የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች
*******************
(ኢ ፕ ድ)
«የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ትናንት ተወያይቷል።
የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች «የህወሓት ቡድን» በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት ያወገዙ ሲሆን፤ ቡድኑ በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የትግራይን ሕዝብ የማይወክልና ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ድርጊት መሆኑንም ነው የተናገሩት።
ከዚህ ቀደም የፓርቲና የመንግሥት ሥራ ተደበላልቆእንደነበረ ያስታወሱት ነዋሪዎቹ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከዚህ ተምሮ ማስተካከል እንዳለበት የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ «የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ብለዋል። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ሕዝባዊ ፖሊሶች በአግባቡ ተደራጅተው ወደ ሥራ እንዲገቡም ጠይቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38227
*******************
(ኢ ፕ ድ)
«የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ትናንት ተወያይቷል።
የመድረኩ ተሳታፊ የነበሩት የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች «የህወሓት ቡድን» በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት ያወገዙ ሲሆን፤ ቡድኑ በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የትግራይን ሕዝብ የማይወክልና ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ድርጊት መሆኑንም ነው የተናገሩት።
ከዚህ ቀደም የፓርቲና የመንግሥት ሥራ ተደበላልቆእንደነበረ ያስታወሱት ነዋሪዎቹ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከዚህ ተምሮ ማስተካከል እንዳለበት የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ «የትግራይ ሕዝብና ህወሓት አንድ ሆነው አያውቁም፤ ህወሓት ሳይፈጠር የትግራይ ሕዝብ ነበር ወደ ፊትም ይኖራል» ብለዋል። በከተማዋ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ሕዝባዊ ፖሊሶች በአግባቡ ተደራጅተው ወደ ሥራ እንዲገቡም ጠይቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38227
«ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ ነው» ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ መሆኑ፤ በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት እንደሚለውጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አሳሰቡ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በቀን፣ በማታ ያሰለጠናቸውን 4ሺህ 87 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎቹን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሰላም ሚኒስትርና ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በተገኙበት ትናንት አስመርቋል።
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት እንደተናገሩት፤ ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ ነው። በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት ይለወጣል። እኔ ላይ አይደርስም ማለት የዋህነት ነው፤ ይህንን ደግሞ ከሌሎች ሀገሮች መማር ይገባል።
በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ንፁሃን ዜጎቻችን እና ለፍቶ አደር ሕዝባችን በማንነት፣ በዘር እና በሃይማኖት ምክንያት ውድ ሕይወታቸውን እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ እያጡ መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቷ፤ በሕይወት የመኖር መብትን የቀደመ ሌላ መብት ባለመኖሩ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል ንፁሃን ሕይወታቸውን እንዲያጡ ማንም መፍቀድ እንደሌለበት ተናግረዋል።
ከተደገሰልን እልቂት ለማዳን ሕግን የማስከበር ተግባራት በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ ለሁላችንም ተስፋ ሰጪ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፤ ሞትን እና ቀውስን የሚደግሱልን እንዳሉ አይተናል እያየንም ነው፤ በታሪካችን የሀገራችንን ኅልውናን የሚፈታተኑ አደጋዎች ጥለውብን ካለፉት ጥቁር ጠባሳዎች ተገቢውን ትምህርት ወስደን ማንኛውንም ስጋት አራግፈን በጋራ መነሳት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38229
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ መሆኑ፤ በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት እንደሚለውጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አሳሰቡ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በቀን፣ በማታ ያሰለጠናቸውን 4ሺህ 87 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎቹን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሰላም ሚኒስትርና ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በተገኙበት ትናንት አስመርቋል።
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት እንደተናገሩት፤ ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለግለሰብ እና ለቡድን ጥቅም ሲባል በእሳት መጫወት አደጋው ከፍተኛ ነው። በእሳት መጫወቱ ካልተጠነቀቁ ማንንም ወደማይምር ሰደድ እሳት ይለወጣል። እኔ ላይ አይደርስም ማለት የዋህነት ነው፤ ይህንን ደግሞ ከሌሎች ሀገሮች መማር ይገባል።
በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ንፁሃን ዜጎቻችን እና ለፍቶ አደር ሕዝባችን በማንነት፣ በዘር እና በሃይማኖት ምክንያት ውድ ሕይወታቸውን እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ እያጡ መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቷ፤ በሕይወት የመኖር መብትን የቀደመ ሌላ መብት ባለመኖሩ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል ንፁሃን ሕይወታቸውን እንዲያጡ ማንም መፍቀድ እንደሌለበት ተናግረዋል።
ከተደገሰልን እልቂት ለማዳን ሕግን የማስከበር ተግባራት በተሳካ ሁኔታ መካሄዱ ለሁላችንም ተስፋ ሰጪ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፤ ሞትን እና ቀውስን የሚደግሱልን እንዳሉ አይተናል እያየንም ነው፤ በታሪካችን የሀገራችንን ኅልውናን የሚፈታተኑ አደጋዎች ጥለውብን ካለፉት ጥቁር ጠባሳዎች ተገቢውን ትምህርት ወስደን ማንኛውንም ስጋት አራግፈን በጋራ መነሳት አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38229
የትግራይ ወጣት በኢትዮጵያዊነቱ እንዲደራደር ሁለት አመት መርዝ ተዝርቶበታል፣
ከሁሉም ወንድም ብሄር ብሄረሰብ እንዲጣላ ጁንታው ሰርቷል፤
የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር የማቀራረብ ስራ ሊሰራ ይገባል
- የመቀሌ ከተማ ወጣቶች
****************^
(ኢ.ፕ.ድ)
የመቐለ ከተማ ወጣቶች በከተማዋ ፀጥታ እና መረጋጋት ዙሪያ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ዛሬ እያካሄዱ ነው።
በከተማው እየተነዛ ያለው የውሸት ወሬዎችን ሳይሰሙ ስለ ከተማው ፀጥታ ለመወያየት ወደ ውይይቱ የመጡ ወጣቶችን የከተማዋ ከንቲባ አቶ አታክልቲ ሃይለስላሴ አመስግነዋል።
ውይይቱን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር መሉ ነጋ፣ የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የመቐለ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ሃይለስላሴ እየመሩ ናቸው።
በመቐለ ከተማ ያጋጠመው ዝርፊያ ከማረሚያቤት በተለቀቁ ታራሚዎች እና ሌሎች ሌቦች እንደሆነ ዶ/ር መሉ ለተወያዮቹ አብራርተዋል።
የክልሉም ሆነ የከተማዋ ግዚያዊ አስተዳደር ለፀጥታ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሰራበት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል።
በመቐለ ከተማ የተበተነ የጦር መሳርያ እንዳለ እና በሰላማዊ መንገድ ወደ ፀጥታ አካላት ማስረከብ እንደሚገባ ዶ/ር ሙሉ አስታውቀዋል።
የከተማዋ ወጣቶች የውሸት ወሬዎችን መታገል እንዳለባቸው ጨምረው ገልፀዋል።
ጁንታው የከተማዋ መሰረተ ልማት እንዲወድም ያደረገ ሲሆን የፌደራል መንግስት ባፋጣኝ መሰረተ ልማቱ እየመለሰ መሆኑን ዶ/ር ሙሉ ነጋ ገልፀዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ "ሌቦችም ከኛው፣ የሚሰረቀውም የኛው ስለሆነ ሁላችንም ፀጥታችን ማስከበር አለብን" ሲሉ ተናግረዋል።
በየሰፈሩ የውሸት ወሬዎች የሚፈበርኩ ሰዎች ሆነ በውጪ ሆነው ህዝብ እያደናገሩ ህዝቡ እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ ሚዲያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣቶቹ ጠይቀዋል።
"የትግራይ ወጣት በኢትዮጵያዊነቱ እንዲደራደር ሁለት አመት መርዝ ተዝርቶለታል፣ ከሁሉም ወንድም ብሄር ብሄረሰብ እንዲጣላ ጁንታው ሰርቷል። የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር የማቀራረብ ስራ ሊሰራ ይገባል" ሲሉ መናገራቸውን ውይይቱን እየተከታተለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ አስታውቋል።
በአማንመስፍን ሚካኤል
- ፎቶ ፋይል
ከሁሉም ወንድም ብሄር ብሄረሰብ እንዲጣላ ጁንታው ሰርቷል፤
የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር የማቀራረብ ስራ ሊሰራ ይገባል
- የመቀሌ ከተማ ወጣቶች
****************^
(ኢ.ፕ.ድ)
የመቐለ ከተማ ወጣቶች በከተማዋ ፀጥታ እና መረጋጋት ዙሪያ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ዛሬ እያካሄዱ ነው።
በከተማው እየተነዛ ያለው የውሸት ወሬዎችን ሳይሰሙ ስለ ከተማው ፀጥታ ለመወያየት ወደ ውይይቱ የመጡ ወጣቶችን የከተማዋ ከንቲባ አቶ አታክልቲ ሃይለስላሴ አመስግነዋል።
ውይይቱን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር መሉ ነጋ፣ የትግራይ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የመቐለ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ሃይለስላሴ እየመሩ ናቸው።
በመቐለ ከተማ ያጋጠመው ዝርፊያ ከማረሚያቤት በተለቀቁ ታራሚዎች እና ሌሎች ሌቦች እንደሆነ ዶ/ር መሉ ለተወያዮቹ አብራርተዋል።
የክልሉም ሆነ የከተማዋ ግዚያዊ አስተዳደር ለፀጥታ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሰራበት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል።
በመቐለ ከተማ የተበተነ የጦር መሳርያ እንዳለ እና በሰላማዊ መንገድ ወደ ፀጥታ አካላት ማስረከብ እንደሚገባ ዶ/ር ሙሉ አስታውቀዋል።
የከተማዋ ወጣቶች የውሸት ወሬዎችን መታገል እንዳለባቸው ጨምረው ገልፀዋል።
ጁንታው የከተማዋ መሰረተ ልማት እንዲወድም ያደረገ ሲሆን የፌደራል መንግስት ባፋጣኝ መሰረተ ልማቱ እየመለሰ መሆኑን ዶ/ር ሙሉ ነጋ ገልፀዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ "ሌቦችም ከኛው፣ የሚሰረቀውም የኛው ስለሆነ ሁላችንም ፀጥታችን ማስከበር አለብን" ሲሉ ተናግረዋል።
በየሰፈሩ የውሸት ወሬዎች የሚፈበርኩ ሰዎች ሆነ በውጪ ሆነው ህዝብ እያደናገሩ ህዝቡ እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ ሚዲያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ የመድረኩ ተሳታፊ ወጣቶቹ ጠይቀዋል።
"የትግራይ ወጣት በኢትዮጵያዊነቱ እንዲደራደር ሁለት አመት መርዝ ተዝርቶለታል፣ ከሁሉም ወንድም ብሄር ብሄረሰብ እንዲጣላ ጁንታው ሰርቷል። የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር የማቀራረብ ስራ ሊሰራ ይገባል" ሲሉ መናገራቸውን ውይይቱን እየተከታተለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ አስታውቋል።
በአማንመስፍን ሚካኤል
- ፎቶ ፋይል
«የትግራይን ሕዝብ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እንጂ እንዲጎዳ በማሰብ የሚሰራ ሥራ የለም»
- አቶ ዛድግ አብርሃ
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር
*********************
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ እንጂ ሆን ተብሎ እንዲጎዳ የተሰራም ሆነ የሚሰራ ሥራ አለመኖሩን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር አስታወቁ፡፡
ሚኒሰትሩ አቶ ዛድግ አብርሃ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፣ መንግሥት የሰሜን ዕዝ መጠቃቱን ተከትሎ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ እንዳለ ሆኖ ወደ ጦርነት የገባበት ዋናው ምክንያት መስዋዕትነትም ተከፍሎ ቢሆን የጁንታው ቡድን እንደመያዣ የያዘውን የትግራይን ሕዝብ ነፃ ለማውጣት ነው። የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን እንደመሆኑ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንጂ እንዲጎዳ በማሰብ የሚሰራ ሥራ የለም ብለዋል አቶ ዛዲግ።
እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ ጁንታው ቡድን መንገድ፣ ድልድይ፣ አየር ማረፊያ አውድሟል፤ ተንቀሳቃሽ የገንዘብ መስጫ (ኤቲኤም) ማሽኖች ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል፤ በኢትዮ ቴሌኮም መስመሮች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት አድርሶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በክልሉ የደረሰው የመሠረተ ልማት ውድመት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ጀምበር መልሶ መገንባቱም ከባድ ነው።
እንደዚህ ዓይነት አቅም ቢኖረንማ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የመሠረተ ልማት ችግር ባልተፈጠረ ነበር ያሉት አቶ ዛድግ እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም ፤ የፈራረሱትን ወደነበሩበት ለመመለስ ጊዜ ይወስዳል ፤ አሁንም ግን ሥራዎች እየተሰሩ ነው፤ በክልሉ የባንክ አገልግሎት ለምን አይጀመርም ተብሎ ለሚቀርበው ጥያቄም መልሱ ይኸው ነው ብለዋል።
ጁንታው በስንት ዓመት በብዙ ልፋትና ጥረት የተገነባን መሠረተ ልማት በ30 ቀን ነው ያወደመው፤ በአሁኑ ወቅትም መንግሥት የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ነው፤ መንገዶች እየተጠገኑ፣ የቴሌኮም መሠረተ ልማቱም እንደገና ወደ ሥራ እንዲገባ ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤ የባንክ አገልግሎቱም እንደዚያው፤ ነገር ግን ሕዝቡም አክቲቪስቱም ሌላውም እንደሚፈልገው በአንድ ቀን መስራት አይቻልም፤ ይህም ቢሆን ግን መንግሥት የለጋሽ አካላትን አቅም በማንቀሳቀስ ሁሉ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ አንዳንድ አካላት እንደሚሉት ሆን ተብሎ የትግራይን ሕዝብ ለመበደል የተሰራ ሥራ የለም፤ ይህንን ለማድረግ የሚያስብ መንግሥትም አለመኖሩን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በመሰረተ ልማቱ ላይ የደረሰው አደጋ ከፍተኛ በመሆኑና መንግሥት ብቻውን የሚፈታው ባለመሆኑ ሕዝቡም ሌላውም አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም ኮማንድ ፖስቱ እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አቶ ዛድግ ገልጸዋል።
- አቶ ዛድግ አብርሃ
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር
*********************
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት የትግራይ ሕዝብ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ እንጂ ሆን ተብሎ እንዲጎዳ የተሰራም ሆነ የሚሰራ ሥራ አለመኖሩን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ግንባታ ሚኒስትር አስታወቁ፡፡
ሚኒሰትሩ አቶ ዛድግ አብርሃ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፣ መንግሥት የሰሜን ዕዝ መጠቃቱን ተከትሎ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ እንዳለ ሆኖ ወደ ጦርነት የገባበት ዋናው ምክንያት መስዋዕትነትም ተከፍሎ ቢሆን የጁንታው ቡድን እንደመያዣ የያዘውን የትግራይን ሕዝብ ነፃ ለማውጣት ነው። የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን እንደመሆኑ እንደማንኛውም ዜጋ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንጂ እንዲጎዳ በማሰብ የሚሰራ ሥራ የለም ብለዋል አቶ ዛዲግ።
እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ ጁንታው ቡድን መንገድ፣ ድልድይ፣ አየር ማረፊያ አውድሟል፤ ተንቀሳቃሽ የገንዘብ መስጫ (ኤቲኤም) ማሽኖች ከጥቅም ውጪ እንዲሆኑ አድርጓል፤ በኢትዮ ቴሌኮም መስመሮች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት አድርሶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በክልሉ የደረሰው የመሠረተ ልማት ውድመት ከፍተኛ በመሆኑ በአንድ ጀምበር መልሶ መገንባቱም ከባድ ነው።
እንደዚህ ዓይነት አቅም ቢኖረንማ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የመሠረተ ልማት ችግር ባልተፈጠረ ነበር ያሉት አቶ ዛድግ እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም ፤ የፈራረሱትን ወደነበሩበት ለመመለስ ጊዜ ይወስዳል ፤ አሁንም ግን ሥራዎች እየተሰሩ ነው፤ በክልሉ የባንክ አገልግሎት ለምን አይጀመርም ተብሎ ለሚቀርበው ጥያቄም መልሱ ይኸው ነው ብለዋል።
ጁንታው በስንት ዓመት በብዙ ልፋትና ጥረት የተገነባን መሠረተ ልማት በ30 ቀን ነው ያወደመው፤ በአሁኑ ወቅትም መንግሥት የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ነው፤ መንገዶች እየተጠገኑ፣ የቴሌኮም መሠረተ ልማቱም እንደገና ወደ ሥራ እንዲገባ ሰፋፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፤ የባንክ አገልግሎቱም እንደዚያው፤ ነገር ግን ሕዝቡም አክቲቪስቱም ሌላውም እንደሚፈልገው በአንድ ቀን መስራት አይቻልም፤ ይህም ቢሆን ግን መንግሥት የለጋሽ አካላትን አቅም በማንቀሳቀስ ሁሉ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
እንደ አቶ ዛድግ ገለጻ አንዳንድ አካላት እንደሚሉት ሆን ተብሎ የትግራይን ሕዝብ ለመበደል የተሰራ ሥራ የለም፤ ይህንን ለማድረግ የሚያስብ መንግሥትም አለመኖሩን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በመሰረተ ልማቱ ላይ የደረሰው አደጋ ከፍተኛ በመሆኑና መንግሥት ብቻውን የሚፈታው ባለመሆኑ ሕዝቡም ሌላውም አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም ኮማንድ ፖስቱ እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አቶ ዛድግ ገልጸዋል።