ከአዲስ አበባ የተነሳው የአደዋ ተጓዥ ቡድን ዛሬ ደሴ ደርሷል። ቡድኑም በደሴ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ይህ አቀባበልና ጉብኝት በድርጅታችን ካሜራ ማን ዳኜ አበራ እንዲህ ተዘግቧል።
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተሰጠ ማሳሰቢያ
*****************************
(ኢ.ፕ.ድ)
ነገ ዓርብ የካቲት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ፣
• በኢትዮ ፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
እንዲሁም ቅዳሜ የካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በፍሊንት ስቶን ሪል እስቴት፣ በአትሌቶች መንደር፣ በለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊት ለፊት እና አካባቢዎቻቸው፣
በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ፤ ክቡራን ደንበኞቻችን ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
*****************************
(ኢ.ፕ.ድ)
ነገ ዓርብ የካቲት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ፣
• በኢትዮ ፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
እንዲሁም ቅዳሜ የካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በፍሊንት ስቶን ሪል እስቴት፣ በአትሌቶች መንደር፣ በለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊት ለፊት እና አካባቢዎቻቸው፣
በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ፤ ክቡራን ደንበኞቻችን ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የከባድ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሰዓት ማሻሻያ ተደረገበት።
በአዲሱ ማሻሻያም ከባድ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1-3 ሰአት እንዲሁም ከሰዓት ከ 10:30-12:00 ውጪ ባሉ ሰዓቶች እንዲንቀሳቀሱ ተወስኗል።
ማሻሻያው የተደረገው የተለያዩ ተቋማት በሰዓት ገደቡ ምክኒያት በተለይም የግንባታ ስራዎቻቸውን ለማከናወን መቸገራቸውን ቅሬታ በማቅረባቸው ነው።
በመሆኑም የትራፊክ እንቅስቃሴውን ጫና ውስጥ በማይከት መልኩ ማሻሻያው ተደርጓል።
እስካሁን በነበረው ህግ በከተማዋ የሚገኙ ከባድ ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር መንቀሳቀስ የሚፈቀድላቸው።
በአዲሱ ማሻሻያም ከባድ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1-3 ሰአት እንዲሁም ከሰዓት ከ 10:30-12:00 ውጪ ባሉ ሰዓቶች እንዲንቀሳቀሱ ተወስኗል።
ማሻሻያው የተደረገው የተለያዩ ተቋማት በሰዓት ገደቡ ምክኒያት በተለይም የግንባታ ስራዎቻቸውን ለማከናወን መቸገራቸውን ቅሬታ በማቅረባቸው ነው።
በመሆኑም የትራፊክ እንቅስቃሴውን ጫና ውስጥ በማይከት መልኩ ማሻሻያው ተደርጓል።
እስካሁን በነበረው ህግ በከተማዋ የሚገኙ ከባድ ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር መንቀሳቀስ የሚፈቀድላቸው።
ከ124 አመት በፊት የአጼ ምንሊክ የክተት አዋጅ
*እግዚእብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ እገር እስፍቶ እኖረኝ ፣ እኔም በእግዚእብሔር ቸርነት ጉዛሁ።እንግዲህ ብሞትሞ ሞት የሁሉም ነውና። ስለ እኔ ሞት እላዝንም ደግሞ እግዚእብሔር አሳፍሮኝ እያውቅም ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ እልጠራጠርም ፣ አሁንም አገር የሚያጠፋ ሀይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚእብሔር የወሰነልንን የባህር በር እልፎ መጥቷልና አሁን ግን ሀገሬን አሳልፌ እልስጥውም ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሽዋ ስው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድርስ ወረኢሉ ከተህ ላግኝህ"
የአድዋ ተጓዧች እዚች ታሪካዊ ከተማ ደርሰው ደማቅ አቀባበል ተድርጎላቸዋል።
ፎቶ ዳኜ አበራ
*እግዚእብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ እገር እስፍቶ እኖረኝ ፣ እኔም በእግዚእብሔር ቸርነት ጉዛሁ።እንግዲህ ብሞትሞ ሞት የሁሉም ነውና። ስለ እኔ ሞት እላዝንም ደግሞ እግዚእብሔር አሳፍሮኝ እያውቅም ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ እልጠራጠርም ፣ አሁንም አገር የሚያጠፋ ሀይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚእብሔር የወሰነልንን የባህር በር እልፎ መጥቷልና አሁን ግን ሀገሬን አሳልፌ እልስጥውም ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሽዋ ስው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድርስ ወረኢሉ ከተህ ላግኝህ"
የአድዋ ተጓዧች እዚች ታሪካዊ ከተማ ደርሰው ደማቅ አቀባበል ተድርጎላቸዋል።
ፎቶ ዳኜ አበራ
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ለካራማራ ድል በዓል ያስተላለፉት መልእክት
************************
ከዚያድ ባሬ መራሹ የሶማሊያ ወራሪ ኃይል ጋር በነበረን ተጋድሎ ወሳኝ ድል ላስመዘገብንበት የካራማራ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ። የ1967ቱ የሶማሊያ ወረራ ሀገራችን ከአብዮት ፍንዳታው ጭጋግ ባልወጣችበትና የእርስ በርስ ግጭት ላይ በነበረችበት ጊዜ የተከሠተ ነው።
ኢትዮጵያን የወረሩ አብዛኞቹ ኃይሎች እንደሚሠሩት ስሕተት ዚያድ ባሬም ተሳሳተ።
ሀገር የደከመች መስሎት ኢትዮጵያን የማሸነፊያ ጊዜ የደረሰለት መሰለው። በዚህ የተሳሳተ ስሌት ተመርቶ ወረራውን ፈጸመ። በመጀመሪያ አካባቢ እንዳሰበውም የጎላ መከላከል ሳይገጥመው ሰፊ የሀገራችንን መሬት ማካለል ችሎ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያውያን እንደፍግ ተኝተው እንደ እቶን በተነሡ ጊዜ ምን እንደሚያደርጉ በዚህ ወረራ ጊዜ ታየ።
በአጭር ጊዜ “የእናት ሀገር ጥሪ” የተሰባሰቡ፣ በቂ የሥልጠናም ሆነ የዝግጅት ሁኔታ ያልነበራቸው፣ ነገር ግን ከየትም የማይበደሩት የሀገር ፍቅርና የማሸነፍ ወኔ ያላቸው ውድ ኢትዮጵያውያን ወረራውን በስኬት መቀልበስ ቻሉ።
መንግሥታትን በሀገር ውስጥ ክዋኔያቸው በአንድም በሌላም ልንመዝናቸው እንችላለን። ነገር ግን የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የሚከፈሉ መሥዋዕትነቶች በየትኛውም ዘመን ቢፈጸሙ የሀገራችን ታሪካዊ ኩራት ናቸው።
የደርግ መንግሥትም በአጭር ጊዜ ጥሪ አቅርቦ፣ አሠልጥኖና አደረራጅቶ የሀገርን ክብር ለማስመለስ ያደረገው ተጋድሎና ያስመዘገው ድል የሁላችንም የኢትዮጵያውያን የአልበገር ባይነትና ለሀገር የመሥዋዕትነት የመክፈል ታሪካችን አካል ነው።
ሁሌም በውስጣችን ክፍተት ሲኖር የውጭ ጠላት እንጋብዛለን፤ ስንጠናከር ግን የታፈርንና የተከበርን እንሆናለን።
************************
ከዚያድ ባሬ መራሹ የሶማሊያ ወራሪ ኃይል ጋር በነበረን ተጋድሎ ወሳኝ ድል ላስመዘገብንበት የካራማራ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ። የ1967ቱ የሶማሊያ ወረራ ሀገራችን ከአብዮት ፍንዳታው ጭጋግ ባልወጣችበትና የእርስ በርስ ግጭት ላይ በነበረችበት ጊዜ የተከሠተ ነው።
ኢትዮጵያን የወረሩ አብዛኞቹ ኃይሎች እንደሚሠሩት ስሕተት ዚያድ ባሬም ተሳሳተ።
ሀገር የደከመች መስሎት ኢትዮጵያን የማሸነፊያ ጊዜ የደረሰለት መሰለው። በዚህ የተሳሳተ ስሌት ተመርቶ ወረራውን ፈጸመ። በመጀመሪያ አካባቢ እንዳሰበውም የጎላ መከላከል ሳይገጥመው ሰፊ የሀገራችንን መሬት ማካለል ችሎ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያውያን እንደፍግ ተኝተው እንደ እቶን በተነሡ ጊዜ ምን እንደሚያደርጉ በዚህ ወረራ ጊዜ ታየ።
በአጭር ጊዜ “የእናት ሀገር ጥሪ” የተሰባሰቡ፣ በቂ የሥልጠናም ሆነ የዝግጅት ሁኔታ ያልነበራቸው፣ ነገር ግን ከየትም የማይበደሩት የሀገር ፍቅርና የማሸነፍ ወኔ ያላቸው ውድ ኢትዮጵያውያን ወረራውን በስኬት መቀልበስ ቻሉ።
መንግሥታትን በሀገር ውስጥ ክዋኔያቸው በአንድም በሌላም ልንመዝናቸው እንችላለን። ነገር ግን የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የሚከፈሉ መሥዋዕትነቶች በየትኛውም ዘመን ቢፈጸሙ የሀገራችን ታሪካዊ ኩራት ናቸው።
የደርግ መንግሥትም በአጭር ጊዜ ጥሪ አቅርቦ፣ አሠልጥኖና አደረራጅቶ የሀገርን ክብር ለማስመለስ ያደረገው ተጋድሎና ያስመዘገው ድል የሁላችንም የኢትዮጵያውያን የአልበገር ባይነትና ለሀገር የመሥዋዕትነት የመክፈል ታሪካችን አካል ነው።
ሁሌም በውስጣችን ክፍተት ሲኖር የውጭ ጠላት እንጋብዛለን፤ ስንጠናከር ግን የታፈርንና የተከበርን እንሆናለን።
የአለም ባንክ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብርን ለመደገፍ 25 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ወሰነ።
ኢ/ር ታከለ ኡማ በኢትዮጵያ የአለምባንክ ዳይሬክተር ሚስ ካሮላይን ተርክ ጋር ተነጋግረዋል።
ዳይሬክተሯ የአለም ባንክ የተማሪዎች ምገባን ለመደገፍ 25 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑንም ገልፀዋል።
የተቋሙ ድጋፍ የከተማ ልማት አቅም መደገፊያ/Urban Productivity Safety Net Program/ አካል ነው።
የአለም ባንክ የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎችን በቀጣይነት እንደሚደግፍ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
ኢ/ር ታከለ ኡማ በኢትዮጵያ የአለምባንክ ዳይሬክተር ሚስ ካሮላይን ተርክ ጋር ተነጋግረዋል።
ዳይሬክተሯ የአለም ባንክ የተማሪዎች ምገባን ለመደገፍ 25 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑንም ገልፀዋል።
የተቋሙ ድጋፍ የከተማ ልማት አቅም መደገፊያ/Urban Productivity Safety Net Program/ አካል ነው።
የአለም ባንክ የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎችን በቀጣይነት እንደሚደግፍ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
የውጭ አገር ሥራ ስምሪት ተጠናክሮ ቀጥሏል
እስከ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ 15541 ዜጎች በአዋጁ መሰረት ወደ ተቀባይ አገራት ተሰማርተዋል
የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከተጀመረ ጀምሮ መንግሥት የሥራ ስምምነት ወደ አደረገባቸው አገራት የሥራ ዕድል አግኝተው ወደ ሣውዲ ዐረቢያ፣ ኳታር፣ ጆርዳን፣ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ 15541 ዜጎቻችን ለሥራ ተሰማርተዋል፡፡ እነዚህ ዜጎቻችን በህጋዊ መንገድ መጓዛቸው ክብራቸው መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ዓይነት የጉዞ ወጪ ሳያወጡ በነፃ በውጭ ሀገር ለሥራ የተሰማሩ ናቸው፡፡
ህብረተሰባችንም በህጋዊ መንገድ የውጭ አገር የሥራ ሥምሪት ተጀምሮ ዜጎች ተጠቃሚ እየሆኑ መሆኑን ተረድቶና ተገንዝቦ ልጆቹን ከህገ-ወጥ ደላላና ከህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም ከህገ-ወጥ የበረሃ ጉዞ እንዲታቀቡ ለማሳሰብ እየወደድን ከላይ የተገለፀው ዳታ በየክልሉ እንደሚከተለው ተመላክቷል ፡፡
እስከ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ 15541 ዜጎች በአዋጁ መሰረት ወደ ተቀባይ አገራት ተሰማርተዋል
የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከተጀመረ ጀምሮ መንግሥት የሥራ ስምምነት ወደ አደረገባቸው አገራት የሥራ ዕድል አግኝተው ወደ ሣውዲ ዐረቢያ፣ ኳታር፣ ጆርዳን፣ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ 15541 ዜጎቻችን ለሥራ ተሰማርተዋል፡፡ እነዚህ ዜጎቻችን በህጋዊ መንገድ መጓዛቸው ክብራቸው መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ዓይነት የጉዞ ወጪ ሳያወጡ በነፃ በውጭ ሀገር ለሥራ የተሰማሩ ናቸው፡፡
ህብረተሰባችንም በህጋዊ መንገድ የውጭ አገር የሥራ ሥምሪት ተጀምሮ ዜጎች ተጠቃሚ እየሆኑ መሆኑን ተረድቶና ተገንዝቦ ልጆቹን ከህገ-ወጥ ደላላና ከህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም ከህገ-ወጥ የበረሃ ጉዞ እንዲታቀቡ ለማሳሰብ እየወደድን ከላይ የተገለፀው ዳታ በየክልሉ እንደሚከተለው ተመላክቷል ፡፡