Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.1K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂ ፒ ኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ በየጊዜው እያጋጠመ ለሚ ገኘው የህይወትና ንብረት ውድመት በህወሓት ጁንታ እና ተላላኪዎቹ የሚፈፀም መሆኑንና ይህንንም ለማስወገድ ብሎም የቡድንን ዕድሜውን ለማሳጠር በ‹ጂ ፒ ኤስ› ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊስ ኢንዶክተሬሽን መምሪያ አስታወቀ።

የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊስ ኢንዶክተሬሽን መም ሪያ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር እንዳለ ቁምላቸው ለበሪሳ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ የህወሓት ጁንታ እና የኦነግ ሸኔን ሴራ ለማክሸፍና ዕድሜ ለማሳጠር ‹‹ጂ ፒ ኤስ›› ቴክኖሎጂ እየተጠቀመ መሆኑን አብራርተዋል።

እነዚህ አካላት ዜጎችን ለምን እንደሚገድሉ እን ደማያውቁ በመጠቆም በህግ ቁጥጥር ሥር ለማዋልም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል። ቴክኖሎጂው እነዚህ አካላት ያሉበትን ቦታ ለመከታተል የሚያስችል እንደሆነም አመልክተዋል።

በዚህ ቴክኖሎጂ በመታገዝ የኦነግ ሸኔ አባላት በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆናቸውን የተናገሩት ኃላ ፊው፤ በሠላማዊ መንገድ እጅ ለማይሰጡና የኃይል አማራጭ ለመጠቀም የሚሞክሩት ላይ ደግሞ እርምጃ እየተወሰደባቸው እንደሆነ አስታውቀዋል ።

እነዚህ ጸረ ሠላም አካላት አባ ቶርቤ በሚል ስያሜ የሚንቀሳቀሱ መሆኑን አመልክተው ፣ ኦሮሚያ ክልልን የግጭትና ጦር አውድማ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ሠላማዊ ዜጎችን መግደል ሥራቸው አድርገው መቆየታቸውንም አመልክተዋል።

ማንኛውንም የፖለቲካ አመለካከት ያለው አካል በዴሞክራሲያዊ መንገድ የፖለቲካ አስተሳሰቡን ለህዝብ መሸጥ ይጠበቅበታል ያሉት ኮማንደር እንዳለ፤ ከዚህ ውጪ ሰላም በማደፍረስና ሠላማዊ ዜጎችን በመግደል ስኬታማ መሆን እንደማይቻል አስረድተዋል።

የኦሮሚያ ፖሊስም ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆነና የዜጎችን ሠላም ለመጠበቅ የተቋቋመ ነው ያሉት ምክትል ኮማንደር ፣ በየትኘውም ሁኔታ የዜጎችን ሰላም ችግር ውስጥ የሚከቱ ተግባራትን አይታገስም ብለዋል። መንግሥትም ለዜጎች ሠላምና ደህንነት መቃወስ ምክንያት የሆኑ እንደ የህወሓት ጁንታና ፣ አባ ቶርቤ፣ ሸኔ እና ሌሎችንም ወደ ህግ ለማቅረብ ከመቼውም በላይ ጠንካራ ሥራ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=36804
በቆላ ተንቤን የሚገኘው የጁንታው የመጨረሻ ምሽግ ተከቦ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል
******************
(ኢ ፕ ድ)
በቆላ ተንቤን የሚገኘው የጁንታው የመ ጨረሻ ምሽግ በሀገር መከላከያ ሰራዊት በሶስት አቅጣጫ ተከቦ እርምጃ እየተወሰደበት እንደሚገኝ ተገለጸ። በቆላ ተምቤን የጁንታውን አመራር ለመያዝ የሚ ደረገውን ዘመቻ እየመሩ ያሉት በመከላከያ ሰራዊት የ31ኛ ክፍለ ጦር ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ኮሎኔል ሻምበል በየነ እንደገለጹት፤ ከመቀሌ ቢሮው ለቆ የሸሸው የጁንታው አመራር በቆላ ተንቤን የመጨረሻ ምሽጉ ላይ ይገኛል።

የመከላከያ ሰራዊትን የጁንታውን የመጨረሻ ምሽግ በተለያዩ አቅጣጫዎች ከቦ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል። ቆላተምቤን ወርቅ አምባ ከተማ ላይ የመጨረሻ ምሽጉን ያደረገውን የጁንታውን አመራር ለመያዝ አሊያም ለመደምሰስ መከላከያ ሰራዊት በመረጃ የተደገፈ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል ያሉት ኮሎኔል ሻምበል፤ ከአድዋ መስመር የመጣው ሰራዊት አካባቢውን ለመቆጣጠር እየገሰገሰ እንደሆነ እና ከሃውዜን እና መቀሌ መስመር ያለውም ወደ ቦታው በከፍተኛ ወኔ እየተጠጋ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

መከላከያ ሰራዊቱ ወርህ የሚባል ትልቅ ወንዝ መሻገር አይችልም በሚል አካባቢ የጁንታው ታጣቂዎች ማጥቃት ቢፈጽምም ሰራዊቱ ወደ አካባቢው ተጠግቶ ከወርቅ አምባ 10 ኪሎ ሜትር ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል። እንደ ኮሎኔል ሻምበል ከሆነ፤ በቆላ ተምቤን ወርቅ አምባ አካባቢ የመሸገው ጁንታው በምድር ከሚወሰድበት እርምጃ ባለፈ በአየር ጭምር እርምጃ ተወስዷል። በአየርና በድሮን አውሮፕላኖች በተወሰደ እርምጃ ወርቅ አምባ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ ሰባት የጁንታው ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ወድመዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=36796
የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ
**************
(ኢ ፕ ድ)
”አንድ በሬ ሸጬ ስድስት ዓመት በመቀሌ የታሰረውን የልጅ ልጄን በደከመ አቅሜ ሄጄ አስፈትቻለሁ። ከተፈታ በኋላም አፋኙ የህወሓት ጁንታ በሚደረግበት ጫናና ክትትል ተማሮ ወደ ሳውዲ አረቢያ ሄዷል። የልጅ ልጄ ያለበትን ቦታና ምን እንዳጋጠመው ስለማላውቅ የበረሃ ራት ሆኖ ይሆን ብዬ እየተጨነኩ ነበር። አምና ግን ሳውዲ መግባቱን ስለሰማሁ ደስታዬ ወደር የለውም” የሚሉት ወይዘሮ ከፍያለች በላይ ናቸው።

ቃፍታ ሁመራ ከተማ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ ነጻ ከወጣች ሶስት
ሳምንት ሁኗታል። ከተማዋ ነጻነቷን በመቀናጀቷ እፎይታ ከተሰማቸው
ነዋሪዎች መካከል አንዷ ወይዘሮ ከፍያለች በላይ ናቸው። አፋኙ ቡድኑ
በማንነታቸው ምክንያት በእኚህ አዛውንት ላይ ከፍተኛ ማንገላታት፣
ሰቆቃና ግፍ ፈጽሞባቸዋል።

ማንነቴን አልሸጥም እኔ የወልቃይት አማራ ነኝ አባቴ፣ አጎቶቼ ይግባኝ ሲኖራቸው መቀሌ ሳይሆን ደባርቅና ዳባት ሄደው ሲያስፈጽሙ ነበር ብዬ በአደባባይ በመናገሬ እያረስኩና እያሳረስኩ ልጆቼን ያሳደኩበትን መሬቴን ተነጥቄያለሁ ይላሉ ።
https://www.press.et/Ama/?p=36795
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የመመስረትና መልሶ የማደራጀት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ
************************
(ኢ ፕ ድ)

መቀሌ፡- በትግራይ ክልል ህግን የማስከበር ሶስተኛው ምእራፍ ከተጠናቀቀ በኋላ ጊዜያዊ አስተዳደር የመመስረትና መልሶ የማደራጀት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የትራይ ብሄራዊ ክልል ጊዜያዊ አስተዳር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ ህግን የማስከበር ርምጃውን በጥንቃቄ በማከናወን ወደ ቀጣዩ ምእራፍ መሸጋገር ተችሏል፡፡ ጊዜያዊ አስተዳደር የመመስረትና መልሶ የማደራጀት ስራ ተጀምሯል።

እስካሁንም በሽሬ እና በአክሱም የተለያዩ ቀበሌዎችንና ወረዳ አስተዳደሮችን መልሶ የማደራጀት ስራ ተሰርቷል።

ለጊዜያዊ አስተዳደሩ የተመረጡ ስራ አስፈጻሚዎች ስራ ጀምረዋል ያሉት ዶ/ር ሙሉ፤ በመቀሌ ከተማ ህዝቡ ወደ መደበኛው ስራው እንዲመለስ፣ የመንግስት ተቋማት ስራቸውን እንዲያከናውኑና የንግድ ተቋማትም ስራቸውን እንዲጀምሩ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ወጣቶች ተደራጅተው ከመከላከያ ጎን እንዲቆሙ የልዩ ሃይልና የሚሊሻ አባላት እጃቸውን በሰላማዊ መንገድ እንዲሰጡም እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ሙሉ፤ የሀገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች የመንግስትን እገዛ ሲጠባበቁ እንደነበርና በከተሞች አልፎ አልፎ የሚታየውን ዘረፋ ለማስቆም ከጸጥታ ሃይሉ ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በጸጥታ ስጋት ምክንያት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ሸሽተው የሄዱ ሰዎችን ወደ ነበሩበት የመመለሱና የማረጋጋት ስራው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

መከላከያ ሰራዊት መቀሌንና ሌሎች ከተሞችን የተቆጣጠረ በመሆኑ ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት ወደሚኖርበት አካባቢ በመምጣት ሰላማዊ ኑሮውን እንዲኖር ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የህግ ማስከበሩ ስራ ለትግራይ ህዝብ ከፍተኛ ጥቅም ይዞ የሚመጣ እንደሆነ የገለጹት ዶክተር ሙሉ፤ ህዝቡ ከነበረበት ጫና ወጥቶ በነጻነት እንዲንቀሳቀስ ያስችለዋል ብለዋል፡፡

የክልሉን የካቢኔ አባላት የማዋቀር ስራ እንደሚሰራና እንደ ባንክ ፣ቴሎኮም፣ መብራት የመሳሉት አገልግሎት ሰጪ ቋማትን ከፌደራል መንግስት ጋር በመተባበር የማስጀመሩ ስራ ትኩረት ተሰጥጦታል ብለዋል፡፡

የስራ እንቅስቃሴ ከመቋረጡ ጋር ተያይዞ የምግብ እጥረት ሊፈጠር ስለሚችል አርዳታዎችን የማስተባበር ስራዎች እንደሚከናወኑ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ገልጸዋል፡፡
በኢያሱ መሰለ
ከአላማጣ ወደ መቀሌ የሚሄደው የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፍያ መስመር እየተጠገነ ነው
***********
(ኢ.ፕ.ድ)

ከአላማጣ ወደ መቀሌ የሚሄደው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፍያ መስመር እየተጠገነ ነው።

በስፍራው የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢ ተዟዙሮ እንደተመለከተው፤ በከሀዲው የህወሓት ታጣቂዎች ጉዳት ደርሶበት የነበረው ይሄው የኤሌክትሪክ ሃይል መስመር ጥገና በፍጥነት እየተከናወነ ነው።

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ትግራይን መልሶ የመገንባቱ ሥራ የድኅረ ዘመቻ ዋናው ተግባራችን ነው ማለታቸውና ይህ ተግባር ሦስት መልኮች እንዳሉት ማስታወቃቸው ይታወቃል።

"ሰብአዊና ማኅበራዊ ድጋፍ፣ የተጎዳውን መሠረተ ልማት መልሶ መገንባት እና መሠረታዊ አገልግሎቶችን መልሶ ማስጀመር። እነዚህ ሥራዎች በስፍራው በተገኙ ቡድኖች አማካኝነት ተጀምረዋል" ማለታቸውም ይታወሣል።
ባለ ከዘራው ኮሎኔል
*********
(ኢ ፕ ድ)
ፊታቸው ላይ የአልበገርም ባይነት ስሜት ጎልቶ ይነበባል፤ እያነከሱም ቢሆን ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳሉ። መገናኛ ራዲዮናቸውን እና የምርኩዝ ከዘራቸውን ይዘው የጁንታው ቡድን አመራር ያለበት ቆላ ተንቤን አቅራቢያ በምትገኝ ሰዋራማ ስፍራ ላይ ጦሩን እየመሩ ይገኛል።
ኮሎኔል ሻምበል በየነ ይባላሉ። በቆሙበት የውጊያ ትዕዛዝ እየሰጡ ኮስታራ ፊታቸውን ወደእኛ ዘወር አደረጉ። ቆስለው አልታከምም በማለት በወኔ እየመሩ የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራር መሆናቸውን ሰማንና ታሪካቸውን እንዲያካፍሉን ጠየቅናቸው።
ድንገተኛ ፈገግታ እያሳዩ ቀድሞም የጁንታው አባላት ውጊያ ሰራዊቱ ላይ ሊከፍቱ እንደሆነ ጥርጣሬ ነበረኝ በማለት በተረጋጋ ስሜት ትውስታቸውን ማጋራት ጀመሩ። እኔ የ31ኛ ክፍለጦር ምክትል የኦፕሬሽን አዛዥ ነበርኩ ዋና አዛዡ ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ቀደም ብሎ የተወሰኑ አባላትን ሽሬ ድረስ ወስዶ ሲሰበስብ የሆነ ነገር ሊፈጥር እንደሚችል አስበው እንደነበር።
ማታውኑ ችግር ሊኖር እንደሚችል በማመን በግሌ ዝግጅት አደረግኩ። ስዘጋጅ በባንክ አካውንቴ የነበረውን ጥቂት ገንዘብ በቤተሰብ አዞርኩ። ከዚያም ጥቃት ለማድረስ ከበባ ሲፈጽሙብኝ ተከብቤያለሁ በሚል ለበላይ አካላት ሪፖርት አደረኩ ።
በመከላከያ ላይ ጥቃት ሲፈጸምም የክፍለጦሩ አዛዡ ከድቶ የጁንታውን ቡድን ተቀላቀለ። በዚህ ጊዜ የክፍለጦር ኮሚቴ ወይም ከበታች አዛዦች አባላት ጋር በመሆን ግብግብ ፈጸምን። እኔም ከፊቴ ያለውን በጥይት መትቼ ጣልኩ። እኔ ጋር የተጀመረች የመከላከል ተኩስ እስከታችኛው የሻለቃ አመራር ድረስ እየተደማመጠ የመከላከል እርምጃውን ወሰደ።
በኋላም የካምፑን ከበባ አጠናቅቄ ስወጣ ደግሞ የልዩ ኃይል ከውጭ ጠበቀኝ የሚሉት ኮሎኔል፤ እነሱንም ጥሼ በመውጣት ከስምንተኛ ሜካናይዝድ ጦር ጋር ተቀላቀልኩ ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ያስታውሱታል።
በወቅቱ እግራቸው ላይ በጥይት መመታታቸው እምብዛም ቁብ አልሰጡትም። በዚያ ሁኔታ ላይ እያሉ ወደኤርትራ በማፈግፈግ በዚያ ከሚገኘው እና በጁንታው ታጣቂ ጥቃት ደርሶበት ከሚገኘው ጦራቸው ጋር ተገናኙ። ጦሩን አደራጅተው በመመለስ ሽራሮ ፣ሽሬ፣ አዲ አደራይ፣ አዲነብሪ እና በርካታ ቦታዎች በማስለቀቅ የህግ ማስከበር እርምጃቸውን በብቃት መወጣትም ቻሉ።
ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ከታፋቸው የሚፈስ ደም እንደ ነበር በቅርበት የሚያውቋቸው ወታደሮች ይናገራሉ። ቁስሉን በየሶስት ቀኑ በጦር ሜዳ አካባቢ እየታከምኩ አንዷ ጥይት ወጣች የሚሉት ኮሎኔል ሻምበል፤ ምርኩዝ ይዘው ግዳጃቸውን መወጣታቸውን ነግረውናል። ዋና አዛዡ ግን የጁንታውን ቡድን በመቀላቀል ለጁንታው አመራር ሽፋን ለመስጠት ጥረት እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
አሁን ላይ ቆላ ተንቤን ላይ ወንጀለኛ ለማስመለጥ እና ወንጀለኛ ለመያዝ ዋናው እና ምክትል አዛዡ ፊት ለፊት ተፋጠዋል። ምክትል አዛዥ ዋናውን ከነጀሌዎቹ እያባረረ እርምጃ እየወሰደበት ይገኛል። ከሚመሩት ጦር ጋር በርካታ ሀገር የከዱ ጄኔራሎችን እያባረሩ ቆላ ተምቤን ላይ ያደረሱት ኮሎኔል ሻምበል፤ እዚህ በመድረሴ ትልቅ ደስታ ይሰማኛል ሲሉ በኩራት ይናገራሉ።
ቆላ ተምቤን ላይ የመሸገውን የከሃዲው ቡድን አመራር አባላት ለህግ ሲቀርቡ በተሻለ ህክምና በጥይት የተመታውን እግራቸውን ሊታከሙት እንደሚችሉ እንደተወርዋሪ ኮኮብ መሳይ ብልጭታ ባለው ፈገግታቸው ታጅበው በለሆሳስ ነገረውናል። ቦታው ላይ ቆስለውም ቢሆን ጦሩን እየመሩ መገኘታቸው ለሰራዊቱም ብርታት መሆኑን አልሸሸጉንም።
በእጃቸው ከዘራቸውን ጨብጠው የሚንቀሳቀሱት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ፤ በጉዳት እያሉም ቢሆን በህግ ማስከበር እርምጃ የጁንታውን አመራሮችን ለመያዝ ፀሐይ ውርጭ ሳይሉ በመታገል ላይ ናቸው። ይህም ኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆችን በየጊዜው አታጣም የሚባለው ብሂል እውነት መሆኑን ያረጋገጠ ነው።
ጌትነት ተስፋማርያም
አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013 ዓ.ም
ጌታቸው ረዳና መሰል የህወሓት ጁንታዎች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው መያዛቸው ተገለጸ
*********************
(ኢፕ ድ)
ጌታቸው ረዳና መሰል የህወሓት ጁንታዎች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ከ40 በላይ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው መያዛቸው ተገለጸ።
የጁንታው ቃል አቀባይ የሆነው ጌታቸው ረዳና መሰሎቹ ከመከላከያ ሰራዊት የተሰነዘረባቸውን ጥቃት ለማምለጥ ሲጠቀሙባቸው የነበሩት እነዚሁ ተሽከርካሪዎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር መግባታቸውን የ32ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ደጀኔ ፀጋዬ አስታውቀዋል።
እንደ ኮሎኔል ደጀኔ ገለጻ፤ ተሽከርካሪዎቹ የተያዙት ከማይጨው 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዴላ ወረዳ ነው።
ተሽከርካሪዎቹ ውስጥ በተደረገው ፍተሻም የከሀዲው ቡድን አመራር አባላት መታወቂያ፣ ፓስፖርትና የተለያዩ የግል ሰነዶቻቸው መገኘታቸውን ኮሎኔል ደጀኔ አስታውቀዋል።
የግል ሰነድ ከተገኘባቸው የጁንታው አባላት መካከል የቀድሞው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት እንደሚጠቀሱ ኮሎኔል ደጀኔ ተናግረዋል።
ከተያዙት ተሽከርካሪዎች ውስጥ እጅግ ዘመናዊና በአሻራ የሚከፈቱም እንዳሉበት ኮሎኔሉ ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ ለመከላከያ ሰራዊት አባላት ፍተኛ ድጋፍ እንዳለው ገልጸው፤ በተለይም ከ10 ሺህ ህዝብ በላይ በማይጨው ስታዲየም ሰብስበው የማረጋጋት እና የማወያየት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
በዚሁ ከህዝብ ጋር በተደረገ ውይይት ጁንታው በስልጣን ላይ ለመቆየት ሲያደርገው ለነበረው መፍጨርጨር ከመንግስት ሰራተኞች የወር ደመወዝ ላይ በመቁረጥ ለሚሊሻውና ለታጣቂዎቹ ደመወዝ ይከፍል እንደነበር ህዝቡ በምሬት መናገሩን ኮሎኔሉ አስታውቀዋል።
ነዋሪዎቹ አሁን ይህ በመቅረቱ መደሰታቸውን እንደገለጹላቸው ኮሎኔሉ ተናግረዋል።
ህዝቡ እንደ ስልክና መብራት ያሉ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን መንግስት በፍጥነት እንዲመልስላቸው ማንሳታቸውን ገልጸው፤ በመንግስት በኩል እየተደረገ ባለው ርብርብ እስከ ኮረም ያለው ጥያቄ መልስ ማግኘቱንና በቀጣይም የተቀሩት ከተሞች ጥያቄ እንደሚመለስ አስታውቀዋል።
በእያሱ መሰለ
«መከላከያ ሰራዊታችን ያሳየን የኢትዮጵያዊነትን ልክ ነው» - ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የዓለም አቀፍና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
መከላከያ ሰራዊታችን በሶስት ሳምንት ውስጥ በታላቅ ጀብዱ የኢትዮጵያዊነታችንን ልክ እንዳሳየን የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የዓለም አቀፍና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ አስታወቁ ፡፡
ዶክተር ቢቂላ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት ፤ በትግራይ ክልል ተሸሽጎ የከረመው ጽንፈኛው የህወሓት ስግብግቡ ጁንታ በአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ መንግስት የሕግ ማስከበሩን ተግባር ባከናወነበት ወቅት የአገር መከላከያ ሰራዊት ትልቅ ጀብድ በመፈጸም የኢትዮጵያዊነትን ልክ አሳይቶናል ።መከላከያ ሰራዊቱ በሶስት ሳምንት ውስጥ በሰራው ጀብዱ በእርግጥም ታላቅነቱንም አስመስክሯል ፡፡
መከላከያ ሰራዊቱ፤ ‹በአገሬ ከመጣህማ እኔን ታርዳለህ እንጂ ትጥቄን አትፈታም፤ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና በአገሬ ማንነት ከመጣህ ትጨርሰኛለህ እንጂ በዘር አትከፋፍለንም የሚል የጀግንነት ጥግ አሳይቷል “ ያሉት ዶክተር ቢቂላ ፤ በተለይም ውስጥ ያሉ አመራሮች ትጥቃቸውን ፈተው ላለመስጠት ያደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ነው ብለዋል።ሌላ ኃይል እስኪደርስላቸው ድረስ አንገት ለአንገት ተናንቀው የታገሉ መሆናቸውንም አስታውቀዋል ። ከድሉ ጀርባ ያለው የአገር አንድነት መለከያ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን እንደሆነም ጠቁመዋል ። https://www.press.et/Ama/?p=36927
ወደ ሕዝብ ባለመተኮስ የተገለጸ ቃል ኪዳንና ጽናት!
****************
(ኢ ፕ ድ)
ሻለቃ ዘላለም ብዙነህ በሰሜን አየር ምድብ የአየር መከላከል እቅድና ስልጠና ቡድን መሪ ነው።ዋናው የስራ ድርሻው ጠላት የአየር ጥቃት እንዳያደርስ መከላከል እና የምድር ኃይሉ እንዳይጎዳ ድጋፍ መስጠት ነው።ሰሜን አየር ምድብ ከመጣም ከ17 ዓመት በላይ ሆኖታል።ሻለቃ ቡዙነህ እንደሚያስረዳው ዶክተር አብይ ወደ ስልጣን ከመጡ ከ2010 ዓ.ም በኋላ ለውጡ ያልጣማቸው ኃይሎች አዳዲስ ባህሪ አምጥተዋል።
ከፌደራል መንግስት የሚተላለፉ መመሪያዎችን ያለመቀበልና ሰራዊቱን ከፋፍሎ የመመልከት ሁኔታዎችም ይስተዋሉ ነበር። የእነሱን ሀሳብ የማይቀበለውን የአየር ኃይል አባል የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊ ነው በማለት ያጥላላሉ።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉም ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ምንም ባላሰቡት ሁኔታ መቀሌ በሚገኘው የሰሜን አየር ምድብ መኖሪያ ቤት የተኩስ ሩምታ ተከፈተ፤ ምንድ ነው ብለው ሲጠይቁም የሴራው ተባባሪ የሆኑና ጉዳዩን የሚያውቁ አባላት ልምምድ ነው እያሉ ያዘናጓቸው እንደነበር ያስታውሳል።
‹‹ሌሊቱን ሙሉ ሳንተኛ አድረን ልክ አስራ ሁለት ሰዓት ሲደርስ ልዩ ኃይሎች ወደ ግቢው መግባት ጀመሩ።በተለይም የአማራና የኦሮሞ ተወላጅ አባላትን ከቤታችን እያወጡ እያመናጨቁና እየገረፉ ወሰዱን።ወደ ማጎሪያ ቤት ከወሰዱን በኋላ በብሔር ከፋፈሉን።ደቡብን ለብቻ ፤ አማራና ኦሮሞን በአንድ ላይ አድርገው አጎሩን። ሚሳኤል የመተኮስ ልምድና እውቀቱ እንዳለኝ ስለሚያውቁ እኔን ለብቻዬ ወሰዱኝና እንድተኩስላቸውና ከእነርሱ ወገን እንድቆም ጠየቁኝ።
https://www.press.et/Ama/?p=36926
«ጁንታው ሕጋዊ የንግድ ውድድርን ማዛባት ብቻ ሳይሆን ተፎካካሪዎችን የማጥፋት አካሄድ ይከተል ነበር » - አቶ ውብሸት ሙላት የህግ ባለሙያ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ወንጀለኛው የህውሓት ጁንታ ሁሉንም የቢዝነስ ተቋማት በቁጥጥሩ ስር ለማድረግ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ ማንኛውም የንግድ ውድድር እንዳይኖር ከማድረግ በዘለለ ተፎካካሪ ሊሆኑ የሚችሉ የግልና የመንግስት የንግድ ተቋማትን እስከማጥፋት መሄዱን የሕግ ምሑሩ አቶ ውብሸት ሙላት አስታወቁ ።
አቶ ውብሸት በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፣ ይህ ቡድን ወደ ስልጣን ከመጣ ጊዜ ጀምሮ በፖለቲካውም ሆነ በኢኮኖሚው መስክ አግላይ ብቻ ሳይሆን ሌላውንና ከሱ ውጭ የሆነውን የሚያስወግድ እና አፋኝ ነበር ። በኢኮኖሚውም መስክ በኢትዮጵያ ትልቁ ኢንቨስተር ይህ ቡድን ነበር ፤ከፌደራል መንግሥት በላይ የኢኮኖሚ አቅም የፈጠረ ነው ።
አንድ ቡድን በፖለቲካውም ሆነ በኢኮኖሚው የበላይ ከሆነ እና በዚያ ላይ ያለው አስተሳሰብ አግላይ ከሆነ አገርን አደጋ ላይ ይጥላል የሚሉት አቶ ውብሸት፤ አገር ማፍረስን ጨምሮ የፈለገውን እንዲያደርግ እድል ይሰጠዋል፤ በወንጀለኛው ጁንታ የሆነው ይኸው ነው ብለዋል ።
https://www.press.et/Ama/?p=36925
"ጃንሜዳን ለጥምቀት በዓል ዝግጁ እናደርጋለን"
- አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ጃንሜዳን ለጥምቀት በዓል ዝግጁ እናደርጋለን ሲሉ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስተወቁ።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል ተብሎ አትክልት ተራ ወደ ጃንሜዳ እንዲዘዋወር መደረጉን ያስታወሱት ወ/ሮ አዳነች፤ "አሁን ጃንሜዳን መልሶ ለጥምቀት በዓል እና ሌሎች ማሀበራዊ አገልግሎቶች ዝግጁ ላማድረግ ቦታውን ማጽዳት እና ማስተካከል ወሳኝ መሆኑን በመረዳት ዛሬ ማለዳ በቦታው በመገኘት የጽዳት ስራ አስጀምረናል"ብለዋል።
በቦታው ያሉ ነጋዴዎችም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በሃይሌ ጋርመንት እና በሌሎች አካባቢዎች ወደተዘጋጁ የገበያ ማዕከላት ይዘዋወራሉና ለዚህ ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም ከንቲባዋ አሳስበዋል።
"አዳዲሶቹ የአትክልት ገበያዎች የሚርቋቸው የከተማችን ነዋሪዎች ይቅርታ እየጠየኩ በገርጂ፣ ጀሞ፣ አቃቂ፣ ጉለሌ እና ሌሎች አካባቢዎች ተጨማሪ የገበያ ስፍራ እያዘጋጀን መሆኑን እና ችግሩ ጊዜአዊ እንደሆነ ማሳወቅ እወዳለሁ" ሲሉም ተናግረዋል።
ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለበዓሉ አከባበር በኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ በመተባበር፣ በመቻቻል እና መተሳሰብ መንፈስ ሃላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪዬን አቀርባለሁ ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
“አስክሬን ማየት በጣም ቀላል ሊሆን ይችላል፤ እኔም አይቸዋለው፡፡ ከዚህ በፊት የአንድ አመት ልጄን ቀብሬያለሁ፤ አልከበደኝም ፡፡ ማይካድራ ላይ ግን መቆም አይቻልም፤ ያዩትን ሁሉ መመስከርም አይቻልም፤ ስሜቱ በጣም ከባድ ነው፡፡ ያንን ተቋቁመን ባንዘግበው፤ ቦታው ላይም ባንቆም ኖሮ ወንጀሉ ተዳፍኖ ይቀር ነበር” - ጋዜጠኛ ወንድአጥር መኮንን
*********************
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት 80ኛ አመት የምስረታ በአሉን አመቱን ሙሉ በተለያቱ መድረኮች እያከበረ ይገኛል። የበአሉ አካል በማድረግም በህግ ማስከበር ዘመቻው ላይ ለተሳተፉ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የምስጋና እና የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በዚሁ መርሀ ግብር ላይም ወደ ግንባር ከተላኩ ጋዜጠኞች መካከል የማይካድራውን ጭፍጨፋ በስፍራው ተገኝቶ የዘገበው የአማራ መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኛ ወንድአጥር መኮንን የተመለከተውን ለእለቱ ታዳሚያን አጋርቷል።

አስክሬን ማየት በጣም ቀላል ሊሆን ይችላል፤ እኔም አይቸዋለው፡፡ ከዚህ በፊት የአንድ አመት ልጄን ቀብሬያለሁ፤ አልከበደኝም ፡፡ ማይካድራ ላይ ግን መቆም አይቻልም፤ ያዩትን ሁሉ መመስከርም አይቻልም፤ ስሜቱ በጣም ከባድ ነው፡፡ ያንን ተቋቁመን ባንዘግበው ቦታውም ላይ ባንቆም ኖሮ ወንጀሉ ተዳፍኖ ይቀር ነበር” ሲል ነው ጋዜጠኛ ወንድአጥር ምልከታውን ያጋራው።

የተመለከትኳቸው ነገሮች የሚያሙ ናቸው፤ እነዚህ ህመሞች እኛን አመው ባይቆሙ ኖሮ ኢትዮጵያም ኢትዮጵያ ሆና አትቀጥልም ነበር፤ እውነት ለመናገር የማይካድራ ህዝብ ህመሙን ባይችለው ኖሮ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሆና አትቀጥልም ነበር፡፡

ጋዜጠኛ ወንድአጥር በእለቱ በሰጠው የአይን ምስክርነት ላይም ያነሳቸው ዋና ዋና ጉዳዮች እንደሚከተለው ቀርበዋል፤

👉በማይካድራ ላይ የሞተው በዋናነት አማራ ይሁን እንጂ ኦሮሞም ሞቷል፤
ወላይታም ሞቷል፤ ሶማሌም ሞቷል፤

👉ትህነግ ለማንኛውም ነገር እንደማይመለስ የስለት ጫፍ ድረስ ከመጨከን
ወደኋላ እንደማይል ያሳየበት ቦታ ማይካድራ ነው፤

👉የትህነግ ጥላቻ ከ1968 ማኔፌስቶውም በፊት ነው፤ ማንፌስቶው እኮ
የአስተሳሰቡ ውጤት ነው፤

👉የትህነግ የማይካድራ ጭካኔና ጭፍጨፋ በፊት ከመጋረጃ ጀርባ እንደሚፈጸም
በሀሜት ደረጃ ይሰማ የነበረው አሁን መጋረጃው የተገለጠበት ሰይጣንም
ያፈረበት ስራው ነው፤

👉የጁንታው ውሸት አስገራሚ ነበር፤ እኔ ሁመራ ሆኜ ዘገባ እየሰራሁ፤ በሬዲዮ
የሰማሁት የእነሱ ዜና ሁመራን ተቆጣጥረናል የሚል ነው፤ ደነገጥኩ የት ነው
ያለሁት እኔ ነኝ ወይንስ ሁመራ ነው ወደሌላ ቦታ የሄደው እስክል ድረስ
ተገረምኩ፤

👉እነሱ ቢዋሹም አይናቸውና እጃቸው አይዋሽም ነበር፤ በሚዲያዎቻቸው
እየቀረቡ ሲዋሹ ሁሉም ነገር ያስታውቅባቸው ነበር፤

👉የትህነግ ሀይል ገኖ ነበር የመጣው፤ በተለይ እኔ በነበርኩበት አብድራፊ በኩል
አብድራፊን ተቆጣጥሮ ወደ ጎንደር፤ ሶሮቃን በዳንሻ በኩል ተቆጣጥሮ ወደ
ጎንደር፤ በራያ በኩል ወደ ወልዲያ የመሄድ እቅድ ነበረው፤ 23ኛው ክፍለ ጦር
ተበትኖ ስለነበረ ምንም አያስቀረውም ነበር።

👉ነገር ግን የአማራ ክልል ልዩ ሃይል ዝግጁ ስለነበረና የኮንትሮባንድ ስራን
ሲቆጣጠሩ በነበሩ ከተፈጸመባቸው ጥቃት ያመለጡ የፌዴራል ፖሊስ አባላትም
ባደረጉት ተጋድሎና ጀግንነት ትህነግ ሊቆም ችሏል፤

👉ከፊት ለፊት በመሳሪያ ከጎናቸው በጓደኞቻቸው አስከሬን ሽታ ተፈትነው ድል
ነስተዋል፤ ይሄንን ድል ያደረጉት በኢትዮጵያ ፍቅር ነው፤ በኢትዮጵጽያዊነት ነው፤

👉የአማራ ልዩ ሀይል ወደማይካድረ ከመሄዱ በፊት ሁለት የግዴታ አማራጮች
ነበሩት፤ አንደኛው ያለውን ስንቅና ጥይት ለተበተኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላት
እያጋራ መዝለቅ፤ የተማረከውን ሀይል ደግሞ ለመከላከያ እየሰጠ መሄድ
ነበረበት፤ ይሄንን አደረገ፤

👉ሁለተኛው አማራ ልዩ ኃይል ሌላኛው ጫና እነማይካድራን ማስለቀቅ፣ የሉግዲ
መሿለኪያን ማስለቀቅ ወደ ሱዳን የሚሄደውን የትህነግ ኃይል የሚሾልከበትን
በር መዝጋትና የሁመራን ቦታ መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን የተከበቡ የመከላከያ
ሰራዊት አባላትን ከጓደኞቻቸው የአስክሬን ሽታ፣ ከተከበቡበትም ሕይወታቸውን
ማትረፍ ግዴታው ነበረ፤ ሀላዊና በረከት ላይ ይህንን አደረገ፤

👉ወደ ማይካድራ ስንደርስ ደም ፈሷል፤ ሁሉም አዝኗል፤ ሁሉም ይተኩሳል፤
ከመኪና ስንወርድ ሁሉም በእኛ ተቆጥቷል፤ ምክንያቱም እኛ ድሉን ስናበስር
ነው የቆየነው፤

👉እዛ ቦታ ላይ ደም ፈሷል፤ የራሳችንን ወገን ደም ረግጠናል፤ እዛ ቦታ ላይ በወደቀ
የአስክሬን ብዛት መካከል መቆም ምናልባትም ትንፋሽን መቁጠር እስከሚያክል
ድረስ የምንተነፍሰው አየር ያስጨንቀን ነበር፤

👉በእንደዚህ አይነት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ትንፋሽ ቅንጦት ነው፣ የልብ ምት
ቅንጦት፤ ሁሉም ጭንቅላታቸው ተከፍቷል፤ ሁሉም ሆዳቸው ተከፍቷል፤ ሁሉም
ደምተዋል፤ ሁሉም ወድቀዋል፤ አልጋ ያገኙት በጣም ጥቂት ናቸው፡፡ በእነዚህ
መሃል መቆም በጣም ከባድ ነበር፤

👉በጋራ ሆነን ይህንን ነገር ለዓለም ማሳወቅ ነበረብን፤ ይህንን ዘግተነው ካለፍን
አደገኛ ነበረ፤ መበርታት ነበረብን፣ ደም ረግጠን ነው የቆምነው፤ ሁላችንም
ደም ረግጠናል፡፡

👉ይህንን ለቅሶ እዛ አላለቀስኩትም፣ ሰላም ስለሆነ ነው፤ ማልቀስም ሰላም
በሆነበት ቦታ ነው የሚቻለው፣

👉ህዝብን አነጋገርን ወስደው እንደ ቀበሯቸው ነገሩን፤ ነገር ግን የተገደሉት እነዚህ
ብቻ አይደሉም አሉን፤

👉ከቢሮ መቀሌ ትገባላችሁ የሚል ትዕዛዝ ተሰጥቶናል፤ መቀሌ መግባት ለእኛ
መዝናናት ነበር፤ ስለሆነም በየቦታው የተደፉ ሰዎችን ማሳየት ነበረብን፤ አሞራና
ዝንብ እየተከተለን በየቦታው የወደቁ አስከሬኖችን አሳየን፤

👉 ዓለም የትህነግን መጥፎነት ያየው ያን ቀን ነበር፤ ምክንያቱም በፕሮፓጋንዳ
ተሸፍኖ ነበረ፤ እኛ ገለጥነው፤

👉 ከአከባቢው ሰው ጋር ተባብረን በመጀመሪያው ቀን የ74 ሰዎችን አስከሬ
አገኘን፤ 74ቱም ስዎች በጋራ ነው የተቀበሩት፤ የህጻናት ጫማ ነበረ፣ የሴቶች
ነጠላ ነበረ፤

👉 አቡነ አረጋዊ በሚባለው ቦታ ላይ የተቀበሩት ሰዎች ቁጥራቸው አይታወቅም፤
በጣም የሚገርመው አስክሬኖቹን መቅበር የማይቻልበት ጊዜ ነው የተደረሰው፤
የአካባቢው ሰው የአስከሬኑን ሽታ ለመቋቋም ሲል ሽቶ ተጠቅመዋል፤

👉 ከሁለት ቀናት በኋላ ተመሳሳይ ጥቆማ ደረሰን፤ አሞራ አከባቢውን ይዞራል፤
ዝንቦች ወረውታል፤ 18 የደረቀ አስክሬን አንድ ላይ ሳይቀበሩ አገኘን፤ እንዲሁ
ነው የተደፉት፤

👉 እስከ መቼ ነው በዚህ ሁኔታ የምንቀጥለው አሁን ያለን አማራጭ ኢትዮጵያ
የሁላችንም ድምቀት መሆን አለባት፤ የሁላችንም ጌጥ ነው መሆን ያለባት፤

👉 ኢትዮጵያን ተጭኖ የተለያዩ ብሔሮችን ዘር እየለየ የሚያጭድ የተንኮል ገበሬ
ካለና እሱ ካልፀዳ ኢትዮጵያዊነት ኢትዮጵያ መሆን አይችልም፤

👉 እያንዳንዱ ወታደር የተዋጋው በሸተተ ጓደኛው አስክሬ ጎን ሆኖ ነው፤ እዚህ
ቦታ ላይ መቆም አስክሬን ማየት በጣም ቀላል ሊሆን ይችላል፤ እኔ

አይቻለሁ ከዚህ በፊት ልጄን ቀብሬያለው፤ አልከበደኝም፤ ማይካድራ ላይ ግን
መቆም አይቻልም፤ ይሀንን መመስከር አይቻልም፤

👉 ሰው ካልሆንን ኢትዮጵያዊ መሆን አይቻልም፤ እነዛ ሰዎች ሰውነታቸው
ስለካዳቸው ነው ኢትዮጵያዊ መሆን ያልቻሉት፤

👉 ከዚህ በኋላ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የመጨረሻውን የተንኮል ስለት የያዘው አካል
በመከላከያ ሰራዊት፣ በልዩ ኃይል አባላት፣ በአፋር ልዩ ኃይል አባላት፣ በሁሉም
ኢትዮጵያዊ ደጀንነት ተሰናብቷል፤
ወታደሮችን በሲኖ ትራክ እስከመጨፍለቅ የዘለቀው የጁንታው የክፋት ጥግ
******************************
(ኢ ፕ ድ)
ሃምሳ አለቃ ደረጀ አንበሳ በመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ የጥገና ባለሙያ ናቸው። በሙያቸው አገራቸውን ሌት ተቀን ከማገልገላቸውም በላይ እንደማንኛውም የመከላከያ አባል ለትግራይ ህዝብ በችግሩ ጊዜ ከጎኑ በመቆም አጋርነታቸውን ሲገልጹ ኖረዋል። የህዝብና የአገር ከለላና መከታ የሆነው የኢፌዴሪ መከላከያ አባል እንደመሆናቸው አንድም ቀን በአገር ልጅ የባንዳነት ተግባር ይፈጸምብኛል ብለው አስበውም አያውቁም።
ይሁንና በእናት ጡት ነካሾች ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም ከምሽቱ አራት ሰዓት ያልታሰበ ጥቃት ተፈጸመባቸውና ያለምንም ጥፋታቸው ተይዘው ለእስር መዳረጋቸውንና ቀላሚኖ እሰርቤት መታሰራቸውን ይገልጻሉ።
"ከቀላሚኖ እስር ቤት ወደ አግቤ በመቀጠልም ከትንሽ ቀን በኋላ ወደ ተንቤን መምህራን ኮሌጅ ወሰዱን። የመከላከያ ሠራዊትን የከባድ መሳሪያ ድምፅ ሲሰሙ የ90 ኪሎ ሜትር የእግር ጉዞ አስጀመሩን። ልክ 40 ኪሎ ሜትር እንደተጓዝን ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ሲኖ ትራክ መኪና ከኋላችን መጣ። ተጓዡ ወደ 1,200 ሰው ነበር። ከአስፋልት እንድንወጣ ካለመፈቀዱም በላይ ከአስፋልቱ መሀል ከወጣን ልዩ ሀይል ተኩሶ ይመታን ነበር። ከግራና ከቀኝ ገደላማ የሆነ ጠባብ ቦታ ላይ ስንደርስ ሲኖ ትራክ መኪና ልከው ከኋላችን ነዱብንና የሚገድለውን እየገደለ፣ ያቆሰለውን እያቆሰለ ሄደብን።
እኔንም አንድ እግሬን አገኘኝና እግሬ ከተሰበረ በኋላ ተንከባልዬ ጉድጒድ ውስጥ ገባሁ። እዚያው ጉድጓዱ ውስጥ ከተጎዱ ጓደኞቼ ጋር ተኝቼ አደርኩ። ሲኖ ትራኩ ቢያንስ እስከ 50 ሜትር የተጓዘው በሰዎች ላይ ነበር። በዚህም ግማሹ ሞተ፣ ግማሹ ቆሰለ የቀረውም ወደገደል ገባ። እንግዲህ የራሳችን ወገን ነው እንዲህ አይነት በደል የፈፀመብን። ይህ ደግሞ በጣም የሚያሳዝን ድርጊት ነው። ስንት ዓመት ሙሉ አብረናቸው ኖረን በመኪና ሲጨፈልቁን በጣም ነው የተሰማኝ፤ በጥይት ቢገድሉኝ ይሻል ነበር" ይላል::
በወቅቱ ሴቶችም ህፃናትም አብረውን ነበሩ ማን እንደሞተ ማን እንደተረፈ አንኳን አላውቅም ያለው ወታደሩ "በወቅቱ በሕይወት የተረፋትም ተበታተኑ፤ አንዳንዶቹም ቆስለው ወደጫካው ገቡ፤ የሞቱትም እዛው ቀሩ አምስት የምንሆን ሰዎች እዛው አድረን ከሞቱት ሰዎች መሀል በሕይወት ወጣን። የሞቱ ልጆችን እንኳን ለመለየት አልቻልኩም፤ አጠገቤ ነው እየጮሁ የሞቱት፤ ምንም ልረዳቸው አልቻልኩም። በወቅቱ እኔም በሁለት እግሬ መቆም አልችልም ነበርና በጉልበቴ ዳዴ እያልኩ ነው የወጣሁት" ሲል የውቅቱን አሳዛኝ ሁኔታ ይገልፃል::
"እኛኮ ከሌሊቱ 11 ሰዓት እየተነሳን አጨዳ የምናጭድ፤ ኮረና ገባ ሲባል ብር እያዋጣን የምንደግፍና ከደሞዛችን እየቆረጥን የልማት ስራዎችን የምንሰራ ነን። እኛ ለትግራይ ህዝብ ልማት ወደኋላ ብለን አናውቅም። ይሁንና ጁንታውና የእሱ ተላላኪዎች በሰው ላይ የማይፈፀም ድርጊት ነው የፈፀሙብን። ሰብስበው በቦንብ ቢያቃጥሉን ወይም በጥይት ቢገድሉን ይሻል ነበር። የውጪ ጠላት እንኳን በመኪና ሰውን ደፍጥጦ አይገድልም። ድርጊቱ ከተፈፀመብን በኋላ በመኪና መንገድ ላይ ስንሄድ እየተሸማቀቅን ነው። ጭንቅላታችን ራሱ ተጎድቷል::
ሌላው ተመሳሳይ ድርጊት የተፈፀመበት አምሣ አለቃ ወንድማገኝ ወልደገብርኤል ነው። እሱ እንደሚገልፀው በልዩ ሀይል እና በሚሊሻ ታጅበን በእግር እየተጓዝን ሳለ ከአስፓልቱ እንዳትወጡ አሉን እኛም ፈንጂ ያለ መስሎን የአስፋልቱን መሀል ይዘን መጓዝ ጀመርን። ጨለምለም ሲል ከኋላችን ሲኖትራክ መኪና መጣ፤ ከፊት ለፊት ተኩስ ተከፈተብን፤ እንዳንመታ ብለን ሁላችንም ተኛን፤ በዚህ ወቅት ሲኖ ትራኩ እየጨፈለቀን ሄደ ።
ግማሹ እየተንከባለለ ወደገደል ገባ፤ ተገጭተን የተረፍነው በማግስቱ ተነሳን፤ ብዙዎች ግን በሚያሳዝን ሁኔታሞቱ፤ አንዳንዶቹም ቆሰሉ፤ አሽከርካሪው ለመትረፍ የሚሞክሩ ሰዎችንም ዚግዛግ እየነዳ ነበር ሲጨፈልቃቸው የነበረው። በእግራችን መሄድ አቅቶን ጅብ ይብላን ብለን እዛው ከተኛን በኋላ ታፍነው በመከላከያ ሰራዊት እርዳታ የተለቀቁ እስረኞች እየረዱን የተወሰነ ርቀት ከተጓዝን በኋላ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ደርሰው ወደዚህ አመጡን። ሲሉ ደረሰባቸውን ግፍ አስረድተዋል።
ኢያሱ መሰለ