Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ከ7 አስከ 10ኛ ክፍል ያሉ ትምህርቶች በዲቪዲ ለገበያ ሊቀርቡ ነው
*********
(ኢ.ፕ.ድ)

ስኮላር ኢ ፐብሊሸር የተባለ የግል ማህበር ከ7ኛ እስከ 10ኛ ያሉ የሂሳብና የሳይንስ ትምህርቶችን በዲቪዲ አምርቶ ኢ ፋኖስ በተባለ የምርት መጠሪያ በገበያ ላይ ሊያሰራጭ መሆኑን አስታውቋል።

ዲቪዲዮዎቹ የትምህርት መስጫ፣ የማጠቃለያና የጥያቄና መልስ ክፍል ፣የማጠቀሻ መፅሀፈት ፣ ላብራቶሪና ጭብጥ ሀሳቦችን በቪድዮና በምስል ያቀርባሉ ሲሉ የማህበሩ አመራሮች ለጋዜጠኞች
ዛሬ ሀሙስ የካቲት 12 ለጋዜጠኞች በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

ዲቪዲዎችም በትምህርት ቤቶችችና በትምህርት መሳሪያ መሸጫ ቤቶች በኩል የሚከፋፈሉ ሲሆን የአንድ ዲቪዲ ዋጋም 98 ብር እንደሆነ ገልፀዋል።

ማህበሩ ከ11ኛ እስከ 10ኛ ያሉ የሂሳብና የሳይንስ ትምህርቶችን በዲቪዲ ለማሰራጨት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

ከኬጂ አስከ ስድስተኛ ያሉ እንግሊዘኛ፣የአማረኛ ቋንቋና የአካባቢ ሳይንስ ትምህርቶችን ተረቶችን ፣ጨዋታዎችን ጭምር ከመልቲሚድያ መልክ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።
በዳግም ከበደ
ከአዲስ አበባ የተነሳው የአደዋ ተጓዥ ቡድን ዛሬ ደሴ ደርሷል። ቡድኑም በደሴ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ይህ አቀባበልና ጉብኝት በድርጅታችን ካሜራ ማን ዳኜ አበራ እንዲህ ተዘግቧል።
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተሰጠ ማሳሰቢያ
*****************************
(ኢ.ፕ.ድ)

ነገ ዓርብ የካቲት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ፣
• በኢትዮ ፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣

እንዲሁም ቅዳሜ የካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በፍሊንት ስቶን ሪል እስቴት፣ በአትሌቶች መንደር፣ በለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊት ለፊት እና አካባቢዎቻቸው፣

በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ፤ ክቡራን ደንበኞቻችን ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የከባድ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ሰዓት ማሻሻያ ተደረገበት።
በአዲሱ ማሻሻያም ከባድ ተሽከርካሪዎች ጠዋት ከ1-3 ሰአት እንዲሁም ከሰዓት ከ 10:30-12:00 ውጪ ባሉ ሰዓቶች እንዲንቀሳቀሱ ተወስኗል።

ማሻሻያው የተደረገው የተለያዩ ተቋማት በሰዓት ገደቡ ምክኒያት በተለይም የግንባታ ስራዎቻቸውን ለማከናወን መቸገራቸውን ቅሬታ በማቅረባቸው ነው።

በመሆኑም የትራፊክ እንቅስቃሴውን ጫና ውስጥ በማይከት መልኩ ማሻሻያው ተደርጓል።

እስካሁን በነበረው ህግ በከተማዋ የሚገኙ ከባድ ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር መንቀሳቀስ የሚፈቀድላቸው።
ከ124 አመት በፊት የአጼ ምንሊክ የክተት አዋጅ
*እግዚእብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ እገር እስፍቶ እኖረኝ ፣ እኔም በእግዚእብሔር ቸርነት ጉዛሁ።እንግዲህ ብሞትሞ ሞት የሁሉም ነውና። ስለ እኔ ሞት እላዝንም ደግሞ እግዚእብሔር አሳፍሮኝ እያውቅም ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ እልጠራጠርም ፣ አሁንም አገር የሚያጠፋ ሀይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚእብሔር የወሰነልንን የባህር በር እልፎ መጥቷልና አሁን ግን ሀገሬን አሳልፌ እልስጥውም ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሽዋ ስው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድርስ ወረኢሉ ከተህ ላግኝህ"
የአድዋ ተጓዧች እዚች ታሪካዊ ከተማ ደርሰው ደማቅ አቀባበል ተድርጎላቸዋል።
ፎቶ ዳኜ አበራ
በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥሮ በመለያ ማእከል ገብቶ የነበረው ግለሰብ ከበሽታው ነጻ መሆኑ ተገለጸ
*************************
(ኢ.ፕ.ድ)

ዛሬ የኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶበት በመለያ ማዕከል ተለይቶ ክትትል ሲደረግለት የቆየው ግለሰብ ከበሽታው ነጻ መሆኑ ተገለጸ።

ከግለሰቡ ናሙናው ተወስዶ በተደረገው የላቦራቶሪ ምርመራ ከቫይረሱ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አ ታውቋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ለካራማራ ድል በዓል ያስተላለፉት መልእክት
************************

ከዚያድ ባሬ መራሹ የሶማሊያ ወራሪ ኃይል ጋር በነበረን ተጋድሎ ወሳኝ ድል ላስመዘገብንበት የካራማራ ድል በዓል እንኳን አደረሳችሁ። የ1967ቱ የሶማሊያ ወረራ ሀገራችን ከአብዮት ፍንዳታው ጭጋግ ባልወጣችበትና የእርስ በርስ ግጭት ላይ በነበረችበት ጊዜ የተከሠተ ነው።

ኢትዮጵያን የወረሩ አብዛኞቹ ኃይሎች እንደሚሠሩት ስሕተት ዚያድ ባሬም ተሳሳተ።

ሀገር የደከመች መስሎት ኢትዮጵያን የማሸነፊያ ጊዜ የደረሰለት መሰለው። በዚህ የተሳሳተ ስሌት ተመርቶ ወረራውን ፈጸመ። በመጀመሪያ አካባቢ እንዳሰበውም የጎላ መከላከል ሳይገጥመው ሰፊ የሀገራችንን መሬት ማካለል ችሎ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያውያን እንደፍግ ተኝተው እንደ እቶን በተነሡ ጊዜ ምን እንደሚያደርጉ በዚህ ወረራ ጊዜ ታየ።

በአጭር ጊዜ “የእናት ሀገር ጥሪ” የተሰባሰቡ፣ በቂ የሥልጠናም ሆነ የዝግጅት ሁኔታ ያልነበራቸው፣ ነገር ግን ከየትም የማይበደሩት የሀገር ፍቅርና የማሸነፍ ወኔ ያላቸው ውድ ኢትዮጵያውያን ወረራውን በስኬት መቀልበስ ቻሉ።

መንግሥታትን በሀገር ውስጥ ክዋኔያቸው በአንድም በሌላም ልንመዝናቸው እንችላለን። ነገር ግን የሀገርን ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር ለማስጠበቅ የሚከፈሉ መሥዋዕትነቶች በየትኛውም ዘመን ቢፈጸሙ የሀገራችን ታሪካዊ ኩራት ናቸው።

የደርግ መንግሥትም በአጭር ጊዜ ጥሪ አቅርቦ፣ አሠልጥኖና አደረራጅቶ የሀገርን ክብር ለማስመለስ ያደረገው ተጋድሎና ያስመዘገው ድል የሁላችንም የኢትዮጵያውያን የአልበገር ባይነትና ለሀገር የመሥዋዕትነት የመክፈል ታሪካችን አካል ነው።

ሁሌም በውስጣችን ክፍተት ሲኖር የውጭ ጠላት እንጋብዛለን፤ ስንጠናከር ግን የታፈርንና የተከበርን እንሆናለን።