በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን፣ አዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎች ድጋፍ አደረጉ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ራያ ቆቦ፡- በአዲስ አበበ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን ፣ የአዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ህግን ለማስከበር ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎችን በግንባር ተገኝተው ለሰራዊቱ አስረክበዋል፡፡
አቶ አብዱልጀሊል አብዱሮ የአዳማ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ በርክብክቡ ወቅት እንደተናገሩት፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሰራዊትና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት በመፈጸም ያነገበውን ሀገር የማፍረስ ዓላማ ለማኮላሸት መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር ርምጃ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ይደግፋል፡፡
የጁንታው አበላት ሀገርን ለማፍረስ ሲል የፈጸማቸውን የሽብር ተግባራት የክልሉ ህዝብ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ እንዳወገዘ ገልጸዋል፡፡
ህዝቡ ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን በመቆም ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ በመግለጽም ከተጠቀሱት ውስን የኦሮሚያ አካባቢዎች የተሰበሰበው ድጋፍ የሞራል ስንቅ ይሁን በሚል ይዘን መጥተናል ብለዋል፡፡
በዚህም መሰረት ከፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚ ልዩ ዞንና ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች የተሰባሰቡ 196 የዕርድ ሰንጋዎች እና ከምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ 230 ፍየሎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ለሠራዊቱ አስረክበዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ህዝብ መንግስት ተገዶ የገባበትን ህግ የማስከበር ርምጃ እንደሚደግፍና ከመከላካያ ሰራዊቱ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል፤ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አቶ አብዱልጀሊል ገልጸዋል፡፡
የራያ አላማጣና አካባቢው ግንባር አመራር አባል ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን በበኩላቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ተወካዮች ረዥም መንገድ ተጉዘው ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰራዊቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ተከትሎ ህዝቡ ከሰራዊቱ እኩል መቆጣቱ ለሀገሩና ለሰራዊቱ ያለውን ፍቅር፣ ክብርና ተቆርቋሪነት የሚያሳይ ነው፡፡
ለሰራዊቱ ድጋፍ በማድረግና ደጀን በመሆን ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሚደረገው ርብርብ የሚመሰገን ነው ብለዋል፡፡
ሰራዊቱ ህዝብን በማቀፍ በተሰማራባቸው ህግን የማስከበር ዘመቻዎቹ ሁሉ ውጤታማ እንደሆነና በሚቀጥሉት ቀናትም ሌሎች ድሎች እንደሚሰሙ ተናግረዋል፡፡
አንድ ተዋጊ ምንም አይነት ዘመናዊ መሳሪያ ቢታጠቅ የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ውጤታማ አይሆንም ያሉት ጀነራሉ እስከ አሁን የተገኙት ድሎችም የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ውጤቶች ናቸው ብለዋል፡፡
ይህ ከሀዲ ቡድን ተደምስሶ ወይም በቁጥጥር ስር ውሎ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰላሟን ታገኛለች ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ ፣ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንሳይ መኮንን ተገኝተው እንግዶቹን ተቀብለዋል፡፡ ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢያሱ መሰለ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ራያ ቆቦ፡- በአዲስ አበበ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን ፣ የአዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ህግን ለማስከበር ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎችን በግንባር ተገኝተው ለሰራዊቱ አስረክበዋል፡፡
አቶ አብዱልጀሊል አብዱሮ የአዳማ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ በርክብክቡ ወቅት እንደተናገሩት፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሰራዊትና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት በመፈጸም ያነገበውን ሀገር የማፍረስ ዓላማ ለማኮላሸት መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር ርምጃ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ይደግፋል፡፡
የጁንታው አበላት ሀገርን ለማፍረስ ሲል የፈጸማቸውን የሽብር ተግባራት የክልሉ ህዝብ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ እንዳወገዘ ገልጸዋል፡፡
ህዝቡ ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን በመቆም ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ በመግለጽም ከተጠቀሱት ውስን የኦሮሚያ አካባቢዎች የተሰበሰበው ድጋፍ የሞራል ስንቅ ይሁን በሚል ይዘን መጥተናል ብለዋል፡፡
በዚህም መሰረት ከፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚ ልዩ ዞንና ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች የተሰባሰቡ 196 የዕርድ ሰንጋዎች እና ከምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ 230 ፍየሎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ለሠራዊቱ አስረክበዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ህዝብ መንግስት ተገዶ የገባበትን ህግ የማስከበር ርምጃ እንደሚደግፍና ከመከላካያ ሰራዊቱ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል፤ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አቶ አብዱልጀሊል ገልጸዋል፡፡
የራያ አላማጣና አካባቢው ግንባር አመራር አባል ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን በበኩላቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ተወካዮች ረዥም መንገድ ተጉዘው ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰራዊቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ተከትሎ ህዝቡ ከሰራዊቱ እኩል መቆጣቱ ለሀገሩና ለሰራዊቱ ያለውን ፍቅር፣ ክብርና ተቆርቋሪነት የሚያሳይ ነው፡፡
ለሰራዊቱ ድጋፍ በማድረግና ደጀን በመሆን ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሚደረገው ርብርብ የሚመሰገን ነው ብለዋል፡፡
ሰራዊቱ ህዝብን በማቀፍ በተሰማራባቸው ህግን የማስከበር ዘመቻዎቹ ሁሉ ውጤታማ እንደሆነና በሚቀጥሉት ቀናትም ሌሎች ድሎች እንደሚሰሙ ተናግረዋል፡፡
አንድ ተዋጊ ምንም አይነት ዘመናዊ መሳሪያ ቢታጠቅ የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ውጤታማ አይሆንም ያሉት ጀነራሉ እስከ አሁን የተገኙት ድሎችም የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ውጤቶች ናቸው ብለዋል፡፡
ይህ ከሀዲ ቡድን ተደምስሶ ወይም በቁጥጥር ስር ውሎ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰላሟን ታገኛለች ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ ፣ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንሳይ መኮንን ተገኝተው እንግዶቹን ተቀብለዋል፡፡ ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢያሱ መሰለ
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ።
ኩባንያው በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቁጥርም 6800 መሆኑን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው ወደ 6800 የፈለገውን የገንዘብ መጠን በማስገባት በመላክ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ክብር እና አጋርነት ማሳየት እንደሚችልም ኩባንያው ግልጽ አድርጓል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ።
ኩባንያው በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቁጥርም 6800 መሆኑን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው ወደ 6800 የፈለገውን የገንዘብ መጠን በማስገባት በመላክ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ክብር እና አጋርነት ማሳየት እንደሚችልም ኩባንያው ግልጽ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የተከማቹ 19 ቦምብ እና ሌሎች የጦር መሣሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ውስጥ ኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገ አሰሳ 19 ቦምብ፣ 55 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 21 ሽጉጦች፣ 2 ኤስ ኬ ኤስ ጠመንጃ፣ 3 ቺኮዝ፣ 1 ብሬን፣ 6 ቺቺ ጠመንጃ እና ሌሎች ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 113 የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
በተጨማሪም 309 የሽጉጥ እና 4829 ዓይነታቸው የተለያየ ጥይቶች ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል።
በዚሁ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ትራኮን ሪልስቴት አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ 64ሺህ 200 የአሜሪካ ዶላር መያዙንና ጉዳዩ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተያዘውን ጨምሮ ከኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ 37 የእጅ ቦምብ፣ 1 ብሬን፣ 5 የጦር ሜዳ መነጽር፣ 18 የሬዲዮ መገናኛ ቁሳቁሶች፣ 589 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 350 ሽጉጦች፣ 46 የተለያዩ ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 1023 የተለያዩ ዓይነት የጦር መሣሪያዎች ከ10 ሺህ 404 መሰል ጥይቶች ጋር በብርበራ እና በፍተሻ መያዙን ገልጿል።
738 የተለያዩ የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት በፍተሻው ወቅት መገኘታቸውንም ጠቅሷል።
በተለያዩ ቦታዎች ተጥለው የተገኙ 7 የእጅ ቦምብ፣ 5 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 1 ተቀጣጣይ ፈንጂ፣ 3 ሽጉጥ፣ 2 የተለያዩ ጠመንጃዎች ከመሰል 841 ጥይቶቻቸው ጋር በኅብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውንም አመልክቷል።
የጥፋት ኃይሎች ለአዲስ አበባ ከተማ የደገሱላትን ሽብርና እልቂት ለመቀልበስ የሚከናወነው ጠንካራ ሕግን የማስከበር ተግባር በኅብረተሰቡ የዕለት ተዕለት መረጃ ሰጪነት እየታገዘ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ውስጥ ኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገ አሰሳ 19 ቦምብ፣ 55 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 21 ሽጉጦች፣ 2 ኤስ ኬ ኤስ ጠመንጃ፣ 3 ቺኮዝ፣ 1 ብሬን፣ 6 ቺቺ ጠመንጃ እና ሌሎች ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 113 የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
በተጨማሪም 309 የሽጉጥ እና 4829 ዓይነታቸው የተለያየ ጥይቶች ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል።
በዚሁ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ትራኮን ሪልስቴት አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ 64ሺህ 200 የአሜሪካ ዶላር መያዙንና ጉዳዩ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተያዘውን ጨምሮ ከኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ 37 የእጅ ቦምብ፣ 1 ብሬን፣ 5 የጦር ሜዳ መነጽር፣ 18 የሬዲዮ መገናኛ ቁሳቁሶች፣ 589 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 350 ሽጉጦች፣ 46 የተለያዩ ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 1023 የተለያዩ ዓይነት የጦር መሣሪያዎች ከ10 ሺህ 404 መሰል ጥይቶች ጋር በብርበራ እና በፍተሻ መያዙን ገልጿል።
738 የተለያዩ የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት በፍተሻው ወቅት መገኘታቸውንም ጠቅሷል።
በተለያዩ ቦታዎች ተጥለው የተገኙ 7 የእጅ ቦምብ፣ 5 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 1 ተቀጣጣይ ፈንጂ፣ 3 ሽጉጥ፣ 2 የተለያዩ ጠመንጃዎች ከመሰል 841 ጥይቶቻቸው ጋር በኅብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውንም አመልክቷል።
የጥፋት ኃይሎች ለአዲስ አበባ ከተማ የደገሱላትን ሽብርና እልቂት ለመቀልበስ የሚከናወነው ጠንካራ ሕግን የማስከበር ተግባር በኅብረተሰቡ የዕለት ተዕለት መረጃ ሰጪነት እየታገዘ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የሻለቃው ትውስታ- ከሸሸቢት እስከ ዓዲ ዳዕሮ
*************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲነብሪ አካባቢ ታንኮች እዚህም እዚያ ተፈነጣጥረው ቆመው ግዳጃቸውን ለመፈጸም በተጠንቀቅ እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ የሽብርተኛውን የህወሓት ጁንታ ታጣቂዎች ለመደምሰስ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ከእነዚህ ታንኮች መካከል የአንዷ ሹፌር ሻለቃ ባሻ በየነ ይባላል፡፡
ሻለቃ ባሻ የሰሜን ዕዝ ስምንተኛ መካናይዝድ አባል ነው፡፡ እሱም ሆነ ጓዶቹ ቀን የአርሶ አደሩን ምርት ለመሰብሰብ አጨዳ ላይ ውለውና በተግባራቸው ረክተው ደክሟቸው አገር ሰላም ብለው በተኙበት ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ የትግራይ ልዩ ሀይል ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ ነው ከእንቅልፋቸው የነቁት ።
በወቅቱም የከበባቸው የጽንፈኛው የህወሓት ሀይል መትተው መመለስ መቻላቸውን ሻለቃ በሻ ያስታወሳሉ። ይህ አሳዘኝ ክስትት በተከሰተ ማግሰት የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች የሻለቃ አመራራቸው በስሩ የሚገኙ ሁሉም የሠራዊት አባላት መሳሪያውን ወደ መጋዘን አስገቡ በማለት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ያስታውሳሉ።
በተቃራኒው የእሱን ትዕዛዙን ሊያስተባብር ወደ ሠራዊቱ የመጣው ኮነሬል ዳኘው ጦሩ መሳሪያውን ወደ መጋዘን እንዳያስገባ ይልቁኑ በየምሽጉ ሆኖ ራሱን እንዲከላከልና ሁኔታዎችን በጥብቅ እንዲከታተል አደረጉ ፤የጁንታው ቡድን ተላላኪ የሆነው ሻለቃ ትዕዛዙ ሊፈጸም አለመቻሉን ለትግራይ ልዩ ሀይል መረጃ በመስጠቱ በማግስቱ ከቀኑ 5፤ከ30 ላይ ከአንድ ሺ በላይ የሚሆኑ የትግራይ ልዩ ሀይል የሦስተኛ ሻለቃ ካምፕ ውስጥ በሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የተጠናከረ ጥቃት ከፈቱ።
በዚህ ጊዜም በሠራዊቱ ውስጥ የነበሩ የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች ጦሩ ከተከፈተበት ጥቃት እንዳይከላከል ሲያዘናጉ ቆይተው ሠራዊቱ ለመከላከል ከግቢ እንደወጣ የሻለቃ አመራሮች ፣ኦፕሬተሮችና የመድፍ አስተኳሽ፣ የታንክ ሹፌሮች ወደ ትግራይ ልዩ ሀይል ተቀላቀሉ ።
በወቅቱ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ቁጥር 225 ቢሆንም በብረት ለበስ ብርታት ጽንፈኛው ኃይል በሠራዊቱ ላይ የሰራውን ቀለበት ሰብረው ሊወጡ መቻላቸውን ይናገራሉ። ከረፋዱ 5 ሰዓት በተጀመረው ውጊያም ከቀኑ10 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ጽንፈኛውን ሀይል በብቃት መክተው መልሰዋል። በተለይ መድፈኛ ሻለቃዋን ለማፈን ያደረገው ጥረት በጀግናው ሰራዊት ተጋድሎ የመድፎቹን መርፌ ማውጣት በመቻሉ ጽንፈኛው ሀይል መድፎቹን ጉትቶ ይዞ እንዳይሄድ አድርገዋል።
የእኛ ካምፕ ከአዲሃገራይ 7 ኪሎ ሜትር ይርቃል የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፣አዲሃገራይ ወደ ሚገኘው የክፍለ ጦር ማዘዣቸው ጽንፈኛውን ሀይል እየተከላከሉ መሄዳቸውን ጠቅሰው፤ከዚያም ሀይል ጦሩ በማህይንጻ አድርጎ ጓል ባድሜ አቋርጦ ወደ ኤርትራ ሸሸቢት ወደ ምትባል ስፍራ ማፈግፈጋቸውን ነው የነገሩን ።
ከሁለት ቀናት ራስን የመከላከልና አድካሚ የእግር ጉዞ በኋላም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከ25 ደቂቃ አካባቢ ኤርትራ ሸሸቢት የምትባል ስፍራ ደርሰዋል ። በዚያም የኤርትራ ህዝብ በሸሸቢት ትምህርት ቤት የቁርስ ግብዣ እንዳደረገላቸው ገልጸውልናል።
ከ”36 ሰዓት በኋላ ነው በሸሸቢት ውሃ የቀረበልንና ምግብ ያገኘነው። በኮዳ ከያዝናት ውሃ በክዳኗ ፉት እያልንና ለሁለት ቀናት ምግብ ሳንበላ የጽንፈኛውን ቡድን ያልተመጣጠነ ጥቃት እየመከትን ኤርትራ ደረስን”ብለዋል።
ግዳጁን ከበድ የሚያደርገው ከውስጣችን ጓዶቻችን ብለን ስናምናቸው የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ከጎናችን ሆነው የእኛን ጓዶች መግደላቸውና መውጋታቸው ነው የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፤እነዚህ ካህዲዎች የታንክ ሹፌሮችን ሳይቀር ገድለውብን ፤በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ግፍ እንደሆነ አመልክተዋል።
አብረህ በልተህ፣ አብረህ ጠጥተህ ይህን አይነት ግፍ መፈጸም በኢትዮጵያ ባህል ያልተለመደ ነው። እኔን ጨምሮ ሌሎች ጓዶቻችን ከ1991ዓ.ም ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ ከምናገኘው ደመወዝ እያዋጣን ትምህርት ቤት፤ጤና ጣቢያ፣መንገድ ሰርተናል። ለህዝብ ጋሻ በሆነው መካላከያ ሠራዊት የዚህ አይነት ክህደት ሲፈጸም በጣም ያማል፤ ያበሳጫልና፣ ያናድዳል፤ያሳዝናልም ብሏል።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ፣ የሌላ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ጓዶቻቸውን በጥይትና በሳንጃ ሲመቱና ሲያርዱ በአይኔ አይቻለሁ፡ እኛም የአጸፋ እርምጃ የወሰድንባቸው አሉ፣ ክህደቱ በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝብም ጭምር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ይህም ድርጊት ሠራዊቱን በጣም አስቆጭቶት በሞራልና በወኔ ጽንፈኛውን ሀይል በመደምሰስ ድል በድል እየተቀናጀ ወደፊት እየገሰገሰ ነው። ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ድባቅ እየተመታ ነው ብለዋል ።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 11/2013
*************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲነብሪ አካባቢ ታንኮች እዚህም እዚያ ተፈነጣጥረው ቆመው ግዳጃቸውን ለመፈጸም በተጠንቀቅ እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ የሽብርተኛውን የህወሓት ጁንታ ታጣቂዎች ለመደምሰስ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ከእነዚህ ታንኮች መካከል የአንዷ ሹፌር ሻለቃ ባሻ በየነ ይባላል፡፡
ሻለቃ ባሻ የሰሜን ዕዝ ስምንተኛ መካናይዝድ አባል ነው፡፡ እሱም ሆነ ጓዶቹ ቀን የአርሶ አደሩን ምርት ለመሰብሰብ አጨዳ ላይ ውለውና በተግባራቸው ረክተው ደክሟቸው አገር ሰላም ብለው በተኙበት ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ የትግራይ ልዩ ሀይል ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ ነው ከእንቅልፋቸው የነቁት ።
በወቅቱም የከበባቸው የጽንፈኛው የህወሓት ሀይል መትተው መመለስ መቻላቸውን ሻለቃ በሻ ያስታወሳሉ። ይህ አሳዘኝ ክስትት በተከሰተ ማግሰት የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች የሻለቃ አመራራቸው በስሩ የሚገኙ ሁሉም የሠራዊት አባላት መሳሪያውን ወደ መጋዘን አስገቡ በማለት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ያስታውሳሉ።
በተቃራኒው የእሱን ትዕዛዙን ሊያስተባብር ወደ ሠራዊቱ የመጣው ኮነሬል ዳኘው ጦሩ መሳሪያውን ወደ መጋዘን እንዳያስገባ ይልቁኑ በየምሽጉ ሆኖ ራሱን እንዲከላከልና ሁኔታዎችን በጥብቅ እንዲከታተል አደረጉ ፤የጁንታው ቡድን ተላላኪ የሆነው ሻለቃ ትዕዛዙ ሊፈጸም አለመቻሉን ለትግራይ ልዩ ሀይል መረጃ በመስጠቱ በማግስቱ ከቀኑ 5፤ከ30 ላይ ከአንድ ሺ በላይ የሚሆኑ የትግራይ ልዩ ሀይል የሦስተኛ ሻለቃ ካምፕ ውስጥ በሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የተጠናከረ ጥቃት ከፈቱ።
በዚህ ጊዜም በሠራዊቱ ውስጥ የነበሩ የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች ጦሩ ከተከፈተበት ጥቃት እንዳይከላከል ሲያዘናጉ ቆይተው ሠራዊቱ ለመከላከል ከግቢ እንደወጣ የሻለቃ አመራሮች ፣ኦፕሬተሮችና የመድፍ አስተኳሽ፣ የታንክ ሹፌሮች ወደ ትግራይ ልዩ ሀይል ተቀላቀሉ ።
በወቅቱ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ቁጥር 225 ቢሆንም በብረት ለበስ ብርታት ጽንፈኛው ኃይል በሠራዊቱ ላይ የሰራውን ቀለበት ሰብረው ሊወጡ መቻላቸውን ይናገራሉ። ከረፋዱ 5 ሰዓት በተጀመረው ውጊያም ከቀኑ10 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ጽንፈኛውን ሀይል በብቃት መክተው መልሰዋል። በተለይ መድፈኛ ሻለቃዋን ለማፈን ያደረገው ጥረት በጀግናው ሰራዊት ተጋድሎ የመድፎቹን መርፌ ማውጣት በመቻሉ ጽንፈኛው ሀይል መድፎቹን ጉትቶ ይዞ እንዳይሄድ አድርገዋል።
የእኛ ካምፕ ከአዲሃገራይ 7 ኪሎ ሜትር ይርቃል የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፣አዲሃገራይ ወደ ሚገኘው የክፍለ ጦር ማዘዣቸው ጽንፈኛውን ሀይል እየተከላከሉ መሄዳቸውን ጠቅሰው፤ከዚያም ሀይል ጦሩ በማህይንጻ አድርጎ ጓል ባድሜ አቋርጦ ወደ ኤርትራ ሸሸቢት ወደ ምትባል ስፍራ ማፈግፈጋቸውን ነው የነገሩን ።
ከሁለት ቀናት ራስን የመከላከልና አድካሚ የእግር ጉዞ በኋላም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከ25 ደቂቃ አካባቢ ኤርትራ ሸሸቢት የምትባል ስፍራ ደርሰዋል ። በዚያም የኤርትራ ህዝብ በሸሸቢት ትምህርት ቤት የቁርስ ግብዣ እንዳደረገላቸው ገልጸውልናል።
ከ”36 ሰዓት በኋላ ነው በሸሸቢት ውሃ የቀረበልንና ምግብ ያገኘነው። በኮዳ ከያዝናት ውሃ በክዳኗ ፉት እያልንና ለሁለት ቀናት ምግብ ሳንበላ የጽንፈኛውን ቡድን ያልተመጣጠነ ጥቃት እየመከትን ኤርትራ ደረስን”ብለዋል።
ግዳጁን ከበድ የሚያደርገው ከውስጣችን ጓዶቻችን ብለን ስናምናቸው የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ከጎናችን ሆነው የእኛን ጓዶች መግደላቸውና መውጋታቸው ነው የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፤እነዚህ ካህዲዎች የታንክ ሹፌሮችን ሳይቀር ገድለውብን ፤በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ግፍ እንደሆነ አመልክተዋል።
አብረህ በልተህ፣ አብረህ ጠጥተህ ይህን አይነት ግፍ መፈጸም በኢትዮጵያ ባህል ያልተለመደ ነው። እኔን ጨምሮ ሌሎች ጓዶቻችን ከ1991ዓ.ም ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ ከምናገኘው ደመወዝ እያዋጣን ትምህርት ቤት፤ጤና ጣቢያ፣መንገድ ሰርተናል። ለህዝብ ጋሻ በሆነው መካላከያ ሠራዊት የዚህ አይነት ክህደት ሲፈጸም በጣም ያማል፤ ያበሳጫልና፣ ያናድዳል፤ያሳዝናልም ብሏል።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ፣ የሌላ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ጓዶቻቸውን በጥይትና በሳንጃ ሲመቱና ሲያርዱ በአይኔ አይቻለሁ፡ እኛም የአጸፋ እርምጃ የወሰድንባቸው አሉ፣ ክህደቱ በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝብም ጭምር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ይህም ድርጊት ሠራዊቱን በጣም አስቆጭቶት በሞራልና በወኔ ጽንፈኛውን ሀይል በመደምሰስ ድል በድል እየተቀናጀ ወደፊት እየገሰገሰ ነው። ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ድባቅ እየተመታ ነው ብለዋል ።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 11/2013
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የፈጸመው 27 ዓመታት የቆየበትን ስልጣን ዳግም ለመያዝ አስቦ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ አስታወቁ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም ወደ ግጭት የገባው የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በኃይል በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ይዞት ወደነበረው ስልጣን ለመመለስ በማሰብ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ ሚስተር ቲቦር ናጊ አስታወቁ፡፡
ምክትል ፀሃፊው ሚስተር ቲቦር ናጊ ለጋዜጠኞች በቴሌ ኮንፈረንስ እንደገለፁት፤ የህወሓት ቡድን ወደ ጥቃት የገባው የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር ከስልጣን በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት ለማስመለስና ወደ ሥልጣን ለመውጣት ያሰቡት ነው።
የህወሓት ቡድን የተከተለው ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለበት የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያዊያን በሚያስገርም ብሄራዊ ቁጭት ጠቅላይ ሚንስትሩን በመደገፍ እንደ አገር ያሰባሰበ ሆኗል ነው ያሉት።
የአገሪቱ ሕገ መንግስትም ራስን በራስ የማስተዳደርን መብት የሚደነግግ መሆኑን አስታውሰው፤ ቡድኑ የቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ በተቀራኒ የስጣን ጥምን ለማርካት ታስቦ የሚደረግ ስለመሆኑም አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም ሕግን ለማስከበር እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ትልቅ ትኩረት መስጠቱንም ጠቁመውል፡፡ በዚህ ህግን የማስከበር እርምጃ ንጹሃን እንዳይጎዱም ከለላ መደረጉ የአሜሪካም ፍላጎት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ መንግስትም ይህን በተግባር ለማዋል ቁርጠኛ ስለመሆኑና ንጹሃንን ለመታደግ ፅኑ ፍላጎት እንዳለው ሚስተር ቲቦር ናጊ አብራርተዋል፡፡
የትግራይ ህዝበ እንደጠላት አለመታየቱንና ፀቡም ከቡድኑ ጋር መሆኑን የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ ይልቁንም አገሪቱ በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ ቡድን የፈጠረውን ሀከት ለማረጋጋት እየተወሰደ የሚገኝ እርምጃ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ አባላት ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓም ሌሊት ጥቃት በመፈጸም ብዙዎችን ዘግናኝ በሆነ መልኩ እንደገደለና የተቀሩትን አፍኖ እንደወሰደ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ጁንታው ከፍተኛ ኪሰራ እየደረሰበት በመሆኑ እንደ ማይካድራ ባሉ ከተሞች በንጹሀን ላይ ጭፍጨፋ መፈጸሙ ይታወሳል፤ በዚህም አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳወገዙት ይታወቃል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም ወደ ግጭት የገባው የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በኃይል በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ይዞት ወደነበረው ስልጣን ለመመለስ በማሰብ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ ሚስተር ቲቦር ናጊ አስታወቁ፡፡
ምክትል ፀሃፊው ሚስተር ቲቦር ናጊ ለጋዜጠኞች በቴሌ ኮንፈረንስ እንደገለፁት፤ የህወሓት ቡድን ወደ ጥቃት የገባው የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር ከስልጣን በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት ለማስመለስና ወደ ሥልጣን ለመውጣት ያሰቡት ነው።
የህወሓት ቡድን የተከተለው ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለበት የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያዊያን በሚያስገርም ብሄራዊ ቁጭት ጠቅላይ ሚንስትሩን በመደገፍ እንደ አገር ያሰባሰበ ሆኗል ነው ያሉት።
የአገሪቱ ሕገ መንግስትም ራስን በራስ የማስተዳደርን መብት የሚደነግግ መሆኑን አስታውሰው፤ ቡድኑ የቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ በተቀራኒ የስጣን ጥምን ለማርካት ታስቦ የሚደረግ ስለመሆኑም አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም ሕግን ለማስከበር እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ትልቅ ትኩረት መስጠቱንም ጠቁመውል፡፡ በዚህ ህግን የማስከበር እርምጃ ንጹሃን እንዳይጎዱም ከለላ መደረጉ የአሜሪካም ፍላጎት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ መንግስትም ይህን በተግባር ለማዋል ቁርጠኛ ስለመሆኑና ንጹሃንን ለመታደግ ፅኑ ፍላጎት እንዳለው ሚስተር ቲቦር ናጊ አብራርተዋል፡፡
የትግራይ ህዝበ እንደጠላት አለመታየቱንና ፀቡም ከቡድኑ ጋር መሆኑን የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ ይልቁንም አገሪቱ በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ ቡድን የፈጠረውን ሀከት ለማረጋጋት እየተወሰደ የሚገኝ እርምጃ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ አባላት ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓም ሌሊት ጥቃት በመፈጸም ብዙዎችን ዘግናኝ በሆነ መልኩ እንደገደለና የተቀሩትን አፍኖ እንደወሰደ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ጁንታው ከፍተኛ ኪሰራ እየደረሰበት በመሆኑ እንደ ማይካድራ ባሉ ከተሞች በንጹሀን ላይ ጭፍጨፋ መፈጸሙ ይታወሳል፤ በዚህም አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳወገዙት ይታወቃል።
ሰበር ዜና!
አዲግራት ከተማ ከህወሓት ጁንታ ነጻ ወጣች
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአዲግራት ከተማን ዛሬ ከህወሃት ጁንታ ሃይል ነጻ አወጣ።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጠዋት የህወሃት ጁንታ ሃይልን ድል አድርጎ የአዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዳወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ አስታወቀ።
የመከላከያ ሠራዊታችን በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ እየገሰገሰ ነው።
አዲግራት ከተማ ከህወሓት ጁንታ ነጻ ወጣች
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአዲግራት ከተማን ዛሬ ከህወሃት ጁንታ ሃይል ነጻ አወጣ።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጠዋት የህወሃት ጁንታ ሃይልን ድል አድርጎ የአዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዳወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ አስታወቀ።
የመከላከያ ሠራዊታችን በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ እየገሰገሰ ነው።
“የሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላት እርቃናቸውን እንዲሆኑ ተደርገዋል፤ ተገድለዋል ፤ ታፍነው ተወስደዋል”
- ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከጥቃቱ ያመለጡ የሰራዊቱ አባል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ታጣቂዎች በሰሜን እዝ ሰራዊት ላይ ያደረሱትን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ ከእነሱ ጋር አልተባበርም ያሉትን
መግደላቸውንና የተቀረውን ማፈናቸውን ሌሎችን ደግሞ እርቃናቸውን ማባረራቸውን ከጥቃቱ ያመለጠው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ አስታወቀ።
የሰሜን ዕዝ 4ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከመከላከያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ እንደተናገረው፤ የክፍለ ጦሩ አመራሮች ከከሀዲው የህወሓት ጁንታ ጋር በነበራቸው ሚስጥራዊ ግንኙነት አስቀድመው ለዋርድያ መጠበቂያ ብቻ አንድ መሳሪያ በማስቀረት ሌላው መስሪያ ወደ ግምጃ ቤት እንዲገባ አድርገዋል።
በመቀጠልም የባንዳው ተላላኪ በሆነው የክፍለ ጦሩ አዛዥ ትዕዛዝ ገቢ የተደረገው መሳሪያ በከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የገለጸው ሻለቃ አምሳሉ፤ ሰራዊቱም ያልጠበቀው ክህደት ሲያጋጥመው ወደ መሳሪያ ግምጃ ቤት ቢያቀናም በታጣቂዎቹ ተኩስ እንደተከፈተበትና ግድያ እንደተፈጸመበት ተናግሯል።
ከሃዲው የህወሓት ቡድን መሳሪያ የሚቀመጥበትን ቦታ ተቆጣጥረው ከዘረፉና መግደል የፈለጉትን ከገደሉ በኋላ የተረፈውን ሰራዊት ልብሱን አስወልቀው እርቃኑን በማድረግ ወደ አዳራሽ አስገብተው እንዳፈኗቸው ጠቁመዋል።
ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ እንደገለፁት፣ ከሀዲው ቡድን በዕለቱ ከግድያ ለተረፉት የሰራዊቱ አባላት ያቀረበው አማራጭ አብሮ ለ20 ዓመት ከኖረና ለ20 ዓመት የትግራይን ህዝብ ላገለገለ ሰራዊት የማይገባው ነበር ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ “ከእኛ ጋር ወግኑ አሊያም በህይወታችሁ ፍረዱ የሚል አማራጭ እንዳቀረቡላቸው አስታውቀዋል።
የከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በክተት በታንከኛ፣ በመድፈኛ፣ በአየር መቃወሚያና በከባድ መሳሪያ ስልጣናዎችን እየወሰዱ እንደሆነ በመረዳታቸው ይህን ተግባር አግባብ እንዳልሆነ ሰራዊቱ ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበር ያስታወሰው ሻለቃው፤ የክፈለ ጦሩ አዛዥ “ከፈለጉ ሌላም ይታጠቁ የክልሉ ሥራ ነው” በሚል ያለመቀበል ሁኔታዎች እንደነበር ገልጿል።
በተለይ የአራተኛ ሜካናይዝ ክፍለ ጦር ኃላፊ ከሰራዊቱ በተቃራኒ የመቆምና ሃሳብን ያለመቀበል፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ሥሩ የሚል ትዕዛዛት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሷል።
“የክፍለ ጦሩ አመራር ለውጡን ባለመቀበል ወደ ብሔርተኝነት አሳተሳሰብ ያዘነበለ ስለነበር ሠራዊቱን አስመትተውታል” ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ ቀን ቀን ካንገት በላይ ሲያወሩ ይውላሉ፤ ማታ መቀሌ ሄደው ሲያሴሩ እንደነበር አስታውቋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42137
- ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከጥቃቱ ያመለጡ የሰራዊቱ አባል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ታጣቂዎች በሰሜን እዝ ሰራዊት ላይ ያደረሱትን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ ከእነሱ ጋር አልተባበርም ያሉትን
መግደላቸውንና የተቀረውን ማፈናቸውን ሌሎችን ደግሞ እርቃናቸውን ማባረራቸውን ከጥቃቱ ያመለጠው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ አስታወቀ።
የሰሜን ዕዝ 4ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከመከላከያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ እንደተናገረው፤ የክፍለ ጦሩ አመራሮች ከከሀዲው የህወሓት ጁንታ ጋር በነበራቸው ሚስጥራዊ ግንኙነት አስቀድመው ለዋርድያ መጠበቂያ ብቻ አንድ መሳሪያ በማስቀረት ሌላው መስሪያ ወደ ግምጃ ቤት እንዲገባ አድርገዋል።
በመቀጠልም የባንዳው ተላላኪ በሆነው የክፍለ ጦሩ አዛዥ ትዕዛዝ ገቢ የተደረገው መሳሪያ በከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የገለጸው ሻለቃ አምሳሉ፤ ሰራዊቱም ያልጠበቀው ክህደት ሲያጋጥመው ወደ መሳሪያ ግምጃ ቤት ቢያቀናም በታጣቂዎቹ ተኩስ እንደተከፈተበትና ግድያ እንደተፈጸመበት ተናግሯል።
ከሃዲው የህወሓት ቡድን መሳሪያ የሚቀመጥበትን ቦታ ተቆጣጥረው ከዘረፉና መግደል የፈለጉትን ከገደሉ በኋላ የተረፈውን ሰራዊት ልብሱን አስወልቀው እርቃኑን በማድረግ ወደ አዳራሽ አስገብተው እንዳፈኗቸው ጠቁመዋል።
ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ እንደገለፁት፣ ከሀዲው ቡድን በዕለቱ ከግድያ ለተረፉት የሰራዊቱ አባላት ያቀረበው አማራጭ አብሮ ለ20 ዓመት ከኖረና ለ20 ዓመት የትግራይን ህዝብ ላገለገለ ሰራዊት የማይገባው ነበር ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ “ከእኛ ጋር ወግኑ አሊያም በህይወታችሁ ፍረዱ የሚል አማራጭ እንዳቀረቡላቸው አስታውቀዋል።
የከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በክተት በታንከኛ፣ በመድፈኛ፣ በአየር መቃወሚያና በከባድ መሳሪያ ስልጣናዎችን እየወሰዱ እንደሆነ በመረዳታቸው ይህን ተግባር አግባብ እንዳልሆነ ሰራዊቱ ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበር ያስታወሰው ሻለቃው፤ የክፈለ ጦሩ አዛዥ “ከፈለጉ ሌላም ይታጠቁ የክልሉ ሥራ ነው” በሚል ያለመቀበል ሁኔታዎች እንደነበር ገልጿል።
በተለይ የአራተኛ ሜካናይዝ ክፍለ ጦር ኃላፊ ከሰራዊቱ በተቃራኒ የመቆምና ሃሳብን ያለመቀበል፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ሥሩ የሚል ትዕዛዛት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሷል።
“የክፍለ ጦሩ አመራር ለውጡን ባለመቀበል ወደ ብሔርተኝነት አሳተሳሰብ ያዘነበለ ስለነበር ሠራዊቱን አስመትተውታል” ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ ቀን ቀን ካንገት በላይ ሲያወሩ ይውላሉ፤ ማታ መቀሌ ሄደው ሲያሴሩ እንደነበር አስታውቋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42137
“ጁንታው ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ጊዜ ለመግዛት እንደራደር ማለቱ የሚጠበቅ ነው”
- አቶ ታዬ ደንደኣ
የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ብሎም ለሌላ ጥፋት ጊዜ ለመግዛት እንደራደር የሚል አጀንዳ ይዞ መምጣቱ የሚጠበቅ እንደሆነ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አስታወቁ።
አቶ ታዬ በተለይ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መከላከያ ሠራዊት ምናልባትም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ሕዝቦች አሁን የሚፈልጉት የሕወሓት ጁንታ ስብስብ እንዲወገድ ነው ብለዋል።
ቡድኑ ላለፉት 27 ዓመታት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአልሸባብ ጋር ተዳምሮ ለቀጠናው የሰላምና መረጋጋት እጦት ምክንያት እንደነበር አመልክተው ፣ይህ ቡድን እንዲቀጥል እድል መስጠት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አለመረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና መዳከም እንዲቀጥል መፍቀድ እንደሆነም አመልክተዋል ።
ጁንታው ቡድን ያሰበው ሁሉ ከንቱ ሆኖ ሲቀርበት ስለድርድር እየጮኸ ነው ያሉት አቶ ታዬ ደንደኣ፣ የቡድኑን የእንደራደር ጩኸት በሁለት መልኩ ማየት የተሻለ ነው ብለዋል። አንደኛውና ዋናው የዚህችን አገር ሕገ መንግስት ከጣሰ፤ የዚህችን አገር ሉዓላዊነት ከደፈረ ጁንታ ቡድን ጋር በምንም አይነት መልኩ ድርድር የሚቀመጥ አካል ሊኖር አይችልም።
ድርድር ሲታሰብ መጀመሪያ ከሕግ በታች በተለይም ከሕገ መንግስት በታች ባለው ነገር ላይ መሆን አለበት። መከላከያን ያጠቃ፤ የዚህችን አገር የሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን፣ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ነጻነትና ክብር የሚንጸባረቅበት ተቋምን ለማፍረስ ይሄን አይነት ተንኮል የሸረበ ሴረኛ ጋር በፍጹም ድርድር አያስፈልግም ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42094
- አቶ ታዬ ደንደኣ
የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ብሎም ለሌላ ጥፋት ጊዜ ለመግዛት እንደራደር የሚል አጀንዳ ይዞ መምጣቱ የሚጠበቅ እንደሆነ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አስታወቁ።
አቶ ታዬ በተለይ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መከላከያ ሠራዊት ምናልባትም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ሕዝቦች አሁን የሚፈልጉት የሕወሓት ጁንታ ስብስብ እንዲወገድ ነው ብለዋል።
ቡድኑ ላለፉት 27 ዓመታት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአልሸባብ ጋር ተዳምሮ ለቀጠናው የሰላምና መረጋጋት እጦት ምክንያት እንደነበር አመልክተው ፣ይህ ቡድን እንዲቀጥል እድል መስጠት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አለመረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና መዳከም እንዲቀጥል መፍቀድ እንደሆነም አመልክተዋል ።
ጁንታው ቡድን ያሰበው ሁሉ ከንቱ ሆኖ ሲቀርበት ስለድርድር እየጮኸ ነው ያሉት አቶ ታዬ ደንደኣ፣ የቡድኑን የእንደራደር ጩኸት በሁለት መልኩ ማየት የተሻለ ነው ብለዋል። አንደኛውና ዋናው የዚህችን አገር ሕገ መንግስት ከጣሰ፤ የዚህችን አገር ሉዓላዊነት ከደፈረ ጁንታ ቡድን ጋር በምንም አይነት መልኩ ድርድር የሚቀመጥ አካል ሊኖር አይችልም።
ድርድር ሲታሰብ መጀመሪያ ከሕግ በታች በተለይም ከሕገ መንግስት በታች ባለው ነገር ላይ መሆን አለበት። መከላከያን ያጠቃ፤ የዚህችን አገር የሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን፣ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ነጻነትና ክብር የሚንጸባረቅበት ተቋምን ለማፍረስ ይሄን አይነት ተንኮል የሸረበ ሴረኛ ጋር በፍጹም ድርድር አያስፈልግም ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42094
‹‹ጁንታው የህወሓት ቡድን የፈጸመው ተግባር የውጭ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ነው›› - አርቲስት ደበበ እሸቱ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው የህወሓት ቡድን በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የክህደት ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም የሀገሪቱን ህዝቦች ለማንበርከክ የሞከሩ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ተግባር መሆኑን አርቲስት ደበበ እሸቱ አስታወቀ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ ጁንታው የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ትቃት አስመልክቶ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቀው ፤ ከሃዲው ቡድን ለ21 ዓመታት ክልሉንና ህዝቡን ሲጠብቅ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመው ጥቃት የከሃዲነት ተግባር ከመሆኑም ባሻገር ትውልድም ይቅር የማይለው ነው።
‹‹ተስፋ የቆረጠ ሰው ብዙ ነገር ያደርጋል። ተስፋ ባይቆርጥ ኖሮ፣ አብሮት ሲሰራና አብሮት ሲበላ የቆየ ወንድሙን አይገድልም ነበር። መከላከያ ሠራዊቱ ከኋላዬም ከፊቴም ያለው የራሴው ወገን ነው ብሎ ወገኑን ተማምኖ በተኛበት በሌሊት ክህደት መፈጸሙ ቡድኑ የመጨረሻ ዘመኑ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ።
“አርቲስት ደበበ እንደሚለው፤ የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የፈፀመው ክህደትና ጭካኔ የውጭ አገር ጠላትና ወራሪ እንኳን ያላደረገው ነው። ጣሊያን አላደረገውም፣ ደርቡሾች አላደረጉትም፣ እንግሊዞች ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስን ለመያዝ በመጡበት ጊዜ እንዲህ አይነት አፀያፊ ድርጊት አልፈጸሙም። የራሳችን ወገን የተባለው ግን እንዲህ አይነት ዘግናኝ ድርጊት ፈጸመ። የሠራዊቱ አባላት ሲወጣ ‹‹ለማን ጥላችሁን ነው የምትሄዱ፣ እባካችሁ ቆዩልን›› ያለ አካል ይሄን ክህደት መፈጸሙ የግድያ ቀን እያመቻቸ ነበር ማለት ነው።
ሠራዊቱ ይህ ክህደት እንደሚፈጸምበት ቢያውቅ ጥሪውን ሳይቀበል ይወጣ ነበር። የወገን ጥሪ ሆኖበት ግን ቆይልኝ ሲባል እዚያው ቆየ። ወገን በወገኑ ላይ እንዲህ ሲጨክን ቅስም ይሰብራል።ኢትዮጵያዊ መሆኑንም እንድንጠራጠር አድርጎናል ብሏል።
‹‹እንዲህ አይነት የአውሬነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች ነበሩ ለካ ሲመሩን የቆዩት›› ያለው አርቲስት ደበበ፤ እነዚህ ሰዎች የፈጸሙት አጸያፊ ተግባርም መላውን ኢትዮጵያዊ ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑንም ጠቁሟል።
እንደ አርቲስት ደበበ አስተያየት፤ ጁንታው የህወሓት ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት ለጥፋት የሚሆኑትን ገንዘብና ሌሎች ነገሮችን ቢያከማችም ሊያዛልቀው ግን አይችልም። አቅም ይሳነዋል። አሁን ላይ ማድረግ የሚችለው የመሰረተ ልማት ውጤቶችን ማውደም ብቻ ነው። ከአዲስ አበባ ጋር ግንኙነቱ ስለተቋረጠ የገንዘብ ምንጩም ይደርቃል። እስከ አሁን ግን ከዚህ በፊት በሰበሰበው ገንዘብ አፈ ቀላጢዎችን ቀጥሮ በውጭ መገናኛ ብዙኃን ብዙ እያስወራ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=42138
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው የህወሓት ቡድን በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የክህደት ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም የሀገሪቱን ህዝቦች ለማንበርከክ የሞከሩ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ተግባር መሆኑን አርቲስት ደበበ እሸቱ አስታወቀ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ ጁንታው የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ትቃት አስመልክቶ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቀው ፤ ከሃዲው ቡድን ለ21 ዓመታት ክልሉንና ህዝቡን ሲጠብቅ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመው ጥቃት የከሃዲነት ተግባር ከመሆኑም ባሻገር ትውልድም ይቅር የማይለው ነው።
‹‹ተስፋ የቆረጠ ሰው ብዙ ነገር ያደርጋል። ተስፋ ባይቆርጥ ኖሮ፣ አብሮት ሲሰራና አብሮት ሲበላ የቆየ ወንድሙን አይገድልም ነበር። መከላከያ ሠራዊቱ ከኋላዬም ከፊቴም ያለው የራሴው ወገን ነው ብሎ ወገኑን ተማምኖ በተኛበት በሌሊት ክህደት መፈጸሙ ቡድኑ የመጨረሻ ዘመኑ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ።
“አርቲስት ደበበ እንደሚለው፤ የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የፈፀመው ክህደትና ጭካኔ የውጭ አገር ጠላትና ወራሪ እንኳን ያላደረገው ነው። ጣሊያን አላደረገውም፣ ደርቡሾች አላደረጉትም፣ እንግሊዞች ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስን ለመያዝ በመጡበት ጊዜ እንዲህ አይነት አፀያፊ ድርጊት አልፈጸሙም። የራሳችን ወገን የተባለው ግን እንዲህ አይነት ዘግናኝ ድርጊት ፈጸመ። የሠራዊቱ አባላት ሲወጣ ‹‹ለማን ጥላችሁን ነው የምትሄዱ፣ እባካችሁ ቆዩልን›› ያለ አካል ይሄን ክህደት መፈጸሙ የግድያ ቀን እያመቻቸ ነበር ማለት ነው።
ሠራዊቱ ይህ ክህደት እንደሚፈጸምበት ቢያውቅ ጥሪውን ሳይቀበል ይወጣ ነበር። የወገን ጥሪ ሆኖበት ግን ቆይልኝ ሲባል እዚያው ቆየ። ወገን በወገኑ ላይ እንዲህ ሲጨክን ቅስም ይሰብራል።ኢትዮጵያዊ መሆኑንም እንድንጠራጠር አድርጎናል ብሏል።
‹‹እንዲህ አይነት የአውሬነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች ነበሩ ለካ ሲመሩን የቆዩት›› ያለው አርቲስት ደበበ፤ እነዚህ ሰዎች የፈጸሙት አጸያፊ ተግባርም መላውን ኢትዮጵያዊ ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑንም ጠቁሟል።
እንደ አርቲስት ደበበ አስተያየት፤ ጁንታው የህወሓት ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት ለጥፋት የሚሆኑትን ገንዘብና ሌሎች ነገሮችን ቢያከማችም ሊያዛልቀው ግን አይችልም። አቅም ይሳነዋል። አሁን ላይ ማድረግ የሚችለው የመሰረተ ልማት ውጤቶችን ማውደም ብቻ ነው። ከአዲስ አበባ ጋር ግንኙነቱ ስለተቋረጠ የገንዘብ ምንጩም ይደርቃል። እስከ አሁን ግን ከዚህ በፊት በሰበሰበው ገንዘብ አፈ ቀላጢዎችን ቀጥሮ በውጭ መገናኛ ብዙኃን ብዙ እያስወራ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=42138
ኦነግ ሸኔ እየተሽመደመደ መምጣቱ ተገለጸ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው የህወሓት ቡድን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ የሚደረግለትና ህዝብን በማሸበር ላይ በሚገኘው የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በቡድኑ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገለጸ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ እንደገለፁት፤ጁንታው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ የኦሮሚያ ክልልን ፀጥታ ለማደፍረስ በተናበበ መንገድ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡
በዚህ እኩይ ተግባራቸው ክልሉን እየበጠበጡት ዜጎችን ሲያፈናቅሉ መቆየታቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ የክልሉ መንግሥት ህግን ለማስከበር በጀመረው እርምጃ የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ቡድኑ ህዝቡን ከማስፈራራትና አልፎ አልፎ በአንዳንድ አካባቢዎች ድንገተኛ ጥቃት ከማድረስ በዘለለ እንደፈለገው መፈንጨት ከማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል ።
የኦነግ ሸኔ አሸባሪዎች እኩይ ሴራቸውን ለመከወን ህዝብ ውስጥ የተደበቁ መሆናቸውን አመልክተው፣ ህዝቡን በእምነትና በብሄር ለማጋጨት የወጠኑት ሥራ ሰፊ ቢሆንም በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉ የተቀናጀ ሥራ መክሸፉን አስታውቀዋል።
ቡድኑን በተለይም ከኦሮሚያ ክልል ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት በሰፊው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ፣ለዚህም በአሁኑ ወቅትም ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ስለ ቡድኑ እኩይ ተግባር ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራሉ ፣የኦነግ ሸኔ አባላትም ባገኙት አጋጣሚ ዘረፋ እያካሄዱ ሃብት ለማካበት እየሞከሩ ነው፡፡ ይሁንና የክልሉን የሚሊሻ ኃይል በማጠናከር እና ከህብረተሰቡ ጋር በተናበበ መንገድ በመስራት ዘራፊውን ቡድን የማጋለጥ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=42139
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው የህወሓት ቡድን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ የሚደረግለትና ህዝብን በማሸበር ላይ በሚገኘው የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በቡድኑ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገለጸ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ እንደገለፁት፤ጁንታው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ የኦሮሚያ ክልልን ፀጥታ ለማደፍረስ በተናበበ መንገድ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡
በዚህ እኩይ ተግባራቸው ክልሉን እየበጠበጡት ዜጎችን ሲያፈናቅሉ መቆየታቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ የክልሉ መንግሥት ህግን ለማስከበር በጀመረው እርምጃ የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ቡድኑ ህዝቡን ከማስፈራራትና አልፎ አልፎ በአንዳንድ አካባቢዎች ድንገተኛ ጥቃት ከማድረስ በዘለለ እንደፈለገው መፈንጨት ከማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል ።
የኦነግ ሸኔ አሸባሪዎች እኩይ ሴራቸውን ለመከወን ህዝብ ውስጥ የተደበቁ መሆናቸውን አመልክተው፣ ህዝቡን በእምነትና በብሄር ለማጋጨት የወጠኑት ሥራ ሰፊ ቢሆንም በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉ የተቀናጀ ሥራ መክሸፉን አስታውቀዋል።
ቡድኑን በተለይም ከኦሮሚያ ክልል ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት በሰፊው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ፣ለዚህም በአሁኑ ወቅትም ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ስለ ቡድኑ እኩይ ተግባር ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራሉ ፣የኦነግ ሸኔ አባላትም ባገኙት አጋጣሚ ዘረፋ እያካሄዱ ሃብት ለማካበት እየሞከሩ ነው፡፡ ይሁንና የክልሉን የሚሊሻ ኃይል በማጠናከር እና ከህብረተሰቡ ጋር በተናበበ መንገድ በመስራት ዘራፊውን ቡድን የማጋለጥ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=42139
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል እየተወሰደ ያለው ህግን የማስከበር እርምጃ እንደሚደግፍ ኢዜማ አስታወቀ
*********************
(ኢ ፐ ድ)
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ የሚደገፍ መሆኑንኢዜማ አስታወቀ ። ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ እኩይ መልእክቶችን በመመልከት የትግራይ ተወላጅ ወንድሞቻችን ከመሸማቀቅ ይልቅ አብሮ በመቆም ቀኑን ማሳለፍ እንደሚገባ ገለጸ ።
ኃላፊው አቶ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት ፣ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጋር በተያያዘ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውን የትግራይን ህዝበ ለመጠበቅ ኑሮውን እዛ ያደረገ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀም ከክህደት ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም ።
ከህዝቡ ጋር በሰላም የኖረ የህዝብ ልጅ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊትን ማጥቃት ተገቢ አለመሆኑን ያመለከቱት አቶ ዘላለም፣ ኢዜማ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የህግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት ያሳየው ትእግስት ጦርነት የሚያስከ ትለውን ጉዳት በማሰብ ቢሆንም የአንድነት፣ የሉአላዊነት እና የህልውና ምልክት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝም ማለት አለበት ብሎ ኢዜማ አያምንም ብለዋል። ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለውን እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል።
“የትግራይ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው፤ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በሰላም መኖር የሚያውቅበት፤ የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ የአስተዳደር ስርአት የሚያውቅ ህዝብ ነው” ያሉት አቶ ዘላለም “ ጦርነቱ የሚያመጣውን ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ጫና ለመቅረፍ መልሶ የማቋቋም ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በፈጸመው ጥፋት በሱላይ ሊመጣ የሚችል አደጋ ባለመኖሩ ሊሰጋ እንደማይገባ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42148
*********************
(ኢ ፐ ድ)
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ የሚደገፍ መሆኑንኢዜማ አስታወቀ ። ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ እኩይ መልእክቶችን በመመልከት የትግራይ ተወላጅ ወንድሞቻችን ከመሸማቀቅ ይልቅ አብሮ በመቆም ቀኑን ማሳለፍ እንደሚገባ ገለጸ ።
ኃላፊው አቶ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት ፣ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጋር በተያያዘ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውን የትግራይን ህዝበ ለመጠበቅ ኑሮውን እዛ ያደረገ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀም ከክህደት ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም ።
ከህዝቡ ጋር በሰላም የኖረ የህዝብ ልጅ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊትን ማጥቃት ተገቢ አለመሆኑን ያመለከቱት አቶ ዘላለም፣ ኢዜማ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የህግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት ያሳየው ትእግስት ጦርነት የሚያስከ ትለውን ጉዳት በማሰብ ቢሆንም የአንድነት፣ የሉአላዊነት እና የህልውና ምልክት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝም ማለት አለበት ብሎ ኢዜማ አያምንም ብለዋል። ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለውን እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል።
“የትግራይ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው፤ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በሰላም መኖር የሚያውቅበት፤ የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ የአስተዳደር ስርአት የሚያውቅ ህዝብ ነው” ያሉት አቶ ዘላለም “ ጦርነቱ የሚያመጣውን ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ጫና ለመቅረፍ መልሶ የማቋቋም ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በፈጸመው ጥፋት በሱላይ ሊመጣ የሚችል አደጋ ባለመኖሩ ሊሰጋ እንደማይገባ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42148
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ልዑካን አማካኝነት ከህወሓት ቡድን ጋር ድርድር ሊያደረጉ ነዉ የሚለው መረጃ ሐሰተኛ ነዉ::
************
(ኢፕድ)
የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ላይ እንደተጠቀሰው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሲሪል ራማፎሳ ልዑካኖችን በመቀበል ታነጋገራለች:: ይህ የልዑካን ቡድኑን መቀበል እና የማነጋገር ሂደት በየተናጠል ከልዑካን ቡድኑ አባላት ጋር ብቻ የሚካሄድ ነዉ::
መልእክተኞቹ የፌዴራል መንግስትን ክህወሓት ጁንታ ጋር ለማስታረቅ ወደ ኢትዮጵያ ይግዋዛሉ በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰተኛ ነዉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ ማስከበር ርምጃው ላይ ድርድር የማይታሰብ መሆኑን ግልፅ ማደረጋቸውም ይታወሳል::
************
(ኢፕድ)
የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ላይ እንደተጠቀሰው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሲሪል ራማፎሳ ልዑካኖችን በመቀበል ታነጋገራለች:: ይህ የልዑካን ቡድኑን መቀበል እና የማነጋገር ሂደት በየተናጠል ከልዑካን ቡድኑ አባላት ጋር ብቻ የሚካሄድ ነዉ::
መልእክተኞቹ የፌዴራል መንግስትን ክህወሓት ጁንታ ጋር ለማስታረቅ ወደ ኢትዮጵያ ይግዋዛሉ በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰተኛ ነዉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ ማስከበር ርምጃው ላይ ድርድር የማይታሰብ መሆኑን ግልፅ ማደረጋቸውም ይታወሳል::
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደነበረ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ
******************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እንደነበረና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደሆነ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ።
የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ኢትዮጵያ ለገባችበት ችግር ዘራፊው ህወሓት እና የእሱ ወዳጆች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ላይ ራሳቸው የበላይ በማድረጋቸው እና በአገሪቱም “ሀሰተኛ” የፌዴራል ስርዓት በመመስረታቸው ነው ብለዋል።
በ 1991 በጎሳዎች ላይ የተመሠረተ የክልሎች ስርዓት በኢትዮጵያ የተቋቋመ ቢሆንም ስርዓቱ የውሸት በመሆኑ ከትግራይ ውጪ ያሉ ክልሎች አንዳቸውም ቢሆኑ በአገሪቱ ላይ የመወሰን መብት አልነበራቸውም ያሉት ኸርማን ኮኸን፤ ሂደቱ የአንድ ፓርቲ የበላይነትን ያነገሰበት ከበርካታ ዓመታት በፊት በአፍሪካ ተሞክሮ የወደቀ አካሄድን የተከተለ ነው ብለዋል።
ጥቂት የህወሓት አባላት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ብቻቸውን በበላይነት በመቆጣጠራቸው ምክንያት ጥቅማ ጥቅሞችን ለእነርሱና እነርሱን ለሚመስሏቸው ብቻ ሲያደርጉ መኖራቸውን የጠቀሱት ኸርማን ኮኸን ፤ በዚህም ምክንያት ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጫና ተፈጥሮባቸዋል፤ የመሰረተ ልማትም ፍትሃዊነት በጎደለው መልኩ ለራሳቸው አድርገውታል፤ ይህ አይነት አካሄድ በሌሎች ላይ ቁጭትና ጫና ፈጥሮባቸዋል ብለዋል አምባሳደሩ።
ይሄንን አይነት በደለን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነትን ተቃውመው ሰልፍ በሚወጡ ባልታጠቁ ሰልፈኞች ላይ የህወሃት ኃይል የሚወስዳቸው እርምጃዎችም ያልተመጣጠነ እንደነበር ኸርማን ኮኸን አብራርተዋል።
ይህን ሁሉ የሰብጻዊ መብት ጥሰት ይፈጽም ለነበረ አካል አሜሪካ ለምንድን ነበር የምትደግፈው ተብለው የተጠየቁት አምባሳደሩ፤ “ ስትራቴጂካዊ ፍላጎታችንን ለማሟላት ስንል ይህን ታግሰናል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
******************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እንደነበረና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደሆነ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ።
የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ኢትዮጵያ ለገባችበት ችግር ዘራፊው ህወሓት እና የእሱ ወዳጆች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ላይ ራሳቸው የበላይ በማድረጋቸው እና በአገሪቱም “ሀሰተኛ” የፌዴራል ስርዓት በመመስረታቸው ነው ብለዋል።
በ 1991 በጎሳዎች ላይ የተመሠረተ የክልሎች ስርዓት በኢትዮጵያ የተቋቋመ ቢሆንም ስርዓቱ የውሸት በመሆኑ ከትግራይ ውጪ ያሉ ክልሎች አንዳቸውም ቢሆኑ በአገሪቱ ላይ የመወሰን መብት አልነበራቸውም ያሉት ኸርማን ኮኸን፤ ሂደቱ የአንድ ፓርቲ የበላይነትን ያነገሰበት ከበርካታ ዓመታት በፊት በአፍሪካ ተሞክሮ የወደቀ አካሄድን የተከተለ ነው ብለዋል።
ጥቂት የህወሓት አባላት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ብቻቸውን በበላይነት በመቆጣጠራቸው ምክንያት ጥቅማ ጥቅሞችን ለእነርሱና እነርሱን ለሚመስሏቸው ብቻ ሲያደርጉ መኖራቸውን የጠቀሱት ኸርማን ኮኸን ፤ በዚህም ምክንያት ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጫና ተፈጥሮባቸዋል፤ የመሰረተ ልማትም ፍትሃዊነት በጎደለው መልኩ ለራሳቸው አድርገውታል፤ ይህ አይነት አካሄድ በሌሎች ላይ ቁጭትና ጫና ፈጥሮባቸዋል ብለዋል አምባሳደሩ።
ይሄንን አይነት በደለን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነትን ተቃውመው ሰልፍ በሚወጡ ባልታጠቁ ሰልፈኞች ላይ የህወሃት ኃይል የሚወስዳቸው እርምጃዎችም ያልተመጣጠነ እንደነበር ኸርማን ኮኸን አብራርተዋል።
ይህን ሁሉ የሰብጻዊ መብት ጥሰት ይፈጽም ለነበረ አካል አሜሪካ ለምንድን ነበር የምትደግፈው ተብለው የተጠየቁት አምባሳደሩ፤ “ ስትራቴጂካዊ ፍላጎታችንን ለማሟላት ስንል ይህን ታግሰናል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬ ከተማ ከገባ በኋላ ከችግርና ውጥረት ታድጎናል- የሽሬ ከተማ ነዋሪዎች
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣ አድርጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የህወሃት ቡድን ቀደም ሲል በክልሉ "ወራሪ፣ ዘራፊና የትግራይን ህዝብ የሚያጠፋ ሃይል እየመጣ ነው" በሚል ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጭ ነበር ይላሉ ነዋሪዎቹ።
በዚህም በርካቶች ፍርሃት አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ግን እውነታውን ተረድተነዋል ብለዋል።
ሰራዊቱ ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ብዙዎቻችን ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ወጥተን ወደ ሰላማዊ ህይወት ገብተናል ነው ያሉት።
ህወሃት ሲያሰራጨው በነበረው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ፍራቻ አድሮብን የነበረ ቢሆንም፤ ሰራዊቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር ህዝባዊነቱንና አብሮነቱን አሳይቶናል ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂ ቡድን ከሽሬ በመውጣቱ ከተማዋ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷንና የተለያዩ አገልግሎቶችም መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት በሽሬ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የከተማዋን ነዋሪዎችን ሰብስቦ በማናገሩም ተደስተናል ብለዋል።
ሰራዊቱ ክልሉን ከዘራፊዎችና ግለኞች ነፃ በማውጣት የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የመጣ መሆኑንም ተረድተናል ነው ያሉት።
በህወሃት ካድሬዎች ፕሮፓጋንዳ ከአካባቢው ርቀው የነበሩ የከተማዋ ነዋሪዎችም ሰላም መሆኑን በመረዳት ወደ ቤታቸው እየተመለሱ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝቡ ንብረት በዘራፊዎች አንዳይወሰድ የአገር መከላከያ ሰራዊት የተቆጣጠረባቸው አካባቢዎች ላይ ጥብቅ ጥበቃና ክትትል በማድረጉም ተደስተናል ብለዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ተላቀናል በቀጣይ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ሰላማችንን እናስጠብቃለን ሲሉም ነው የተናገሩት።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች አሁን ላይ ለሰራዊቱ መረጃ በመስጠትና የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ፍቅሩን አሳይቶናል፣ አረጋግቶናል፣ ህወሃት ከፈጠረብን ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣም አድርጎናል በማለት ገልጸዋል።
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣ አድርጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የህወሃት ቡድን ቀደም ሲል በክልሉ "ወራሪ፣ ዘራፊና የትግራይን ህዝብ የሚያጠፋ ሃይል እየመጣ ነው" በሚል ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጭ ነበር ይላሉ ነዋሪዎቹ።
በዚህም በርካቶች ፍርሃት አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ግን እውነታውን ተረድተነዋል ብለዋል።
ሰራዊቱ ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ብዙዎቻችን ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ወጥተን ወደ ሰላማዊ ህይወት ገብተናል ነው ያሉት።
ህወሃት ሲያሰራጨው በነበረው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ፍራቻ አድሮብን የነበረ ቢሆንም፤ ሰራዊቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር ህዝባዊነቱንና አብሮነቱን አሳይቶናል ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂ ቡድን ከሽሬ በመውጣቱ ከተማዋ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷንና የተለያዩ አገልግሎቶችም መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት በሽሬ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የከተማዋን ነዋሪዎችን ሰብስቦ በማናገሩም ተደስተናል ብለዋል።
ሰራዊቱ ክልሉን ከዘራፊዎችና ግለኞች ነፃ በማውጣት የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የመጣ መሆኑንም ተረድተናል ነው ያሉት።
በህወሃት ካድሬዎች ፕሮፓጋንዳ ከአካባቢው ርቀው የነበሩ የከተማዋ ነዋሪዎችም ሰላም መሆኑን በመረዳት ወደ ቤታቸው እየተመለሱ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝቡ ንብረት በዘራፊዎች አንዳይወሰድ የአገር መከላከያ ሰራዊት የተቆጣጠረባቸው አካባቢዎች ላይ ጥብቅ ጥበቃና ክትትል በማድረጉም ተደስተናል ብለዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ተላቀናል በቀጣይ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ሰላማችንን እናስጠብቃለን ሲሉም ነው የተናገሩት።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች አሁን ላይ ለሰራዊቱ መረጃ በመስጠትና የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ፍቅሩን አሳይቶናል፣ አረጋግቶናል፣ ህወሃት ከፈጠረብን ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣም አድርጎናል በማለት ገልጸዋል።
የህወሃት ጁንታ አክሱም ኤርፖርትን በ26 የተለያዩ አካባቢዎች በግሬደር አርሶታል
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የህወሃት የጥፋት ቡድን አክሱም ኤርፖርትን በ26 የተለያዩ አካባቢዎች በግሬደር እንዳረሰው የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ተናገሩ።
ቡድኑ በአገር መከላከያ ሰራዊት እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ በአካባቢው ላይ የከፋ ጉዳት ያስከትል እንደነበርም ታውቋል።
የህወሃት ጁንታ አሁን ላይ ተስፋ እየቆረጠ በመምጣቱ በተለይ የህዝብ መገልገያ መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጥፋት እየፈፀመ ይገኛል።
የጥፋት ቡድኑ የአክሱም ኤርፖርትን ከ23 አስከ 26 የተለያዩ አካባቢዎች በግሬደር በማረስ የህዝቡ ጠላት መሆኑን ማሳየቱን ከሰራዊቱ አመራሮች መካከል ሻምበል አብይ ሩፋኤል ገልጸውልናል።
ጁንታው በሰራዊቱ አፋጣኝ አርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ ኤርፖርቱን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም ቅርሶችን ሙሉ ለሙሉ የማውደም እቅድ ነበረውም ብለዋል።
የህወሃት ፅንፈኛ ሃይል በፊትም ለጥፋት የቆመ ሃይል ነው ያሉት ሻምበል አብይ፤ አሁን ደግሞ በይፋ የህዝብ ጠላትነቱን አሳይቷል ብለዋል።
በአክሱም ኤርፖርት የፈፀመውም የአውሮፕላን መንደርደሪያውን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመቆፈር ጉዳት አድርሷል።
በኤርፖርቱ ህንፃ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ንብረቶችንና ቅርሶችንም መዝረፉን ገልጸው፤ በሰራዊቱ ፈጣን እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ አካባቢው ላይ ተጨማሪ ጥፋት ያደርስ ነበር ብለዋል።
የህወሃት ጁንታ እየፈፀመው ያለው ተግባር የህዝብ ግልፅ ጠላት መሆኑን በአደባባይ ያረጋገጠ መሆኑን ሌላው የሰራዊቱ አመራር ሌተናል ኮሎኔል ወልዴ ሃይሌ ገልጸውልናል።
የጥፋት ቡድኑ በአገር መከላከያ ሰራዊት ፈጣን እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ በአካባቢው ላይ ሌላም የከፋ ጉዳት ያስከትል ነበር ያሉት ደግሞ ሻምበል ባሻ ሙላት ናቸው ።
የህወሃት ጁንታ የተለያዩ የእምነት ተቋማትን እንደ መደበቂያ በመጠቀም ጉዳት እንዲደርስባቸው ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሌተናል ኮሎኔል ተመስገን ነጋ እንዳሉትም የህወሃት ታጣቂ ሃይል በተለይም ቤተክረስቲያናትን፣ መስጅዶችና ቅርሶች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች በምሽግነት እየተጠቀማቸው ይገኛል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት ግን እስካሁን ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የኦፕሬሽን ስራውን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የትግራይ ህዝብ የህወሃት ፅንፈኛ ቡድን እኩይ አላማ እና የጥፋት ተልእኮ ተረድቷል ያሉት አመራሮቹ፤ ለአገር መከላከያ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።
ህወሃት ለህዝብ የማያስብ፣ ሴረኛ፣ አጥፊና ለራሱ ህልውና ብቻ የሚያስብ የጥፋት ስብስብ መሆኑን የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ በአግባቡ ተገንዝቦታልም ብለዋል።
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የህወሃት የጥፋት ቡድን አክሱም ኤርፖርትን በ26 የተለያዩ አካባቢዎች በግሬደር እንዳረሰው የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ተናገሩ።
ቡድኑ በአገር መከላከያ ሰራዊት እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ በአካባቢው ላይ የከፋ ጉዳት ያስከትል እንደነበርም ታውቋል።
የህወሃት ጁንታ አሁን ላይ ተስፋ እየቆረጠ በመምጣቱ በተለይ የህዝብ መገልገያ መሰረተ ልማቶች ላይ ከፍተኛ ጥፋት እየፈፀመ ይገኛል።
የጥፋት ቡድኑ የአክሱም ኤርፖርትን ከ23 አስከ 26 የተለያዩ አካባቢዎች በግሬደር በማረስ የህዝቡ ጠላት መሆኑን ማሳየቱን ከሰራዊቱ አመራሮች መካከል ሻምበል አብይ ሩፋኤል ገልጸውልናል።
ጁንታው በሰራዊቱ አፋጣኝ አርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ ኤርፖርቱን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችን እንዲሁም ቅርሶችን ሙሉ ለሙሉ የማውደም እቅድ ነበረውም ብለዋል።
የህወሃት ፅንፈኛ ሃይል በፊትም ለጥፋት የቆመ ሃይል ነው ያሉት ሻምበል አብይ፤ አሁን ደግሞ በይፋ የህዝብ ጠላትነቱን አሳይቷል ብለዋል።
በአክሱም ኤርፖርት የፈፀመውም የአውሮፕላን መንደርደሪያውን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመቆፈር ጉዳት አድርሷል።
በኤርፖርቱ ህንፃ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ንብረቶችንና ቅርሶችንም መዝረፉን ገልጸው፤ በሰራዊቱ ፈጣን እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ አካባቢው ላይ ተጨማሪ ጥፋት ያደርስ ነበር ብለዋል።
የህወሃት ጁንታ እየፈፀመው ያለው ተግባር የህዝብ ግልፅ ጠላት መሆኑን በአደባባይ ያረጋገጠ መሆኑን ሌላው የሰራዊቱ አመራር ሌተናል ኮሎኔል ወልዴ ሃይሌ ገልጸውልናል።
የጥፋት ቡድኑ በአገር መከላከያ ሰራዊት ፈጣን እርምጃ ባይወሰድበት ኖሮ በአካባቢው ላይ ሌላም የከፋ ጉዳት ያስከትል ነበር ያሉት ደግሞ ሻምበል ባሻ ሙላት ናቸው ።
የህወሃት ጁንታ የተለያዩ የእምነት ተቋማትን እንደ መደበቂያ በመጠቀም ጉዳት እንዲደርስባቸው ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሌተናል ኮሎኔል ተመስገን ነጋ እንዳሉትም የህወሃት ታጣቂ ሃይል በተለይም ቤተክረስቲያናትን፣ መስጅዶችና ቅርሶች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች በምሽግነት እየተጠቀማቸው ይገኛል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአገር መከላከያ ሰራዊት ግን እስካሁን ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የኦፕሬሽን ስራውን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የትግራይ ህዝብ የህወሃት ፅንፈኛ ቡድን እኩይ አላማ እና የጥፋት ተልእኮ ተረድቷል ያሉት አመራሮቹ፤ ለአገር መከላከያ ድጋፍና እገዛ እያደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።
ህወሃት ለህዝብ የማያስብ፣ ሴረኛ፣ አጥፊና ለራሱ ህልውና ብቻ የሚያስብ የጥፋት ስብስብ መሆኑን የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ በአግባቡ ተገንዝቦታልም ብለዋል።
“የህወሓት ጁንታ አዲስ አበባ ውስጥ ከ600 ሺ እስከ አምስት ሚሊዮን ብር የሚከራይ ህንጻ ያላቸው ጄኔራሎችን ፈጥሯል”
– አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ረዳ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
መሰሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ሆነ ፖለቲካ በቤተሰብ ኔትዎርክ በመያዝ አገሪቷን ሲዘርፍ መኖሩን የትግራይ ክልል የሽግግር ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት እና የድርጅት ንቅናቄ ዘርፍ አባል አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ቡድን ሲፈጠር ጀምሮ ከአንድ ቤተሰብ (ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አከባቢ) የወጣ መሆኑንም አመለከቱ።
አቶ ሊላይ ኃይለማርያም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ እንዳመለከቱት፣ መሰሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን ሲፈጠር ጀምሮ ከአንድ ቤተሰብ (ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አካባቢ) የወጣ ነው ። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚም ሆነ ፖለቲካ በዚህ የቤተሰብ ኔትዎርክ በመያዝ አገሪቷን ሲዘርፍ ኖሯል። በዚህም በቤተሰብና በአካባቢ ተደራጅቶ ለ27 ዓመታት የኢትዮጵያን ሀብት ሲዘርፍ የቆየው የህወሓት ጁንታ ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከ600 ሺ እስከ አምስት ሚሊዮን ብር የሚከራይ ህንጻ ያላቸው ጄኔራሎችንም ፈጥሯል።
“ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አካባቢ የወጣው ይህ መሰሪ ቡድን ስልጣኑንም ኢኮኖሚውንም ለመቆጣጠር እንዲመቸው ሲል ከቤተ መንግስት እስከ ቤተ ክህነት ያለውን መዋቅር ሁሉ ተቆጣጥሯል። ለዚህ ደግሞ ስብሃት ነጋ መጀመሪያ አዲስ አበባ እንደገባ እና ስልጣን እንደያዘ አቡነ ጳውሎስን ከአሜሪካ አስመጥቶ ቤተ ክህነቱን አስያዘ። አቡነ ጳውሎስ ማለት ደግሞ የእነሱ ቤተሰብ ናቸው። አራት ኪሎ ቤተ መንግስቱን በመለስ አስያዙ፤ የመቀሌውን ቤተ መንግስት ደግሞ በቅዱሳን ነጋ ባል በአለቃ ፀጋዬ ነው የያዙት። እንዲህ አድርገው ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግስት ከተቆጣጠሩ በኋላ፤ ሁሉንም ነገር በኔትዎርክና በቤተብ ወደሚሰራ ሥርዓት አስገቡት” ብለዋል ።
ለምሳሌ፣ ቤተ ክህነት አንድ ህንጻ ቤተክርስቲያን ለማሳደስ ጨረታ ያወጣል። እናም አቡነ ጳውሎስ ያለምንም ጨረታ በአምስት ሚሊዮን ብር ጨረታውን ለኮሎኔል በላይ ይሰጡታል። ይሄ ሰውዬ ደግሞ ላይሰንስ የለውም፤ ኢንጂነርም አይደለም፤ ጡረታ የወጣ የደርግ ኮሎኔል እንደሆነ አመልክተዋል።
ሲኖዱሱም በአንድ ሚሊዮን የሚሰራ ስራ እንዴት በአምስት ሚሊዮን ይሰጣል በሚል ይሄንን አካሄድ ይቃወማል። የእሳቸውም ፀሃፊ የነበረውም በተመሳሳይ በመቃወሙ ጨረታው ይቆማል። ጨረታ ይውጣ ሲባል፣ 700 ሺህ፣ 800 ሺህ፣ አንድ ሚሊዮን የሚል ይወጣል። እሳቸው ደግሞ ይቆይ ብለው ያቆዩትና ከአንድ አራት ወር በኋላ በአምስት ሚሊዮን ብር ለእሱ ሰጥቼዋለሁ ብለው ያዛሉ። የዛኔም የሳቸው ፀሐፊ የነበረው በዚህ መልኩ አልሰራም ብሎ ስራውን ትቶ ወጥቷል። ከዛም በኋላ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የስብሃት ነጋ ኔትዎርክ ሰዎች ናቸው ተሰብስበው እንዲገቡ የተደረገው እና የቤተ ክህነቱ የቢዝነስ መስመር በሙሉ ለእነሱ እንዲሰጥ ተደርጎ ሚሊየነር ሆነዋል ብለዋል።
እንደ አቶ ሊላይ ማብራሪያ፤ ከዚህ በተጓዳኝ የስዩም መስፍን፣ የስብሃት ነጋ እና የሌሎቹም ዘመዶቻቸው በኤርፖርት ይግቡ በጅቡቲ የጉምሩክ ታክስ ከፍለው አያውቁም። በአዲስ አበባ ተሸንሽኖ የተወሰደው መሬት ውስጥ አንዳቸውም በሊዝ ገዝተው አያውቁም፤ በሊዝ የገዙም ካሉ በሳንቲም ቤት ነው የሚገዙት። ይሄን ደግሞ ፋይሉን ከማዘጋጃ ቤት ወይም ከተማ ልማት ሊገኝ የሚችል ነው። እናም እነዚህ ሰዎች በሁሉም መስክ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ተቆጣጥረውት ቆይተዋል። ሌላው ቀርቶ ኮትሮባንድ ንግድ ከአብዲ ኢሌ ጋር ሆነው ሲሰሩ እንደነበር አመልክተዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42253
– አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ረዳ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
መሰሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ሆነ ፖለቲካ በቤተሰብ ኔትዎርክ በመያዝ አገሪቷን ሲዘርፍ መኖሩን የትግራይ ክልል የሽግግር ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት እና የድርጅት ንቅናቄ ዘርፍ አባል አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ቡድን ሲፈጠር ጀምሮ ከአንድ ቤተሰብ (ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አከባቢ) የወጣ መሆኑንም አመለከቱ።
አቶ ሊላይ ኃይለማርያም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ እንዳመለከቱት፣ መሰሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን ሲፈጠር ጀምሮ ከአንድ ቤተሰብ (ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አካባቢ) የወጣ ነው ። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚም ሆነ ፖለቲካ በዚህ የቤተሰብ ኔትዎርክ በመያዝ አገሪቷን ሲዘርፍ ኖሯል። በዚህም በቤተሰብና በአካባቢ ተደራጅቶ ለ27 ዓመታት የኢትዮጵያን ሀብት ሲዘርፍ የቆየው የህወሓት ጁንታ ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከ600 ሺ እስከ አምስት ሚሊዮን ብር የሚከራይ ህንጻ ያላቸው ጄኔራሎችንም ፈጥሯል።
“ከስብሃት ነጋ ቤተሰብና አካባቢ የወጣው ይህ መሰሪ ቡድን ስልጣኑንም ኢኮኖሚውንም ለመቆጣጠር እንዲመቸው ሲል ከቤተ መንግስት እስከ ቤተ ክህነት ያለውን መዋቅር ሁሉ ተቆጣጥሯል። ለዚህ ደግሞ ስብሃት ነጋ መጀመሪያ አዲስ አበባ እንደገባ እና ስልጣን እንደያዘ አቡነ ጳውሎስን ከአሜሪካ አስመጥቶ ቤተ ክህነቱን አስያዘ። አቡነ ጳውሎስ ማለት ደግሞ የእነሱ ቤተሰብ ናቸው። አራት ኪሎ ቤተ መንግስቱን በመለስ አስያዙ፤ የመቀሌውን ቤተ መንግስት ደግሞ በቅዱሳን ነጋ ባል በአለቃ ፀጋዬ ነው የያዙት። እንዲህ አድርገው ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግስት ከተቆጣጠሩ በኋላ፤ ሁሉንም ነገር በኔትዎርክና በቤተብ ወደሚሰራ ሥርዓት አስገቡት” ብለዋል ።
ለምሳሌ፣ ቤተ ክህነት አንድ ህንጻ ቤተክርስቲያን ለማሳደስ ጨረታ ያወጣል። እናም አቡነ ጳውሎስ ያለምንም ጨረታ በአምስት ሚሊዮን ብር ጨረታውን ለኮሎኔል በላይ ይሰጡታል። ይሄ ሰውዬ ደግሞ ላይሰንስ የለውም፤ ኢንጂነርም አይደለም፤ ጡረታ የወጣ የደርግ ኮሎኔል እንደሆነ አመልክተዋል።
ሲኖዱሱም በአንድ ሚሊዮን የሚሰራ ስራ እንዴት በአምስት ሚሊዮን ይሰጣል በሚል ይሄንን አካሄድ ይቃወማል። የእሳቸውም ፀሃፊ የነበረውም በተመሳሳይ በመቃወሙ ጨረታው ይቆማል። ጨረታ ይውጣ ሲባል፣ 700 ሺህ፣ 800 ሺህ፣ አንድ ሚሊዮን የሚል ይወጣል። እሳቸው ደግሞ ይቆይ ብለው ያቆዩትና ከአንድ አራት ወር በኋላ በአምስት ሚሊዮን ብር ለእሱ ሰጥቼዋለሁ ብለው ያዛሉ። የዛኔም የሳቸው ፀሐፊ የነበረው በዚህ መልኩ አልሰራም ብሎ ስራውን ትቶ ወጥቷል። ከዛም በኋላ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የስብሃት ነጋ ኔትዎርክ ሰዎች ናቸው ተሰብስበው እንዲገቡ የተደረገው እና የቤተ ክህነቱ የቢዝነስ መስመር በሙሉ ለእነሱ እንዲሰጥ ተደርጎ ሚሊየነር ሆነዋል ብለዋል።
እንደ አቶ ሊላይ ማብራሪያ፤ ከዚህ በተጓዳኝ የስዩም መስፍን፣ የስብሃት ነጋ እና የሌሎቹም ዘመዶቻቸው በኤርፖርት ይግቡ በጅቡቲ የጉምሩክ ታክስ ከፍለው አያውቁም። በአዲስ አበባ ተሸንሽኖ የተወሰደው መሬት ውስጥ አንዳቸውም በሊዝ ገዝተው አያውቁም፤ በሊዝ የገዙም ካሉ በሳንቲም ቤት ነው የሚገዙት። ይሄን ደግሞ ፋይሉን ከማዘጋጃ ቤት ወይም ከተማ ልማት ሊገኝ የሚችል ነው። እናም እነዚህ ሰዎች በሁሉም መስክ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ተቆጣጥረውት ቆይተዋል። ሌላው ቀርቶ ኮትሮባንድ ንግድ ከአብዲ ኢሌ ጋር ሆነው ሲሰሩ እንደነበር አመልክተዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42253
የተሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም እጅግ በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት በየግንባሩ እጅ እየሰጡ ነው
መንግሥት የሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም እጅግ በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት በየግንባሩ እጅ እየሰጡ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ።
በአፋር ክልል በኩል ብዙዎች ገብተው እጅ የሰጡ ሲሆን በማይ ጸብሪ ተቆርጦ የቀረው ኃይል እጁን በሰላም በመስጠት ላይ መሆኑም ተገልጿል።
ጥሪውን ሰምተው እጅ በመስጠት ላይ ለሚገኙ የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ አባላት ለሕዝባቸው በማሰባቸው መንግሥት ምስጋናው አቅርቧል።
"በጁንታው ኃይል ተጽዕኖ ውስጥ ሆናችሁ እጅ ለመስጠት ያልቻላችሁ ሁሉ፣ በያላችሁበት ትጥቃችሁን ፈትታችሁና የጁንታው መጠቀሚያ ከመሆን ተቆጥባችሁ፣ መከላከያ እስከሚደርስላችሁ እንድትጠብቁ በአጽንዖት እናሳስባለን" ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት የሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም እጅግ በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት በየግንባሩ እጅ እየሰጡ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ።
በአፋር ክልል በኩል ብዙዎች ገብተው እጅ የሰጡ ሲሆን በማይ ጸብሪ ተቆርጦ የቀረው ኃይል እጁን በሰላም በመስጠት ላይ መሆኑም ተገልጿል።
ጥሪውን ሰምተው እጅ በመስጠት ላይ ለሚገኙ የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ አባላት ለሕዝባቸው በማሰባቸው መንግሥት ምስጋናው አቅርቧል።
"በጁንታው ኃይል ተጽዕኖ ውስጥ ሆናችሁ እጅ ለመስጠት ያልቻላችሁ ሁሉ፣ በያላችሁበት ትጥቃችሁን ፈትታችሁና የጁንታው መጠቀሚያ ከመሆን ተቆጥባችሁ፣ መከላከያ እስከሚደርስላችሁ እንድትጠብቁ በአጽንዖት እናሳስባለን" ጥሪ ቀርቧል።
ጉለሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች 40 የበሬ ሰንጋዎችን ጨምሮ ከ74.8 ሚሊዮን ብር በላይ የቁሳቁስና ጥሬ ገንዘብ ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አደረጉ።
የጉሌሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት በጁንታው ህወሓት የጥፋትቡድን ላይ እየወሰደ ያላውን የህግ ማስከበር እርምጃ ለመደገፍ ለሰራዊቱ የሚሆን 40 የበሬ ሰንጋዎችን ጨምሮ ከ74 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎቹ ያደረጉትን ድጋፍ የአዲስ አበባ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ ከመከላከያ ሰራዊቱ ተወክለው የተገኙት ብርጋዴል ጄነራል ደሳለኝ ደቼ አስረክበዋል፡፡
በርክክቡ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ እንደገለጹት የከተማዋ ነዋሪዎች በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተፈፀመን ጥቃት ለመመከት እየተዋጋ ላለው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆኑን ያሳየ ነው ብለዋል፡፡
ለሰራዊቱ በሁሉም ደረጃ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች እያደረጉት ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ያሉት አቶ መለሰ በስካሁኑ ድጋፉን በማስተባበር እና ድጋፍ በማድረግ ተሳትፎ ላደረጉ አካላት በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በመከላከያ ሚኒስቴር የቅርስ ጥበቃና ሙዚየም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዴል ጄነራል ደሳለኝ ደቼ በበኩላቸው፣ ህግ የማስከበር ስራዎች የህዝቡን ድጋፍ የሚሹ ናቸው፤ 100 የማይሞላውን የጥፋት ቡድን 100 ሚሊየን በላይ በሚልቅ የህዝብ ድጋፍ ድል እናደርጋለን” ብለዋል፡፡
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ አባወይ ዮሃንስ በክፍለ ከተማው የሚገኙ ነዋሪዎች፣የመንግስት ሰራተኞች ፣ባለሀብቶች፣የጤና ባለሙያዎች ፣መምህራን፣ነጋዴዎችና በተለያየ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙ ነዋሪዎች በፈቃደኝነት የለገሱት መሆኑን ገልጸዋል።
የጉሌሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት በጁንታው ህወሓት የጥፋትቡድን ላይ እየወሰደ ያላውን የህግ ማስከበር እርምጃ ለመደገፍ ለሰራዊቱ የሚሆን 40 የበሬ ሰንጋዎችን ጨምሮ ከ74 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የክፍለ ከተማው ነዋሪዎቹ ያደረጉትን ድጋፍ የአዲስ አበባ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ ከመከላከያ ሰራዊቱ ተወክለው የተገኙት ብርጋዴል ጄነራል ደሳለኝ ደቼ አስረክበዋል፡፡
በርክክቡ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ እንደገለጹት የከተማዋ ነዋሪዎች በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተፈፀመን ጥቃት ለመመከት እየተዋጋ ላለው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆኑን ያሳየ ነው ብለዋል፡፡
ለሰራዊቱ በሁሉም ደረጃ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች እያደረጉት ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ያሉት አቶ መለሰ በስካሁኑ ድጋፉን በማስተባበር እና ድጋፍ በማድረግ ተሳትፎ ላደረጉ አካላት በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በመከላከያ ሚኒስቴር የቅርስ ጥበቃና ሙዚየም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዴል ጄነራል ደሳለኝ ደቼ በበኩላቸው፣ ህግ የማስከበር ስራዎች የህዝቡን ድጋፍ የሚሹ ናቸው፤ 100 የማይሞላውን የጥፋት ቡድን 100 ሚሊየን በላይ በሚልቅ የህዝብ ድጋፍ ድል እናደርጋለን” ብለዋል፡፡
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ አባወይ ዮሃንስ በክፍለ ከተማው የሚገኙ ነዋሪዎች፣የመንግስት ሰራተኞች ፣ባለሀብቶች፣የጤና ባለሙያዎች ፣መምህራን፣ነጋዴዎችና በተለያየ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙ ነዋሪዎች በፈቃደኝነት የለገሱት መሆኑን ገልጸዋል።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት የፈጸመውና ተኩስ የጀመረው ላለፉት 27 አመታት የሰራቸውን ወንጀሎችና ጥፋቶች ለመሸፋፈንና ከተጠያቂነት ለማምለጥ አስቦ እንደሆነ የቀድሞው ጠ/ሚ/ር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሀገር መከላከያ ሰራዊትና ላይ ጥቃት የፈጸመውና ተኩስ የጀመረው ላለፉት 27 አመታት የሰራቸውን ወንጀሎችና ጥፋቶች ለመሸፈፈን ብሎም ከተጠያቂነት ለማምለጥ አስቦ እንደሆነ የቀድሞው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ።
አቶ ኃይለማርያም ለፎሬን ፖሊሲ መጽሄት በጻፉት ሰፋ ያለ ጽሁፍ፤ እርሳቸው በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት የከሀዲው ህወሓት አመራሮችን ባህሪና ጥፋት ጠንቅቀው እንደሚያውቁ ገልጸዋል።
ይሄው የህወሓት ከሀዲ ቡድን በማዕከላዊ መንግስት ስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ከፈጸማቸው ጥፋቶች ለማምለጥ ሲል ወደ ተኩስ ገብቷል ነው ያሉት አቶ ኃይለማርያም።
ላለፉት 27 አመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ብሎም በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የሰሩት ብሄር ተኮር መከፋፈሎች አገሪቷን ወደ ቀውስ ውስጥ እንደሚያስገባትና በዚህ መሀል እነሱ የራሳቸውን ሰዎችና አቅም ተጠቅመው የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ አድርገው ያስቡ ነበር ያሉት አቶ ኃይለማርያም፤ ነገሩ ግን በተቃራኒው ሄዶባቸው የፌዴራል መንግስቱን እና ኢትዮጵያዊያንን ከመቼውም በላይ አንድ አድርጎ እንዳጠናከራቸው አብራርተዋል።
መንግስትነ ህዝቡም ወንጀለኞችን ለፍትህ ለማቅረብ የተቀናጀ ስራ እንዲሰሩ አስችሏቸዋል ሲሉም ነው አቶ ኃይለማርያም የገለጹት።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ከዚህ በፊት ሲፈጽመው ከነበረውና አሁንም እየፈፀመው ካለው ወንጀል ራሱን ለማስመለጥ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ እንደሆነ የገለጹት አቶ ኃይለማርያም፤ ድርድር የሚለውም ለጊዜ መግዣና ችግሩን ዓለም አቀፍ ይዘት ለማሰጠት በዚህ መሀልም ወንጀሉን ደባብቆ ለማስቀረት ከተሳካለትም ስልጣን ለመጋራት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ድርድር የሚባለው ጉዳይ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የማይሆን መንገድ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ኃይለማርያም፤ መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር እርምጃ በአስቸኳይ ንፁሃን የክልሉን ነዋሪዎች በማይጎዳ መልኩ ፈጽሞ ከሀዲ ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ብቸኛው መፍትሄ ነው ሲሉ ከከሃዲው ጁንታ ባህሪ ተነስተው አብራርተዋል።
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሀገር መከላከያ ሰራዊትና ላይ ጥቃት የፈጸመውና ተኩስ የጀመረው ላለፉት 27 አመታት የሰራቸውን ወንጀሎችና ጥፋቶች ለመሸፈፈን ብሎም ከተጠያቂነት ለማምለጥ አስቦ እንደሆነ የቀድሞው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ።
አቶ ኃይለማርያም ለፎሬን ፖሊሲ መጽሄት በጻፉት ሰፋ ያለ ጽሁፍ፤ እርሳቸው በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት የከሀዲው ህወሓት አመራሮችን ባህሪና ጥፋት ጠንቅቀው እንደሚያውቁ ገልጸዋል።
ይሄው የህወሓት ከሀዲ ቡድን በማዕከላዊ መንግስት ስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ከፈጸማቸው ጥፋቶች ለማምለጥ ሲል ወደ ተኩስ ገብቷል ነው ያሉት አቶ ኃይለማርያም።
ላለፉት 27 አመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ብሎም በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የሰሩት ብሄር ተኮር መከፋፈሎች አገሪቷን ወደ ቀውስ ውስጥ እንደሚያስገባትና በዚህ መሀል እነሱ የራሳቸውን ሰዎችና አቅም ተጠቅመው የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ አድርገው ያስቡ ነበር ያሉት አቶ ኃይለማርያም፤ ነገሩ ግን በተቃራኒው ሄዶባቸው የፌዴራል መንግስቱን እና ኢትዮጵያዊያንን ከመቼውም በላይ አንድ አድርጎ እንዳጠናከራቸው አብራርተዋል።
መንግስትነ ህዝቡም ወንጀለኞችን ለፍትህ ለማቅረብ የተቀናጀ ስራ እንዲሰሩ አስችሏቸዋል ሲሉም ነው አቶ ኃይለማርያም የገለጹት።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ከዚህ በፊት ሲፈጽመው ከነበረውና አሁንም እየፈፀመው ካለው ወንጀል ራሱን ለማስመለጥ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ እንደሆነ የገለጹት አቶ ኃይለማርያም፤ ድርድር የሚለውም ለጊዜ መግዣና ችግሩን ዓለም አቀፍ ይዘት ለማሰጠት በዚህ መሀልም ወንጀሉን ደባብቆ ለማስቀረት ከተሳካለትም ስልጣን ለመጋራት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ድርድር የሚባለው ጉዳይ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የማይሆን መንገድ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ኃይለማርያም፤ መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር እርምጃ በአስቸኳይ ንፁሃን የክልሉን ነዋሪዎች በማይጎዳ መልኩ ፈጽሞ ከሀዲ ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ብቸኛው መፍትሄ ነው ሲሉ ከከሃዲው ጁንታ ባህሪ ተነስተው አብራርተዋል።