የማይካድራው ጭፍጨፋ የዓይን እማኝ
******************
(ኢ ፐ ድ)
መላ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፤ ከንፈሩ ደርቋል። ለሁለት ቀናት ምግብ አላገኘም። ድንጋጤ አለቀቀውም። ከማይካድራ ግድያ አምልጦ ሁመራ ከተማ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በር ላይ ያገኘነው ወጣት ዳንኤል ማሚን።
የደቡብ ክልል የቴፒ ተወላጅ ነው፤ አገር ሰላም ብሎ በማይካድራ ልብስ እየነገደ መኖር ከጀመረ 13 ዓመት ሆኖታል። በዚች ከተማ ይህን ያህል ሲኖር የከፋ አይደለም፤ ቀለል ያለ ችግርም አጋጥሞት አያውቅም። በሚኖርባትና ህይወቱን ለማሻሻል በሚደክምባት ከተማ ቤትና ንብረትም አፍርቷል።
ከሰባት ቀናት በፊት ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በማይካድራ ከተማ በአማራና በሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ያልታሰበ፣ አስደንጋጭና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በዓይኑ ተመልክቷል ፤ እሱም ከዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አምልጦ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ወደ ዋለችው ሁመራ ከተማ መምጣቱን ይናገራል።
የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻዎች በአማራና በሌሎች ብሄሮች የፈጸሙት ግፍና ግድያ በጣም የሚያስደነግጥ ያልታሰበ ነበር የሚለው ወጣቱ፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ በምንኖር ንጹሐን ሰዎች ላይ በትግራይ ሚሊሻዎችና ልዩ ኃይሎች ዘግናኝ ጥቃት ይደርስብናል ብለን አስበንም አልመንም አናውቅም። ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ በከተማዋ በሚኖሩ አማራን ጨምሮ በሌሎች ብሄሮች ዘግናኝ ድርጊት ፈጸሙ ይላል።
“መጀመሪያ ላይ ጥቃቱን የጀመሩት በወልቃይት አማራዎች ላይ መሆኑን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ንጹሐን ሰዎችን በየመንገዱ እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ። ሰው ሮጦ እንዳያመልጥ እንኳን መንገዱ በሚሊሻ ተከቧል። ሩጠው ለማምለጥ የሚሞክሩትን በጭካኔ በጥይት እየመቱ ገድሏቸዋል” ብሏል ።
በአይኔ ሰው ሲገደል አይቻላሁ። እኔም የዳንኤል ቤት የትኛው ነው እያሉ ሲጠይቁ ሰምቼ ሩጬ ማምለጥ ችያለሁ የሚለው ወጣቱ፤ በዚህ ቀውጢ ስዓት እሱም ሆነ ብዙ በርካታ ሰዎች እየሮጡ ጫካ ባይገቡና ባያመልጡ ኖሮ በማይካድራ ከተማ በግፍ እንደተገደሉት ንጹሐን ሰዎች ሁሉ የእሱም ዕጣ ፋንታ በህወሓት አሸባሪ ቡድን ይገደል እንደነበር ነግሮናል።
ሰዎች ሲገደሉ በዓይኑ ማየቱን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ሁለቱ ከድብደባው ለማምለጥ ሲሮጡ በጥይት ሁለቱ ደግሞ በሳንጃ አንገታቸውን ተወገተው አስፓልት ላይ ሲወድቁ እግሬ አውጪኝ ብሎ ከአካባቢው ተሰውሮ ጫካ መግባቱን ንግሮናል። ሰው በጭካኔ እየተገደለ ባየሁበት ከተማ ለመኖር አልጓጓም ያለው ወጣቱ ከሁመራ ወደ ጎንደር ከዚያም ወደ ትውልድ አገሩ ቴፒ ለመሄድ መወሰኑን ገልጾልናል።
ወጣት ዳንኤል፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ የህወሓት ጸንፈኛ ቡድንን ያልደገፈ የሚደርስበት ጫና እንግልት ከፍተኛ መሆኑን ይናገራል። ለትግራይ ልማት የሚሆን ገንዘብ አዋጣ ሲሉኝ 100.00 ብር አዋጣሁ። ሁለተኛ ዙርም ለውጊያ አዋጣ አሉኝ ። እኔም ውጊያውን ስለማላምንበት ብር የለኝም አልኳቸው። ለካስ ያላዋጣነው ሰዎች የቀበሌው የህወሓት ተላላኪዎች የስም ዝርዝራችንን ይዘው ኑሯል፤ጊዜ ጠብቀው የበቀል ጭካኔያቸውን አወረዱብን።
በየመኖሪያ ቤታችን እየዞሩ እስከ ወዲያኛው ሊያስናብቱን እየገሰገሱ መጡ። እግዜአብሄር አትርፎኝ ይኸው ሁመራ ከተማ አግኝተኸኛል” ሲል የጭካኔያቸው ጥግና የበቀል ዕርምጃቸው ከባድ መሆኑን ገልጾታል።
ማይካድራ ከተማ ውስጥ የሚኖር ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከትግራይ ቴሌቪዥንና ከወያኔ ድምፅ ቴሌቪዥን በስተቀር ሌሎች የቴሌዥን ጣቢያዎችን ማየት ወንጀል ነው የሚለው ወጣቱ፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ ዋልታ፣ ፋና ቴሌቪዥንና ሌሎች ህወሓት የሚጠላቸውን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ማየት ፈጽሞ የተከለከለና የሚያስቀጣ ነው። ሲያይ የተገኘም ካለ በህይወቱ የፈረደ ሰው ብቻ ነው ይላል።
ማይካድራ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል ማይካድራ ለምን አትምለስም የሚል ጥያቄ አቅርበንለት የወጣቱ ምልሽ ሌላ አካባቢ ሊስትሮም ቢሆን ሠርቼ መኖርን እመርጣሉሁ እንጂ ሁለተኛ ትግራይ ክልል አልኖርም። ምክንያቱም ያየሁት የጭካኔ አገዳዳል ለሌት በህልሜ ይመጣብኛል። ዘግናኝ ነው። ይህን እያስብኩ እዚያ ከተማ መኖር አልፈልግም። ህይወቴ ተመሰቃቅሏል ሲልም ያየው የጭካን ተግባር የቱን ያህል እንደጎዳው፣ ከቃላቶቹ በላይ ሁኔታውን ሲያስታውስ የሚሰማው ስሜት ይናገራል።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም
******************
(ኢ ፐ ድ)
መላ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፤ ከንፈሩ ደርቋል። ለሁለት ቀናት ምግብ አላገኘም። ድንጋጤ አለቀቀውም። ከማይካድራ ግድያ አምልጦ ሁመራ ከተማ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በር ላይ ያገኘነው ወጣት ዳንኤል ማሚን።
የደቡብ ክልል የቴፒ ተወላጅ ነው፤ አገር ሰላም ብሎ በማይካድራ ልብስ እየነገደ መኖር ከጀመረ 13 ዓመት ሆኖታል። በዚች ከተማ ይህን ያህል ሲኖር የከፋ አይደለም፤ ቀለል ያለ ችግርም አጋጥሞት አያውቅም። በሚኖርባትና ህይወቱን ለማሻሻል በሚደክምባት ከተማ ቤትና ንብረትም አፍርቷል።
ከሰባት ቀናት በፊት ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በማይካድራ ከተማ በአማራና በሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ያልታሰበ፣ አስደንጋጭና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በዓይኑ ተመልክቷል ፤ እሱም ከዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አምልጦ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ወደ ዋለችው ሁመራ ከተማ መምጣቱን ይናገራል።
የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻዎች በአማራና በሌሎች ብሄሮች የፈጸሙት ግፍና ግድያ በጣም የሚያስደነግጥ ያልታሰበ ነበር የሚለው ወጣቱ፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ በምንኖር ንጹሐን ሰዎች ላይ በትግራይ ሚሊሻዎችና ልዩ ኃይሎች ዘግናኝ ጥቃት ይደርስብናል ብለን አስበንም አልመንም አናውቅም። ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ በከተማዋ በሚኖሩ አማራን ጨምሮ በሌሎች ብሄሮች ዘግናኝ ድርጊት ፈጸሙ ይላል።
“መጀመሪያ ላይ ጥቃቱን የጀመሩት በወልቃይት አማራዎች ላይ መሆኑን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ንጹሐን ሰዎችን በየመንገዱ እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ። ሰው ሮጦ እንዳያመልጥ እንኳን መንገዱ በሚሊሻ ተከቧል። ሩጠው ለማምለጥ የሚሞክሩትን በጭካኔ በጥይት እየመቱ ገድሏቸዋል” ብሏል ።
በአይኔ ሰው ሲገደል አይቻላሁ። እኔም የዳንኤል ቤት የትኛው ነው እያሉ ሲጠይቁ ሰምቼ ሩጬ ማምለጥ ችያለሁ የሚለው ወጣቱ፤ በዚህ ቀውጢ ስዓት እሱም ሆነ ብዙ በርካታ ሰዎች እየሮጡ ጫካ ባይገቡና ባያመልጡ ኖሮ በማይካድራ ከተማ በግፍ እንደተገደሉት ንጹሐን ሰዎች ሁሉ የእሱም ዕጣ ፋንታ በህወሓት አሸባሪ ቡድን ይገደል እንደነበር ነግሮናል።
ሰዎች ሲገደሉ በዓይኑ ማየቱን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ሁለቱ ከድብደባው ለማምለጥ ሲሮጡ በጥይት ሁለቱ ደግሞ በሳንጃ አንገታቸውን ተወገተው አስፓልት ላይ ሲወድቁ እግሬ አውጪኝ ብሎ ከአካባቢው ተሰውሮ ጫካ መግባቱን ንግሮናል። ሰው በጭካኔ እየተገደለ ባየሁበት ከተማ ለመኖር አልጓጓም ያለው ወጣቱ ከሁመራ ወደ ጎንደር ከዚያም ወደ ትውልድ አገሩ ቴፒ ለመሄድ መወሰኑን ገልጾልናል።
ወጣት ዳንኤል፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ የህወሓት ጸንፈኛ ቡድንን ያልደገፈ የሚደርስበት ጫና እንግልት ከፍተኛ መሆኑን ይናገራል። ለትግራይ ልማት የሚሆን ገንዘብ አዋጣ ሲሉኝ 100.00 ብር አዋጣሁ። ሁለተኛ ዙርም ለውጊያ አዋጣ አሉኝ ። እኔም ውጊያውን ስለማላምንበት ብር የለኝም አልኳቸው። ለካስ ያላዋጣነው ሰዎች የቀበሌው የህወሓት ተላላኪዎች የስም ዝርዝራችንን ይዘው ኑሯል፤ጊዜ ጠብቀው የበቀል ጭካኔያቸውን አወረዱብን።
በየመኖሪያ ቤታችን እየዞሩ እስከ ወዲያኛው ሊያስናብቱን እየገሰገሱ መጡ። እግዜአብሄር አትርፎኝ ይኸው ሁመራ ከተማ አግኝተኸኛል” ሲል የጭካኔያቸው ጥግና የበቀል ዕርምጃቸው ከባድ መሆኑን ገልጾታል።
ማይካድራ ከተማ ውስጥ የሚኖር ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከትግራይ ቴሌቪዥንና ከወያኔ ድምፅ ቴሌቪዥን በስተቀር ሌሎች የቴሌዥን ጣቢያዎችን ማየት ወንጀል ነው የሚለው ወጣቱ፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ ዋልታ፣ ፋና ቴሌቪዥንና ሌሎች ህወሓት የሚጠላቸውን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ማየት ፈጽሞ የተከለከለና የሚያስቀጣ ነው። ሲያይ የተገኘም ካለ በህይወቱ የፈረደ ሰው ብቻ ነው ይላል።
ማይካድራ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል ማይካድራ ለምን አትምለስም የሚል ጥያቄ አቅርበንለት የወጣቱ ምልሽ ሌላ አካባቢ ሊስትሮም ቢሆን ሠርቼ መኖርን እመርጣሉሁ እንጂ ሁለተኛ ትግራይ ክልል አልኖርም። ምክንያቱም ያየሁት የጭካኔ አገዳዳል ለሌት በህልሜ ይመጣብኛል። ዘግናኝ ነው። ይህን እያስብኩ እዚያ ከተማ መኖር አልፈልግም። ህይወቴ ተመሰቃቅሏል ሲልም ያየው የጭካን ተግባር የቱን ያህል እንደጎዳው፣ ከቃላቶቹ በላይ ሁኔታውን ሲያስታውስ የሚሰማው ስሜት ይናገራል።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታምዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ ከፍተኛ የሆነ ሽንፈት ስለደረሰበት እና አብዛኛውን ግዛቱን እየተነጠቀ ስለሆነ ወደ ጥፋት ተልዕኮ እየገባ ነው።
እንደ ጠቅላይ ኢታምዦር ሹሙ ገለጻ፤ የጁንታው ታጣቂዎች ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሱ ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቶቹንና ተተኳሾቹን ቤተክርስቲያን ላይ አድርጓል።
የመከላከያ ሰራዊቱም ይሄንን በመገንዘብ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘራፊው ጁንታ በግሬደርና በዶዘር ታግዞ በከፍተኛ ሃብት የተሰራውን የአስፓልት መንገድ እየቆረጠ እና ድልድይ እያፈረሰ የሰራዊቱን እንቅስቃሴ ለመግታት ሙከራ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ለአብነት ያህልም በጨርጨር ግንባር ሶስት ድልድዮችን ማፍረሱን አስታውቀዋል።
በወንድወሰን ሽመልስ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታምዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ ከፍተኛ የሆነ ሽንፈት ስለደረሰበት እና አብዛኛውን ግዛቱን እየተነጠቀ ስለሆነ ወደ ጥፋት ተልዕኮ እየገባ ነው።
እንደ ጠቅላይ ኢታምዦር ሹሙ ገለጻ፤ የጁንታው ታጣቂዎች ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሱ ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቶቹንና ተተኳሾቹን ቤተክርስቲያን ላይ አድርጓል።
የመከላከያ ሰራዊቱም ይሄንን በመገንዘብ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘራፊው ጁንታ በግሬደርና በዶዘር ታግዞ በከፍተኛ ሃብት የተሰራውን የአስፓልት መንገድ እየቆረጠ እና ድልድይ እያፈረሰ የሰራዊቱን እንቅስቃሴ ለመግታት ሙከራ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ለአብነት ያህልም በጨርጨር ግንባር ሶስት ድልድዮችን ማፍረሱን አስታውቀዋል።
በወንድወሰን ሽመልስ
በምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት፤ በምዕራብ ወለጋ በጉሊሶ ዞን በአርሶ አደሩ ላይ ከተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ ወዲህ የኦሮሚያ ፖሊስ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ ቀጥለዋል።
በቅርቡም 142 በሚሆኑ የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገለጸው፤ 48 አባላት እጅ የሰጡ ሲሆን 64 የሚሆኑት ደግሞ ከህብረተሰቡ ውስጥ ቢቀላቀሉም እየተያዙ እንዳለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ ከሁለት ሳምንት ወዲህ በቅንጅት በተሰራው ስራ ይህንን ቡድን ከኦሮሚያ ለማፅዳት ጫካ ላለው ኦነግ ሸኔ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ 1 ሺህ 341 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለውል። ከነዚህ ውስጥ 104 የሚሆኑት የከሀዲው ህወሓት አባላት ናቸው፡፡
ቦንብን ጨምሮ 57 የጦር መሳሪያዎች ከ681 ጥይቶች ጋር መያዛቸውንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
አሁን ባለው ተጨባች ሁኔታ ኦነግ ሸኔ እና ከሃዲው የህወሓት ቡድን ለአንድ አላማ የሚሰሩ የጥፋት ሀይሎች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ኮሚሽነር መርዳሳ ማናገራቸውን የኦሮሚያ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡
በሀይማኖት ከበደ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት፤ በምዕራብ ወለጋ በጉሊሶ ዞን በአርሶ አደሩ ላይ ከተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ ወዲህ የኦሮሚያ ፖሊስ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ ቀጥለዋል።
በቅርቡም 142 በሚሆኑ የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገለጸው፤ 48 አባላት እጅ የሰጡ ሲሆን 64 የሚሆኑት ደግሞ ከህብረተሰቡ ውስጥ ቢቀላቀሉም እየተያዙ እንዳለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ ከሁለት ሳምንት ወዲህ በቅንጅት በተሰራው ስራ ይህንን ቡድን ከኦሮሚያ ለማፅዳት ጫካ ላለው ኦነግ ሸኔ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ 1 ሺህ 341 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለውል። ከነዚህ ውስጥ 104 የሚሆኑት የከሀዲው ህወሓት አባላት ናቸው፡፡
ቦንብን ጨምሮ 57 የጦር መሳሪያዎች ከ681 ጥይቶች ጋር መያዛቸውንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
አሁን ባለው ተጨባች ሁኔታ ኦነግ ሸኔ እና ከሃዲው የህወሓት ቡድን ለአንድ አላማ የሚሰሩ የጥፋት ሀይሎች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ኮሚሽነር መርዳሳ ማናገራቸውን የኦሮሚያ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡
በሀይማኖት ከበደ
ገቢዎች ሚኒስቴር በአራት ወራት ውስጥ ከ107 ነጥብ 8 ቢለዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት ለመሰብሰብ ካደቀው 104 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ 107 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አቶ ላቀ አያሌው አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ17.3 ቢሊየን ብር እድገት ማሳየቱን ጠቅሰው የህግ ተገዢነት ደረጃ መሻሻል፣ የተቋሙ ሰራተኛና አመራሮች ቁርጠኝነት መጨመር እና የገቢው መሰረትን ለማስፋት የተደረጉ ጥረቶች ገቢው እንዲጨምር ከሚጠቀሱ ምክንያቶች መካከል ናቸው።
እንደ አቶ ላቀ ገለጻ፤ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶችም በአራት ወራት መጠናከራቸውን ለገቢ አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡
ህግን ለማስከበር ከተከናወኑ ተግብራት መካከል የኮንትሮባንድ ክትትል አንዱ ሲሆን በወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የተገኘ መሆኑን አስታውቀዋል።
የፌደራል እና የክልል የጸጥታ አካላት፣ የጉምሩክ ኮምሽን ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች አጋር አካላት ሚና የላቀ በመሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት ለመሰብሰብ ካደቀው 104 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ 107 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አቶ ላቀ አያሌው አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ17.3 ቢሊየን ብር እድገት ማሳየቱን ጠቅሰው የህግ ተገዢነት ደረጃ መሻሻል፣ የተቋሙ ሰራተኛና አመራሮች ቁርጠኝነት መጨመር እና የገቢው መሰረትን ለማስፋት የተደረጉ ጥረቶች ገቢው እንዲጨምር ከሚጠቀሱ ምክንያቶች መካከል ናቸው።
እንደ አቶ ላቀ ገለጻ፤ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶችም በአራት ወራት መጠናከራቸውን ለገቢ አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡
ህግን ለማስከበር ከተከናወኑ ተግብራት መካከል የኮንትሮባንድ ክትትል አንዱ ሲሆን በወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የተገኘ መሆኑን አስታውቀዋል።
የፌደራል እና የክልል የጸጥታ አካላት፣ የጉምሩክ ኮምሽን ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች አጋር አካላት ሚና የላቀ በመሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአዲስ አበባ ባለቤት ያልተገኘላቸው ህንጻዎች 100 መድረሳቸውን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የከተማዋ ወጣቶች ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በከተማዋ የሚገኙ ህንጻዎች፣ ታጥረው የሚገኙ መሬቶች እና የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ እየተደረገ ባለው ዳሰሳ እስካሁን 100 ህንጻዎች ባለቤት አልተገኘላቸውም።
እንደ ኢቢሲ.ዘገባ፤ ከዚህም በተጨማሪ ታጥሮ የተቀመጠ ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ባለቤት ሳይገኝለት ቀርቷል።
በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ ቤቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ወጣቶች በትግራይ ክልል እየተደረገ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውን ገልጸዋል።
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የከተማዋ ወጣቶች ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በከተማዋ የሚገኙ ህንጻዎች፣ ታጥረው የሚገኙ መሬቶች እና የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ እየተደረገ ባለው ዳሰሳ እስካሁን 100 ህንጻዎች ባለቤት አልተገኘላቸውም።
እንደ ኢቢሲ.ዘገባ፤ ከዚህም በተጨማሪ ታጥሮ የተቀመጠ ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ባለቤት ሳይገኝለት ቀርቷል።
በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ ቤቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ወጣቶች በትግራይ ክልል እየተደረገ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን፣ አዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎች ድጋፍ አደረጉ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ራያ ቆቦ፡- በአዲስ አበበ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን ፣ የአዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ህግን ለማስከበር ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎችን በግንባር ተገኝተው ለሰራዊቱ አስረክበዋል፡፡
አቶ አብዱልጀሊል አብዱሮ የአዳማ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ በርክብክቡ ወቅት እንደተናገሩት፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሰራዊትና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት በመፈጸም ያነገበውን ሀገር የማፍረስ ዓላማ ለማኮላሸት መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር ርምጃ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ይደግፋል፡፡
የጁንታው አበላት ሀገርን ለማፍረስ ሲል የፈጸማቸውን የሽብር ተግባራት የክልሉ ህዝብ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ እንዳወገዘ ገልጸዋል፡፡
ህዝቡ ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን በመቆም ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ በመግለጽም ከተጠቀሱት ውስን የኦሮሚያ አካባቢዎች የተሰበሰበው ድጋፍ የሞራል ስንቅ ይሁን በሚል ይዘን መጥተናል ብለዋል፡፡
በዚህም መሰረት ከፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚ ልዩ ዞንና ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች የተሰባሰቡ 196 የዕርድ ሰንጋዎች እና ከምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ 230 ፍየሎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ለሠራዊቱ አስረክበዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ህዝብ መንግስት ተገዶ የገባበትን ህግ የማስከበር ርምጃ እንደሚደግፍና ከመከላካያ ሰራዊቱ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል፤ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አቶ አብዱልጀሊል ገልጸዋል፡፡
የራያ አላማጣና አካባቢው ግንባር አመራር አባል ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን በበኩላቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ተወካዮች ረዥም መንገድ ተጉዘው ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰራዊቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ተከትሎ ህዝቡ ከሰራዊቱ እኩል መቆጣቱ ለሀገሩና ለሰራዊቱ ያለውን ፍቅር፣ ክብርና ተቆርቋሪነት የሚያሳይ ነው፡፡
ለሰራዊቱ ድጋፍ በማድረግና ደጀን በመሆን ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሚደረገው ርብርብ የሚመሰገን ነው ብለዋል፡፡
ሰራዊቱ ህዝብን በማቀፍ በተሰማራባቸው ህግን የማስከበር ዘመቻዎቹ ሁሉ ውጤታማ እንደሆነና በሚቀጥሉት ቀናትም ሌሎች ድሎች እንደሚሰሙ ተናግረዋል፡፡
አንድ ተዋጊ ምንም አይነት ዘመናዊ መሳሪያ ቢታጠቅ የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ውጤታማ አይሆንም ያሉት ጀነራሉ እስከ አሁን የተገኙት ድሎችም የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ውጤቶች ናቸው ብለዋል፡፡
ይህ ከሀዲ ቡድን ተደምስሶ ወይም በቁጥጥር ስር ውሎ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰላሟን ታገኛለች ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ ፣ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንሳይ መኮንን ተገኝተው እንግዶቹን ተቀብለዋል፡፡ ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢያሱ መሰለ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ራያ ቆቦ፡- በአዲስ አበበ ዙሪያ የኦሮሚ ልዩ ዞን ፣ የአዳማ ከተማና የምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ በራያ አላማጣ አካባቢ ህግን ለማስከበር ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊት 196 የእርድ ሰንጋና 230 ፍየሎችን በግንባር ተገኝተው ለሰራዊቱ አስረክበዋል፡፡
አቶ አብዱልጀሊል አብዱሮ የአዳማ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ በርክብክቡ ወቅት እንደተናገሩት፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሰራዊትና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት በመፈጸም ያነገበውን ሀገር የማፍረስ ዓላማ ለማኮላሸት መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር ርምጃ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ይደግፋል፡፡
የጁንታው አበላት ሀገርን ለማፍረስ ሲል የፈጸማቸውን የሽብር ተግባራት የክልሉ ህዝብ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ እንዳወገዘ ገልጸዋል፡፡
ህዝቡ ከመከላከያ ሰራዊቱ ጎን በመቆም ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ በመግለጽም ከተጠቀሱት ውስን የኦሮሚያ አካባቢዎች የተሰበሰበው ድጋፍ የሞራል ስንቅ ይሁን በሚል ይዘን መጥተናል ብለዋል፡፡
በዚህም መሰረት ከፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚ ልዩ ዞንና ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች የተሰባሰቡ 196 የዕርድ ሰንጋዎች እና ከምስራቅ ባሌ ዞን ራይቱ ወረዳ 230 ፍየሎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ለሠራዊቱ አስረክበዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ህዝብ መንግስት ተገዶ የገባበትን ህግ የማስከበር ርምጃ እንደሚደግፍና ከመከላካያ ሰራዊቱ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል፤ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አቶ አብዱልጀሊል ገልጸዋል፡፡
የራያ አላማጣና አካባቢው ግንባር አመራር አባል ሌተናል ጀነራል ይመር መኮንን በበኩላቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት የኦሮሚያ ክልል መንግስት ተወካዮች ረዥም መንገድ ተጉዘው ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰራዊቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ተከትሎ ህዝቡ ከሰራዊቱ እኩል መቆጣቱ ለሀገሩና ለሰራዊቱ ያለውን ፍቅር፣ ክብርና ተቆርቋሪነት የሚያሳይ ነው፡፡
ለሰራዊቱ ድጋፍ በማድረግና ደጀን በመሆን ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሚደረገው ርብርብ የሚመሰገን ነው ብለዋል፡፡
ሰራዊቱ ህዝብን በማቀፍ በተሰማራባቸው ህግን የማስከበር ዘመቻዎቹ ሁሉ ውጤታማ እንደሆነና በሚቀጥሉት ቀናትም ሌሎች ድሎች እንደሚሰሙ ተናግረዋል፡፡
አንድ ተዋጊ ምንም አይነት ዘመናዊ መሳሪያ ቢታጠቅ የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ውጤታማ አይሆንም ያሉት ጀነራሉ እስከ አሁን የተገኙት ድሎችም የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ውጤቶች ናቸው ብለዋል፡፡
ይህ ከሀዲ ቡድን ተደምስሶ ወይም በቁጥጥር ስር ውሎ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰላሟን ታገኛለች ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ ፣ የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወልደትንሳይ መኮንን ተገኝተው እንግዶቹን ተቀብለዋል፡፡ ለተደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢያሱ መሰለ
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ።
ኩባንያው በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቁጥርም 6800 መሆኑን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው ወደ 6800 የፈለገውን የገንዘብ መጠን በማስገባት በመላክ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ክብር እና አጋርነት ማሳየት እንደሚችልም ኩባንያው ግልጽ አድርጓል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ-ቴሌኮም ለሀገር መከላከያ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት መቀበያ ቁጥር ይፋ አደረገ።
ኩባንያው በዛሬው እለት ይፋ ያደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቁጥርም 6800 መሆኑን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው ወደ 6800 የፈለገውን የገንዘብ መጠን በማስገባት በመላክ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ክብር እና አጋርነት ማሳየት እንደሚችልም ኩባንያው ግልጽ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የተከማቹ 19 ቦምብ እና ሌሎች የጦር መሣሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ውስጥ ኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገ አሰሳ 19 ቦምብ፣ 55 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 21 ሽጉጦች፣ 2 ኤስ ኬ ኤስ ጠመንጃ፣ 3 ቺኮዝ፣ 1 ብሬን፣ 6 ቺቺ ጠመንጃ እና ሌሎች ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 113 የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
በተጨማሪም 309 የሽጉጥ እና 4829 ዓይነታቸው የተለያየ ጥይቶች ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል።
በዚሁ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ትራኮን ሪልስቴት አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ 64ሺህ 200 የአሜሪካ ዶላር መያዙንና ጉዳዩ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተያዘውን ጨምሮ ከኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ 37 የእጅ ቦምብ፣ 1 ብሬን፣ 5 የጦር ሜዳ መነጽር፣ 18 የሬዲዮ መገናኛ ቁሳቁሶች፣ 589 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 350 ሽጉጦች፣ 46 የተለያዩ ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 1023 የተለያዩ ዓይነት የጦር መሣሪያዎች ከ10 ሺህ 404 መሰል ጥይቶች ጋር በብርበራ እና በፍተሻ መያዙን ገልጿል።
738 የተለያዩ የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት በፍተሻው ወቅት መገኘታቸውንም ጠቅሷል።
በተለያዩ ቦታዎች ተጥለው የተገኙ 7 የእጅ ቦምብ፣ 5 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 1 ተቀጣጣይ ፈንጂ፣ 3 ሽጉጥ፣ 2 የተለያዩ ጠመንጃዎች ከመሰል 841 ጥይቶቻቸው ጋር በኅብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውንም አመልክቷል።
የጥፋት ኃይሎች ለአዲስ አበባ ከተማ የደገሱላትን ሽብርና እልቂት ለመቀልበስ የሚከናወነው ጠንካራ ሕግን የማስከበር ተግባር በኅብረተሰቡ የዕለት ተዕለት መረጃ ሰጪነት እየታገዘ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ውስጥ ኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገ አሰሳ 19 ቦምብ፣ 55 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 21 ሽጉጦች፣ 2 ኤስ ኬ ኤስ ጠመንጃ፣ 3 ቺኮዝ፣ 1 ብሬን፣ 6 ቺቺ ጠመንጃ እና ሌሎች ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 113 የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
በተጨማሪም 309 የሽጉጥ እና 4829 ዓይነታቸው የተለያየ ጥይቶች ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል።
በዚሁ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ትራኮን ሪልስቴት አካባቢ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ 64ሺህ 200 የአሜሪካ ዶላር መያዙንና ጉዳዩ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ከኅዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተያዘውን ጨምሮ ከኅዳር 3 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ 37 የእጅ ቦምብ፣ 1 ብሬን፣ 5 የጦር ሜዳ መነጽር፣ 18 የሬዲዮ መገናኛ ቁሳቁሶች፣ 589 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 350 ሽጉጦች፣ 46 የተለያዩ ጠመንጃዎች በአጠቃላይ 1023 የተለያዩ ዓይነት የጦር መሣሪያዎች ከ10 ሺህ 404 መሰል ጥይቶች ጋር በብርበራ እና በፍተሻ መያዙን ገልጿል።
738 የተለያዩ የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት በፍተሻው ወቅት መገኘታቸውንም ጠቅሷል።
በተለያዩ ቦታዎች ተጥለው የተገኙ 7 የእጅ ቦምብ፣ 5 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 1 ተቀጣጣይ ፈንጂ፣ 3 ሽጉጥ፣ 2 የተለያዩ ጠመንጃዎች ከመሰል 841 ጥይቶቻቸው ጋር በኅብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውንም አመልክቷል።
የጥፋት ኃይሎች ለአዲስ አበባ ከተማ የደገሱላትን ሽብርና እልቂት ለመቀልበስ የሚከናወነው ጠንካራ ሕግን የማስከበር ተግባር በኅብረተሰቡ የዕለት ተዕለት መረጃ ሰጪነት እየታገዘ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የሻለቃው ትውስታ- ከሸሸቢት እስከ ዓዲ ዳዕሮ
*************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲነብሪ አካባቢ ታንኮች እዚህም እዚያ ተፈነጣጥረው ቆመው ግዳጃቸውን ለመፈጸም በተጠንቀቅ እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ የሽብርተኛውን የህወሓት ጁንታ ታጣቂዎች ለመደምሰስ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ከእነዚህ ታንኮች መካከል የአንዷ ሹፌር ሻለቃ ባሻ በየነ ይባላል፡፡
ሻለቃ ባሻ የሰሜን ዕዝ ስምንተኛ መካናይዝድ አባል ነው፡፡ እሱም ሆነ ጓዶቹ ቀን የአርሶ አደሩን ምርት ለመሰብሰብ አጨዳ ላይ ውለውና በተግባራቸው ረክተው ደክሟቸው አገር ሰላም ብለው በተኙበት ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ የትግራይ ልዩ ሀይል ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ ነው ከእንቅልፋቸው የነቁት ።
በወቅቱም የከበባቸው የጽንፈኛው የህወሓት ሀይል መትተው መመለስ መቻላቸውን ሻለቃ በሻ ያስታወሳሉ። ይህ አሳዘኝ ክስትት በተከሰተ ማግሰት የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች የሻለቃ አመራራቸው በስሩ የሚገኙ ሁሉም የሠራዊት አባላት መሳሪያውን ወደ መጋዘን አስገቡ በማለት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ያስታውሳሉ።
በተቃራኒው የእሱን ትዕዛዙን ሊያስተባብር ወደ ሠራዊቱ የመጣው ኮነሬል ዳኘው ጦሩ መሳሪያውን ወደ መጋዘን እንዳያስገባ ይልቁኑ በየምሽጉ ሆኖ ራሱን እንዲከላከልና ሁኔታዎችን በጥብቅ እንዲከታተል አደረጉ ፤የጁንታው ቡድን ተላላኪ የሆነው ሻለቃ ትዕዛዙ ሊፈጸም አለመቻሉን ለትግራይ ልዩ ሀይል መረጃ በመስጠቱ በማግስቱ ከቀኑ 5፤ከ30 ላይ ከአንድ ሺ በላይ የሚሆኑ የትግራይ ልዩ ሀይል የሦስተኛ ሻለቃ ካምፕ ውስጥ በሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የተጠናከረ ጥቃት ከፈቱ።
በዚህ ጊዜም በሠራዊቱ ውስጥ የነበሩ የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች ጦሩ ከተከፈተበት ጥቃት እንዳይከላከል ሲያዘናጉ ቆይተው ሠራዊቱ ለመከላከል ከግቢ እንደወጣ የሻለቃ አመራሮች ፣ኦፕሬተሮችና የመድፍ አስተኳሽ፣ የታንክ ሹፌሮች ወደ ትግራይ ልዩ ሀይል ተቀላቀሉ ።
በወቅቱ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ቁጥር 225 ቢሆንም በብረት ለበስ ብርታት ጽንፈኛው ኃይል በሠራዊቱ ላይ የሰራውን ቀለበት ሰብረው ሊወጡ መቻላቸውን ይናገራሉ። ከረፋዱ 5 ሰዓት በተጀመረው ውጊያም ከቀኑ10 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ጽንፈኛውን ሀይል በብቃት መክተው መልሰዋል። በተለይ መድፈኛ ሻለቃዋን ለማፈን ያደረገው ጥረት በጀግናው ሰራዊት ተጋድሎ የመድፎቹን መርፌ ማውጣት በመቻሉ ጽንፈኛው ሀይል መድፎቹን ጉትቶ ይዞ እንዳይሄድ አድርገዋል።
የእኛ ካምፕ ከአዲሃገራይ 7 ኪሎ ሜትር ይርቃል የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፣አዲሃገራይ ወደ ሚገኘው የክፍለ ጦር ማዘዣቸው ጽንፈኛውን ሀይል እየተከላከሉ መሄዳቸውን ጠቅሰው፤ከዚያም ሀይል ጦሩ በማህይንጻ አድርጎ ጓል ባድሜ አቋርጦ ወደ ኤርትራ ሸሸቢት ወደ ምትባል ስፍራ ማፈግፈጋቸውን ነው የነገሩን ።
ከሁለት ቀናት ራስን የመከላከልና አድካሚ የእግር ጉዞ በኋላም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከ25 ደቂቃ አካባቢ ኤርትራ ሸሸቢት የምትባል ስፍራ ደርሰዋል ። በዚያም የኤርትራ ህዝብ በሸሸቢት ትምህርት ቤት የቁርስ ግብዣ እንዳደረገላቸው ገልጸውልናል።
ከ”36 ሰዓት በኋላ ነው በሸሸቢት ውሃ የቀረበልንና ምግብ ያገኘነው። በኮዳ ከያዝናት ውሃ በክዳኗ ፉት እያልንና ለሁለት ቀናት ምግብ ሳንበላ የጽንፈኛውን ቡድን ያልተመጣጠነ ጥቃት እየመከትን ኤርትራ ደረስን”ብለዋል።
ግዳጁን ከበድ የሚያደርገው ከውስጣችን ጓዶቻችን ብለን ስናምናቸው የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ከጎናችን ሆነው የእኛን ጓዶች መግደላቸውና መውጋታቸው ነው የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፤እነዚህ ካህዲዎች የታንክ ሹፌሮችን ሳይቀር ገድለውብን ፤በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ግፍ እንደሆነ አመልክተዋል።
አብረህ በልተህ፣ አብረህ ጠጥተህ ይህን አይነት ግፍ መፈጸም በኢትዮጵያ ባህል ያልተለመደ ነው። እኔን ጨምሮ ሌሎች ጓዶቻችን ከ1991ዓ.ም ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ ከምናገኘው ደመወዝ እያዋጣን ትምህርት ቤት፤ጤና ጣቢያ፣መንገድ ሰርተናል። ለህዝብ ጋሻ በሆነው መካላከያ ሠራዊት የዚህ አይነት ክህደት ሲፈጸም በጣም ያማል፤ ያበሳጫልና፣ ያናድዳል፤ያሳዝናልም ብሏል።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ፣ የሌላ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ጓዶቻቸውን በጥይትና በሳንጃ ሲመቱና ሲያርዱ በአይኔ አይቻለሁ፡ እኛም የአጸፋ እርምጃ የወሰድንባቸው አሉ፣ ክህደቱ በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝብም ጭምር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ይህም ድርጊት ሠራዊቱን በጣም አስቆጭቶት በሞራልና በወኔ ጽንፈኛውን ሀይል በመደምሰስ ድል በድል እየተቀናጀ ወደፊት እየገሰገሰ ነው። ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ድባቅ እየተመታ ነው ብለዋል ።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 11/2013
*************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲነብሪ አካባቢ ታንኮች እዚህም እዚያ ተፈነጣጥረው ቆመው ግዳጃቸውን ለመፈጸም በተጠንቀቅ እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ የሽብርተኛውን የህወሓት ጁንታ ታጣቂዎች ለመደምሰስ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ከእነዚህ ታንኮች መካከል የአንዷ ሹፌር ሻለቃ ባሻ በየነ ይባላል፡፡
ሻለቃ ባሻ የሰሜን ዕዝ ስምንተኛ መካናይዝድ አባል ነው፡፡ እሱም ሆነ ጓዶቹ ቀን የአርሶ አደሩን ምርት ለመሰብሰብ አጨዳ ላይ ውለውና በተግባራቸው ረክተው ደክሟቸው አገር ሰላም ብለው በተኙበት ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ የትግራይ ልዩ ሀይል ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ ነው ከእንቅልፋቸው የነቁት ።
በወቅቱም የከበባቸው የጽንፈኛው የህወሓት ሀይል መትተው መመለስ መቻላቸውን ሻለቃ በሻ ያስታወሳሉ። ይህ አሳዘኝ ክስትት በተከሰተ ማግሰት የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች የሻለቃ አመራራቸው በስሩ የሚገኙ ሁሉም የሠራዊት አባላት መሳሪያውን ወደ መጋዘን አስገቡ በማለት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ያስታውሳሉ።
በተቃራኒው የእሱን ትዕዛዙን ሊያስተባብር ወደ ሠራዊቱ የመጣው ኮነሬል ዳኘው ጦሩ መሳሪያውን ወደ መጋዘን እንዳያስገባ ይልቁኑ በየምሽጉ ሆኖ ራሱን እንዲከላከልና ሁኔታዎችን በጥብቅ እንዲከታተል አደረጉ ፤የጁንታው ቡድን ተላላኪ የሆነው ሻለቃ ትዕዛዙ ሊፈጸም አለመቻሉን ለትግራይ ልዩ ሀይል መረጃ በመስጠቱ በማግስቱ ከቀኑ 5፤ከ30 ላይ ከአንድ ሺ በላይ የሚሆኑ የትግራይ ልዩ ሀይል የሦስተኛ ሻለቃ ካምፕ ውስጥ በሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ የተጠናከረ ጥቃት ከፈቱ።
በዚህ ጊዜም በሠራዊቱ ውስጥ የነበሩ የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች ጦሩ ከተከፈተበት ጥቃት እንዳይከላከል ሲያዘናጉ ቆይተው ሠራዊቱ ለመከላከል ከግቢ እንደወጣ የሻለቃ አመራሮች ፣ኦፕሬተሮችና የመድፍ አስተኳሽ፣ የታንክ ሹፌሮች ወደ ትግራይ ልዩ ሀይል ተቀላቀሉ ።
በወቅቱ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ቁጥር 225 ቢሆንም በብረት ለበስ ብርታት ጽንፈኛው ኃይል በሠራዊቱ ላይ የሰራውን ቀለበት ሰብረው ሊወጡ መቻላቸውን ይናገራሉ። ከረፋዱ 5 ሰዓት በተጀመረው ውጊያም ከቀኑ10 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ጽንፈኛውን ሀይል በብቃት መክተው መልሰዋል። በተለይ መድፈኛ ሻለቃዋን ለማፈን ያደረገው ጥረት በጀግናው ሰራዊት ተጋድሎ የመድፎቹን መርፌ ማውጣት በመቻሉ ጽንፈኛው ሀይል መድፎቹን ጉትቶ ይዞ እንዳይሄድ አድርገዋል።
የእኛ ካምፕ ከአዲሃገራይ 7 ኪሎ ሜትር ይርቃል የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፣አዲሃገራይ ወደ ሚገኘው የክፍለ ጦር ማዘዣቸው ጽንፈኛውን ሀይል እየተከላከሉ መሄዳቸውን ጠቅሰው፤ከዚያም ሀይል ጦሩ በማህይንጻ አድርጎ ጓል ባድሜ አቋርጦ ወደ ኤርትራ ሸሸቢት ወደ ምትባል ስፍራ ማፈግፈጋቸውን ነው የነገሩን ።
ከሁለት ቀናት ራስን የመከላከልና አድካሚ የእግር ጉዞ በኋላም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከ25 ደቂቃ አካባቢ ኤርትራ ሸሸቢት የምትባል ስፍራ ደርሰዋል ። በዚያም የኤርትራ ህዝብ በሸሸቢት ትምህርት ቤት የቁርስ ግብዣ እንዳደረገላቸው ገልጸውልናል።
ከ”36 ሰዓት በኋላ ነው በሸሸቢት ውሃ የቀረበልንና ምግብ ያገኘነው። በኮዳ ከያዝናት ውሃ በክዳኗ ፉት እያልንና ለሁለት ቀናት ምግብ ሳንበላ የጽንፈኛውን ቡድን ያልተመጣጠነ ጥቃት እየመከትን ኤርትራ ደረስን”ብለዋል።
ግዳጁን ከበድ የሚያደርገው ከውስጣችን ጓዶቻችን ብለን ስናምናቸው የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ከጎናችን ሆነው የእኛን ጓዶች መግደላቸውና መውጋታቸው ነው የሚሉት ሻለቃ ባሻ ፤እነዚህ ካህዲዎች የታንክ ሹፌሮችን ሳይቀር ገድለውብን ፤በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ግፍ እንደሆነ አመልክተዋል።
አብረህ በልተህ፣ አብረህ ጠጥተህ ይህን አይነት ግፍ መፈጸም በኢትዮጵያ ባህል ያልተለመደ ነው። እኔን ጨምሮ ሌሎች ጓዶቻችን ከ1991ዓ.ም ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ ከምናገኘው ደመወዝ እያዋጣን ትምህርት ቤት፤ጤና ጣቢያ፣መንገድ ሰርተናል። ለህዝብ ጋሻ በሆነው መካላከያ ሠራዊት የዚህ አይነት ክህደት ሲፈጸም በጣም ያማል፤ ያበሳጫልና፣ ያናድዳል፤ያሳዝናልም ብሏል።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የጁንታው ቡድን ተላላኪዎች ፣ የሌላ ብሄር ተወላጅ የሆኑ የመከላከያ ጓዶቻቸውን በጥይትና በሳንጃ ሲመቱና ሲያርዱ በአይኔ አይቻለሁ፡ እኛም የአጸፋ እርምጃ የወሰድንባቸው አሉ፣ ክህደቱ በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝብም ጭምር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ይህም ድርጊት ሠራዊቱን በጣም አስቆጭቶት በሞራልና በወኔ ጽንፈኛውን ሀይል በመደምሰስ ድል በድል እየተቀናጀ ወደፊት እየገሰገሰ ነው። ጽንፈኛው የህወሓት ቡድን በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ድባቅ እየተመታ ነው ብለዋል ።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 11/2013
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የፈጸመው 27 ዓመታት የቆየበትን ስልጣን ዳግም ለመያዝ አስቦ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ አስታወቁ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም ወደ ግጭት የገባው የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በኃይል በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ይዞት ወደነበረው ስልጣን ለመመለስ በማሰብ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ ሚስተር ቲቦር ናጊ አስታወቁ፡፡
ምክትል ፀሃፊው ሚስተር ቲቦር ናጊ ለጋዜጠኞች በቴሌ ኮንፈረንስ እንደገለፁት፤ የህወሓት ቡድን ወደ ጥቃት የገባው የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር ከስልጣን በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት ለማስመለስና ወደ ሥልጣን ለመውጣት ያሰቡት ነው።
የህወሓት ቡድን የተከተለው ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለበት የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያዊያን በሚያስገርም ብሄራዊ ቁጭት ጠቅላይ ሚንስትሩን በመደገፍ እንደ አገር ያሰባሰበ ሆኗል ነው ያሉት።
የአገሪቱ ሕገ መንግስትም ራስን በራስ የማስተዳደርን መብት የሚደነግግ መሆኑን አስታውሰው፤ ቡድኑ የቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ በተቀራኒ የስጣን ጥምን ለማርካት ታስቦ የሚደረግ ስለመሆኑም አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም ሕግን ለማስከበር እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ትልቅ ትኩረት መስጠቱንም ጠቁመውል፡፡ በዚህ ህግን የማስከበር እርምጃ ንጹሃን እንዳይጎዱም ከለላ መደረጉ የአሜሪካም ፍላጎት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ መንግስትም ይህን በተግባር ለማዋል ቁርጠኛ ስለመሆኑና ንጹሃንን ለመታደግ ፅኑ ፍላጎት እንዳለው ሚስተር ቲቦር ናጊ አብራርተዋል፡፡
የትግራይ ህዝበ እንደጠላት አለመታየቱንና ፀቡም ከቡድኑ ጋር መሆኑን የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ ይልቁንም አገሪቱ በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ ቡድን የፈጠረውን ሀከት ለማረጋጋት እየተወሰደ የሚገኝ እርምጃ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ አባላት ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓም ሌሊት ጥቃት በመፈጸም ብዙዎችን ዘግናኝ በሆነ መልኩ እንደገደለና የተቀሩትን አፍኖ እንደወሰደ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ጁንታው ከፍተኛ ኪሰራ እየደረሰበት በመሆኑ እንደ ማይካድራ ባሉ ከተሞች በንጹሀን ላይ ጭፍጨፋ መፈጸሙ ይታወሳል፤ በዚህም አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳወገዙት ይታወቃል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈጸም ወደ ግጭት የገባው የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በኃይል በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ይዞት ወደነበረው ስልጣን ለመመለስ በማሰብ መሆኑን በአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ፀሃፊ ሚስተር ቲቦር ናጊ አስታወቁ፡፡
ምክትል ፀሃፊው ሚስተር ቲቦር ናጊ ለጋዜጠኞች በቴሌ ኮንፈረንስ እንደገለፁት፤ የህወሓት ቡድን ወደ ጥቃት የገባው የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር ከስልጣን በማስወገድ ላለፉት 27 ዓመታት በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት ለማስመለስና ወደ ሥልጣን ለመውጣት ያሰቡት ነው።
የህወሓት ቡድን የተከተለው ስልት ተቃራኒ ነገር እንዳስከተለበት የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ አሁን ላይ ኢትዮጵያዊያን በሚያስገርም ብሄራዊ ቁጭት ጠቅላይ ሚንስትሩን በመደገፍ እንደ አገር ያሰባሰበ ሆኗል ነው ያሉት።
የአገሪቱ ሕገ መንግስትም ራስን በራስ የማስተዳደርን መብት የሚደነግግ መሆኑን አስታውሰው፤ ቡድኑ የቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ በተቀራኒ የስጣን ጥምን ለማርካት ታስቦ የሚደረግ ስለመሆኑም አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም ሕግን ለማስከበር እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ትልቅ ትኩረት መስጠቱንም ጠቁመውል፡፡ በዚህ ህግን የማስከበር እርምጃ ንጹሃን እንዳይጎዱም ከለላ መደረጉ የአሜሪካም ፍላጎት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ መንግስትም ይህን በተግባር ለማዋል ቁርጠኛ ስለመሆኑና ንጹሃንን ለመታደግ ፅኑ ፍላጎት እንዳለው ሚስተር ቲቦር ናጊ አብራርተዋል፡፡
የትግራይ ህዝበ እንደጠላት አለመታየቱንና ፀቡም ከቡድኑ ጋር መሆኑን የጠቀሱት ቲቦር ናጊ፤ ይልቁንም አገሪቱ በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ ቡድን የፈጠረውን ሀከት ለማረጋጋት እየተወሰደ የሚገኝ እርምጃ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል።
ከሀዲው የህወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ አባላት ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓም ሌሊት ጥቃት በመፈጸም ብዙዎችን ዘግናኝ በሆነ መልኩ እንደገደለና የተቀሩትን አፍኖ እንደወሰደ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ጁንታው ከፍተኛ ኪሰራ እየደረሰበት በመሆኑ እንደ ማይካድራ ባሉ ከተሞች በንጹሀን ላይ ጭፍጨፋ መፈጸሙ ይታወሳል፤ በዚህም አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዳወገዙት ይታወቃል።
ሰበር ዜና!
አዲግራት ከተማ ከህወሓት ጁንታ ነጻ ወጣች
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአዲግራት ከተማን ዛሬ ከህወሃት ጁንታ ሃይል ነጻ አወጣ።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጠዋት የህወሃት ጁንታ ሃይልን ድል አድርጎ የአዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዳወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ አስታወቀ።
የመከላከያ ሠራዊታችን በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ እየገሰገሰ ነው።
አዲግራት ከተማ ከህወሓት ጁንታ ነጻ ወጣች
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአዲግራት ከተማን ዛሬ ከህወሃት ጁንታ ሃይል ነጻ አወጣ።
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጠዋት የህወሃት ጁንታ ሃይልን ድል አድርጎ የአዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዳወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጣሪያ አስታወቀ።
የመከላከያ ሠራዊታችን በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ እየገሰገሰ ነው።
“የሰሜን ዕዝ ሰራዊት አባላት እርቃናቸውን እንዲሆኑ ተደርገዋል፤ ተገድለዋል ፤ ታፍነው ተወስደዋል”
- ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከጥቃቱ ያመለጡ የሰራዊቱ አባል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ታጣቂዎች በሰሜን እዝ ሰራዊት ላይ ያደረሱትን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ ከእነሱ ጋር አልተባበርም ያሉትን
መግደላቸውንና የተቀረውን ማፈናቸውን ሌሎችን ደግሞ እርቃናቸውን ማባረራቸውን ከጥቃቱ ያመለጠው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ አስታወቀ።
የሰሜን ዕዝ 4ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከመከላከያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ እንደተናገረው፤ የክፍለ ጦሩ አመራሮች ከከሀዲው የህወሓት ጁንታ ጋር በነበራቸው ሚስጥራዊ ግንኙነት አስቀድመው ለዋርድያ መጠበቂያ ብቻ አንድ መሳሪያ በማስቀረት ሌላው መስሪያ ወደ ግምጃ ቤት እንዲገባ አድርገዋል።
በመቀጠልም የባንዳው ተላላኪ በሆነው የክፍለ ጦሩ አዛዥ ትዕዛዝ ገቢ የተደረገው መሳሪያ በከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የገለጸው ሻለቃ አምሳሉ፤ ሰራዊቱም ያልጠበቀው ክህደት ሲያጋጥመው ወደ መሳሪያ ግምጃ ቤት ቢያቀናም በታጣቂዎቹ ተኩስ እንደተከፈተበትና ግድያ እንደተፈጸመበት ተናግሯል።
ከሃዲው የህወሓት ቡድን መሳሪያ የሚቀመጥበትን ቦታ ተቆጣጥረው ከዘረፉና መግደል የፈለጉትን ከገደሉ በኋላ የተረፈውን ሰራዊት ልብሱን አስወልቀው እርቃኑን በማድረግ ወደ አዳራሽ አስገብተው እንዳፈኗቸው ጠቁመዋል።
ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ እንደገለፁት፣ ከሀዲው ቡድን በዕለቱ ከግድያ ለተረፉት የሰራዊቱ አባላት ያቀረበው አማራጭ አብሮ ለ20 ዓመት ከኖረና ለ20 ዓመት የትግራይን ህዝብ ላገለገለ ሰራዊት የማይገባው ነበር ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ “ከእኛ ጋር ወግኑ አሊያም በህይወታችሁ ፍረዱ የሚል አማራጭ እንዳቀረቡላቸው አስታውቀዋል።
የከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በክተት በታንከኛ፣ በመድፈኛ፣ በአየር መቃወሚያና በከባድ መሳሪያ ስልጣናዎችን እየወሰዱ እንደሆነ በመረዳታቸው ይህን ተግባር አግባብ እንዳልሆነ ሰራዊቱ ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበር ያስታወሰው ሻለቃው፤ የክፈለ ጦሩ አዛዥ “ከፈለጉ ሌላም ይታጠቁ የክልሉ ሥራ ነው” በሚል ያለመቀበል ሁኔታዎች እንደነበር ገልጿል።
በተለይ የአራተኛ ሜካናይዝ ክፍለ ጦር ኃላፊ ከሰራዊቱ በተቃራኒ የመቆምና ሃሳብን ያለመቀበል፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ሥሩ የሚል ትዕዛዛት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሷል።
“የክፍለ ጦሩ አመራር ለውጡን ባለመቀበል ወደ ብሔርተኝነት አሳተሳሰብ ያዘነበለ ስለነበር ሠራዊቱን አስመትተውታል” ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ ቀን ቀን ካንገት በላይ ሲያወሩ ይውላሉ፤ ማታ መቀሌ ሄደው ሲያሴሩ እንደነበር አስታውቋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42137
- ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከጥቃቱ ያመለጡ የሰራዊቱ አባል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው የህወሓት ቡድን ታጣቂዎች በሰሜን እዝ ሰራዊት ላይ ያደረሱትን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ ከእነሱ ጋር አልተባበርም ያሉትን
መግደላቸውንና የተቀረውን ማፈናቸውን ሌሎችን ደግሞ እርቃናቸውን ማባረራቸውን ከጥቃቱ ያመለጠው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ አስታወቀ።
የሰሜን ዕዝ 4ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ ከመከላከያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ እንደተናገረው፤ የክፍለ ጦሩ አመራሮች ከከሀዲው የህወሓት ጁንታ ጋር በነበራቸው ሚስጥራዊ ግንኙነት አስቀድመው ለዋርድያ መጠበቂያ ብቻ አንድ መሳሪያ በማስቀረት ሌላው መስሪያ ወደ ግምጃ ቤት እንዲገባ አድርገዋል።
በመቀጠልም የባንዳው ተላላኪ በሆነው የክፍለ ጦሩ አዛዥ ትዕዛዝ ገቢ የተደረገው መሳሪያ በከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ሰራዊቱ ላይ ጥቃት መፈጸሙን የገለጸው ሻለቃ አምሳሉ፤ ሰራዊቱም ያልጠበቀው ክህደት ሲያጋጥመው ወደ መሳሪያ ግምጃ ቤት ቢያቀናም በታጣቂዎቹ ተኩስ እንደተከፈተበትና ግድያ እንደተፈጸመበት ተናግሯል።
ከሃዲው የህወሓት ቡድን መሳሪያ የሚቀመጥበትን ቦታ ተቆጣጥረው ከዘረፉና መግደል የፈለጉትን ከገደሉ በኋላ የተረፈውን ሰራዊት ልብሱን አስወልቀው እርቃኑን በማድረግ ወደ አዳራሽ አስገብተው እንዳፈኗቸው ጠቁመዋል።
ሻለቃ አምሳሉ ደመቀ እንደገለፁት፣ ከሀዲው ቡድን በዕለቱ ከግድያ ለተረፉት የሰራዊቱ አባላት ያቀረበው አማራጭ አብሮ ለ20 ዓመት ከኖረና ለ20 ዓመት የትግራይን ህዝብ ላገለገለ ሰራዊት የማይገባው ነበር ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ “ከእኛ ጋር ወግኑ አሊያም በህይወታችሁ ፍረዱ የሚል አማራጭ እንዳቀረቡላቸው አስታውቀዋል።
የከሀዲው ህወሓት ታጣቂዎች በክተት በታንከኛ፣ በመድፈኛ፣ በአየር መቃወሚያና በከባድ መሳሪያ ስልጣናዎችን እየወሰዱ እንደሆነ በመረዳታቸው ይህን ተግባር አግባብ እንዳልሆነ ሰራዊቱ ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበር ያስታወሰው ሻለቃው፤ የክፈለ ጦሩ አዛዥ “ከፈለጉ ሌላም ይታጠቁ የክልሉ ሥራ ነው” በሚል ያለመቀበል ሁኔታዎች እንደነበር ገልጿል።
በተለይ የአራተኛ ሜካናይዝ ክፍለ ጦር ኃላፊ ከሰራዊቱ በተቃራኒ የመቆምና ሃሳብን ያለመቀበል፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ሥሩ የሚል ትዕዛዛት ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሷል።
“የክፍለ ጦሩ አመራር ለውጡን ባለመቀበል ወደ ብሔርተኝነት አሳተሳሰብ ያዘነበለ ስለነበር ሠራዊቱን አስመትተውታል” ያለው ሻለቃ አምሳሉ፤ ቀን ቀን ካንገት በላይ ሲያወሩ ይውላሉ፤ ማታ መቀሌ ሄደው ሲያሴሩ እንደነበር አስታውቋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42137
“ጁንታው ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ጊዜ ለመግዛት እንደራደር ማለቱ የሚጠበቅ ነው”
- አቶ ታዬ ደንደኣ
የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ብሎም ለሌላ ጥፋት ጊዜ ለመግዛት እንደራደር የሚል አጀንዳ ይዞ መምጣቱ የሚጠበቅ እንደሆነ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አስታወቁ።
አቶ ታዬ በተለይ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መከላከያ ሠራዊት ምናልባትም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ሕዝቦች አሁን የሚፈልጉት የሕወሓት ጁንታ ስብስብ እንዲወገድ ነው ብለዋል።
ቡድኑ ላለፉት 27 ዓመታት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአልሸባብ ጋር ተዳምሮ ለቀጠናው የሰላምና መረጋጋት እጦት ምክንያት እንደነበር አመልክተው ፣ይህ ቡድን እንዲቀጥል እድል መስጠት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አለመረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና መዳከም እንዲቀጥል መፍቀድ እንደሆነም አመልክተዋል ።
ጁንታው ቡድን ያሰበው ሁሉ ከንቱ ሆኖ ሲቀርበት ስለድርድር እየጮኸ ነው ያሉት አቶ ታዬ ደንደኣ፣ የቡድኑን የእንደራደር ጩኸት በሁለት መልኩ ማየት የተሻለ ነው ብለዋል። አንደኛውና ዋናው የዚህችን አገር ሕገ መንግስት ከጣሰ፤ የዚህችን አገር ሉዓላዊነት ከደፈረ ጁንታ ቡድን ጋር በምንም አይነት መልኩ ድርድር የሚቀመጥ አካል ሊኖር አይችልም።
ድርድር ሲታሰብ መጀመሪያ ከሕግ በታች በተለይም ከሕገ መንግስት በታች ባለው ነገር ላይ መሆን አለበት። መከላከያን ያጠቃ፤ የዚህችን አገር የሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን፣ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ነጻነትና ክብር የሚንጸባረቅበት ተቋምን ለማፍረስ ይሄን አይነት ተንኮል የሸረበ ሴረኛ ጋር በፍጹም ድርድር አያስፈልግም ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42094
- አቶ ታዬ ደንደኣ
የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የህወሓት ጁንታ ሕይወቱን ለማትረፍ እና ለሌላ ሴራና ተንኮል ብሎም ለሌላ ጥፋት ጊዜ ለመግዛት እንደራደር የሚል አጀንዳ ይዞ መምጣቱ የሚጠበቅ እንደሆነ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አስታወቁ።
አቶ ታዬ በተለይ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መከላከያ ሠራዊት ምናልባትም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ሕዝቦች አሁን የሚፈልጉት የሕወሓት ጁንታ ስብስብ እንዲወገድ ነው ብለዋል።
ቡድኑ ላለፉት 27 ዓመታት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአልሸባብ ጋር ተዳምሮ ለቀጠናው የሰላምና መረጋጋት እጦት ምክንያት እንደነበር አመልክተው ፣ይህ ቡድን እንዲቀጥል እድል መስጠት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና አለመረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ቀውስና መዳከም እንዲቀጥል መፍቀድ እንደሆነም አመልክተዋል ።
ጁንታው ቡድን ያሰበው ሁሉ ከንቱ ሆኖ ሲቀርበት ስለድርድር እየጮኸ ነው ያሉት አቶ ታዬ ደንደኣ፣ የቡድኑን የእንደራደር ጩኸት በሁለት መልኩ ማየት የተሻለ ነው ብለዋል። አንደኛውና ዋናው የዚህችን አገር ሕገ መንግስት ከጣሰ፤ የዚህችን አገር ሉዓላዊነት ከደፈረ ጁንታ ቡድን ጋር በምንም አይነት መልኩ ድርድር የሚቀመጥ አካል ሊኖር አይችልም።
ድርድር ሲታሰብ መጀመሪያ ከሕግ በታች በተለይም ከሕገ መንግስት በታች ባለው ነገር ላይ መሆን አለበት። መከላከያን ያጠቃ፤ የዚህችን አገር የሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን፣ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ነጻነትና ክብር የሚንጸባረቅበት ተቋምን ለማፍረስ ይሄን አይነት ተንኮል የሸረበ ሴረኛ ጋር በፍጹም ድርድር አያስፈልግም ብለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42094
‹‹ጁንታው የህወሓት ቡድን የፈጸመው ተግባር የውጭ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ነው›› - አርቲስት ደበበ እሸቱ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው የህወሓት ቡድን በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የክህደት ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም የሀገሪቱን ህዝቦች ለማንበርከክ የሞከሩ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ተግባር መሆኑን አርቲስት ደበበ እሸቱ አስታወቀ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ ጁንታው የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ትቃት አስመልክቶ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቀው ፤ ከሃዲው ቡድን ለ21 ዓመታት ክልሉንና ህዝቡን ሲጠብቅ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመው ጥቃት የከሃዲነት ተግባር ከመሆኑም ባሻገር ትውልድም ይቅር የማይለው ነው።
‹‹ተስፋ የቆረጠ ሰው ብዙ ነገር ያደርጋል። ተስፋ ባይቆርጥ ኖሮ፣ አብሮት ሲሰራና አብሮት ሲበላ የቆየ ወንድሙን አይገድልም ነበር። መከላከያ ሠራዊቱ ከኋላዬም ከፊቴም ያለው የራሴው ወገን ነው ብሎ ወገኑን ተማምኖ በተኛበት በሌሊት ክህደት መፈጸሙ ቡድኑ የመጨረሻ ዘመኑ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ።
“አርቲስት ደበበ እንደሚለው፤ የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የፈፀመው ክህደትና ጭካኔ የውጭ አገር ጠላትና ወራሪ እንኳን ያላደረገው ነው። ጣሊያን አላደረገውም፣ ደርቡሾች አላደረጉትም፣ እንግሊዞች ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስን ለመያዝ በመጡበት ጊዜ እንዲህ አይነት አፀያፊ ድርጊት አልፈጸሙም። የራሳችን ወገን የተባለው ግን እንዲህ አይነት ዘግናኝ ድርጊት ፈጸመ። የሠራዊቱ አባላት ሲወጣ ‹‹ለማን ጥላችሁን ነው የምትሄዱ፣ እባካችሁ ቆዩልን›› ያለ አካል ይሄን ክህደት መፈጸሙ የግድያ ቀን እያመቻቸ ነበር ማለት ነው።
ሠራዊቱ ይህ ክህደት እንደሚፈጸምበት ቢያውቅ ጥሪውን ሳይቀበል ይወጣ ነበር። የወገን ጥሪ ሆኖበት ግን ቆይልኝ ሲባል እዚያው ቆየ። ወገን በወገኑ ላይ እንዲህ ሲጨክን ቅስም ይሰብራል።ኢትዮጵያዊ መሆኑንም እንድንጠራጠር አድርጎናል ብሏል።
‹‹እንዲህ አይነት የአውሬነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች ነበሩ ለካ ሲመሩን የቆዩት›› ያለው አርቲስት ደበበ፤ እነዚህ ሰዎች የፈጸሙት አጸያፊ ተግባርም መላውን ኢትዮጵያዊ ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑንም ጠቁሟል።
እንደ አርቲስት ደበበ አስተያየት፤ ጁንታው የህወሓት ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት ለጥፋት የሚሆኑትን ገንዘብና ሌሎች ነገሮችን ቢያከማችም ሊያዛልቀው ግን አይችልም። አቅም ይሳነዋል። አሁን ላይ ማድረግ የሚችለው የመሰረተ ልማት ውጤቶችን ማውደም ብቻ ነው። ከአዲስ አበባ ጋር ግንኙነቱ ስለተቋረጠ የገንዘብ ምንጩም ይደርቃል። እስከ አሁን ግን ከዚህ በፊት በሰበሰበው ገንዘብ አፈ ቀላጢዎችን ቀጥሮ በውጭ መገናኛ ብዙኃን ብዙ እያስወራ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=42138
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጁንታው የህወሓት ቡድን በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ጥቃት የክህደት ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም የሀገሪቱን ህዝቦች ለማንበርከክ የሞከሩ ወራሪዎች እንኳን ያልፈጸሙት ተግባር መሆኑን አርቲስት ደበበ እሸቱ አስታወቀ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ ጁንታው የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ትቃት አስመልክቶ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቀው ፤ ከሃዲው ቡድን ለ21 ዓመታት ክልሉንና ህዝቡን ሲጠብቅ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመው ጥቃት የከሃዲነት ተግባር ከመሆኑም ባሻገር ትውልድም ይቅር የማይለው ነው።
‹‹ተስፋ የቆረጠ ሰው ብዙ ነገር ያደርጋል። ተስፋ ባይቆርጥ ኖሮ፣ አብሮት ሲሰራና አብሮት ሲበላ የቆየ ወንድሙን አይገድልም ነበር። መከላከያ ሠራዊቱ ከኋላዬም ከፊቴም ያለው የራሴው ወገን ነው ብሎ ወገኑን ተማምኖ በተኛበት በሌሊት ክህደት መፈጸሙ ቡድኑ የመጨረሻ ዘመኑ ላይ መድረሱን የሚያመላክት ነው ።
“አርቲስት ደበበ እንደሚለው፤ የህወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የፈፀመው ክህደትና ጭካኔ የውጭ አገር ጠላትና ወራሪ እንኳን ያላደረገው ነው። ጣሊያን አላደረገውም፣ ደርቡሾች አላደረጉትም፣ እንግሊዞች ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስን ለመያዝ በመጡበት ጊዜ እንዲህ አይነት አፀያፊ ድርጊት አልፈጸሙም። የራሳችን ወገን የተባለው ግን እንዲህ አይነት ዘግናኝ ድርጊት ፈጸመ። የሠራዊቱ አባላት ሲወጣ ‹‹ለማን ጥላችሁን ነው የምትሄዱ፣ እባካችሁ ቆዩልን›› ያለ አካል ይሄን ክህደት መፈጸሙ የግድያ ቀን እያመቻቸ ነበር ማለት ነው።
ሠራዊቱ ይህ ክህደት እንደሚፈጸምበት ቢያውቅ ጥሪውን ሳይቀበል ይወጣ ነበር። የወገን ጥሪ ሆኖበት ግን ቆይልኝ ሲባል እዚያው ቆየ። ወገን በወገኑ ላይ እንዲህ ሲጨክን ቅስም ይሰብራል።ኢትዮጵያዊ መሆኑንም እንድንጠራጠር አድርጎናል ብሏል።
‹‹እንዲህ አይነት የአውሬነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች ነበሩ ለካ ሲመሩን የቆዩት›› ያለው አርቲስት ደበበ፤ እነዚህ ሰዎች የፈጸሙት አጸያፊ ተግባርም መላውን ኢትዮጵያዊ ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑንም ጠቁሟል።
እንደ አርቲስት ደበበ አስተያየት፤ ጁንታው የህወሓት ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየባቸው ዓመታት ለጥፋት የሚሆኑትን ገንዘብና ሌሎች ነገሮችን ቢያከማችም ሊያዛልቀው ግን አይችልም። አቅም ይሳነዋል። አሁን ላይ ማድረግ የሚችለው የመሰረተ ልማት ውጤቶችን ማውደም ብቻ ነው። ከአዲስ አበባ ጋር ግንኙነቱ ስለተቋረጠ የገንዘብ ምንጩም ይደርቃል። እስከ አሁን ግን ከዚህ በፊት በሰበሰበው ገንዘብ አፈ ቀላጢዎችን ቀጥሮ በውጭ መገናኛ ብዙኃን ብዙ እያስወራ ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=42138
ኦነግ ሸኔ እየተሽመደመደ መምጣቱ ተገለጸ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው የህወሓት ቡድን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ የሚደረግለትና ህዝብን በማሸበር ላይ በሚገኘው የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በቡድኑ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገለጸ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ እንደገለፁት፤ጁንታው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ የኦሮሚያ ክልልን ፀጥታ ለማደፍረስ በተናበበ መንገድ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡
በዚህ እኩይ ተግባራቸው ክልሉን እየበጠበጡት ዜጎችን ሲያፈናቅሉ መቆየታቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ የክልሉ መንግሥት ህግን ለማስከበር በጀመረው እርምጃ የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ቡድኑ ህዝቡን ከማስፈራራትና አልፎ አልፎ በአንዳንድ አካባቢዎች ድንገተኛ ጥቃት ከማድረስ በዘለለ እንደፈለገው መፈንጨት ከማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል ።
የኦነግ ሸኔ አሸባሪዎች እኩይ ሴራቸውን ለመከወን ህዝብ ውስጥ የተደበቁ መሆናቸውን አመልክተው፣ ህዝቡን በእምነትና በብሄር ለማጋጨት የወጠኑት ሥራ ሰፊ ቢሆንም በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉ የተቀናጀ ሥራ መክሸፉን አስታውቀዋል።
ቡድኑን በተለይም ከኦሮሚያ ክልል ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት በሰፊው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ፣ለዚህም በአሁኑ ወቅትም ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ስለ ቡድኑ እኩይ ተግባር ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራሉ ፣የኦነግ ሸኔ አባላትም ባገኙት አጋጣሚ ዘረፋ እያካሄዱ ሃብት ለማካበት እየሞከሩ ነው፡፡ ይሁንና የክልሉን የሚሊሻ ኃይል በማጠናከር እና ከህብረተሰቡ ጋር በተናበበ መንገድ በመስራት ዘራፊውን ቡድን የማጋለጥ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=42139
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በጁንታው የህወሓት ቡድን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ የሚደረግለትና ህዝብን በማሸበር ላይ በሚገኘው የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በቡድኑ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገለጸ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ እንደገለፁት፤ጁንታው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ የኦሮሚያ ክልልን ፀጥታ ለማደፍረስ በተናበበ መንገድ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡
በዚህ እኩይ ተግባራቸው ክልሉን እየበጠበጡት ዜጎችን ሲያፈናቅሉ መቆየታቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ የክልሉ መንግሥት ህግን ለማስከበር በጀመረው እርምጃ የኦነግ ሸኔ ቡድን እየተሽመደመደ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ቡድኑ ህዝቡን ከማስፈራራትና አልፎ አልፎ በአንዳንድ አካባቢዎች ድንገተኛ ጥቃት ከማድረስ በዘለለ እንደፈለገው መፈንጨት ከማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል ።
የኦነግ ሸኔ አሸባሪዎች እኩይ ሴራቸውን ለመከወን ህዝብ ውስጥ የተደበቁ መሆናቸውን አመልክተው፣ ህዝቡን በእምነትና በብሄር ለማጋጨት የወጠኑት ሥራ ሰፊ ቢሆንም በህዝቡና በጸጥታ ኃይሉ የተቀናጀ ሥራ መክሸፉን አስታውቀዋል።
ቡድኑን በተለይም ከኦሮሚያ ክልል ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት በሰፊው እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ፣ለዚህም በአሁኑ ወቅትም ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ስለ ቡድኑ እኩይ ተግባር ግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራሉ ፣የኦነግ ሸኔ አባላትም ባገኙት አጋጣሚ ዘረፋ እያካሄዱ ሃብት ለማካበት እየሞከሩ ነው፡፡ ይሁንና የክልሉን የሚሊሻ ኃይል በማጠናከር እና ከህብረተሰቡ ጋር በተናበበ መንገድ በመስራት ዘራፊውን ቡድን የማጋለጥ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡
https://www.press.et/Ama/?p=42139
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል እየተወሰደ ያለው ህግን የማስከበር እርምጃ እንደሚደግፍ ኢዜማ አስታወቀ
*********************
(ኢ ፐ ድ)
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ የሚደገፍ መሆኑንኢዜማ አስታወቀ ። ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ እኩይ መልእክቶችን በመመልከት የትግራይ ተወላጅ ወንድሞቻችን ከመሸማቀቅ ይልቅ አብሮ በመቆም ቀኑን ማሳለፍ እንደሚገባ ገለጸ ።
ኃላፊው አቶ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት ፣ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጋር በተያያዘ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውን የትግራይን ህዝበ ለመጠበቅ ኑሮውን እዛ ያደረገ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀም ከክህደት ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም ።
ከህዝቡ ጋር በሰላም የኖረ የህዝብ ልጅ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊትን ማጥቃት ተገቢ አለመሆኑን ያመለከቱት አቶ ዘላለም፣ ኢዜማ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የህግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት ያሳየው ትእግስት ጦርነት የሚያስከ ትለውን ጉዳት በማሰብ ቢሆንም የአንድነት፣ የሉአላዊነት እና የህልውና ምልክት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝም ማለት አለበት ብሎ ኢዜማ አያምንም ብለዋል። ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለውን እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል።
“የትግራይ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው፤ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በሰላም መኖር የሚያውቅበት፤ የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ የአስተዳደር ስርአት የሚያውቅ ህዝብ ነው” ያሉት አቶ ዘላለም “ ጦርነቱ የሚያመጣውን ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ጫና ለመቅረፍ መልሶ የማቋቋም ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በፈጸመው ጥፋት በሱላይ ሊመጣ የሚችል አደጋ ባለመኖሩ ሊሰጋ እንደማይገባ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42148
*********************
(ኢ ፐ ድ)
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለው ህግ የማስከበር እርምጃ የሚደገፍ መሆኑንኢዜማ አስታወቀ ። ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ እኩይ መልእክቶችን በመመልከት የትግራይ ተወላጅ ወንድሞቻችን ከመሸማቀቅ ይልቅ አብሮ በመቆም ቀኑን ማሳለፍ እንደሚገባ ገለጸ ።
ኃላፊው አቶ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት ፣ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጋር በተያያዘ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውን የትግራይን ህዝበ ለመጠበቅ ኑሮውን እዛ ያደረገ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀም ከክህደት ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም ።
ከህዝቡ ጋር በሰላም የኖረ የህዝብ ልጅ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊትን ማጥቃት ተገቢ አለመሆኑን ያመለከቱት አቶ ዘላለም፣ ኢዜማ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የህግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት ያሳየው ትእግስት ጦርነት የሚያስከ ትለውን ጉዳት በማሰብ ቢሆንም የአንድነት፣ የሉአላዊነት እና የህልውና ምልክት የሆነው መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝም ማለት አለበት ብሎ ኢዜማ አያምንም ብለዋል። ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠልም እየተወሰደ ያለውን እርምጃ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል።
“የትግራይ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው፤ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በሰላም መኖር የሚያውቅበት፤ የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ የአስተዳደር ስርአት የሚያውቅ ህዝብ ነው” ያሉት አቶ ዘላለም “ ጦርነቱ የሚያመጣውን ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ጫና ለመቅረፍ መልሶ የማቋቋም ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል። የትግራይ ህዝብ ቡድኑ በፈጸመው ጥፋት በሱላይ ሊመጣ የሚችል አደጋ ባለመኖሩ ሊሰጋ እንደማይገባ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=42148
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ልዑካን አማካኝነት ከህወሓት ቡድን ጋር ድርድር ሊያደረጉ ነዉ የሚለው መረጃ ሐሰተኛ ነዉ::
************
(ኢፕድ)
የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ላይ እንደተጠቀሰው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሲሪል ራማፎሳ ልዑካኖችን በመቀበል ታነጋገራለች:: ይህ የልዑካን ቡድኑን መቀበል እና የማነጋገር ሂደት በየተናጠል ከልዑካን ቡድኑ አባላት ጋር ብቻ የሚካሄድ ነዉ::
መልእክተኞቹ የፌዴራል መንግስትን ክህወሓት ጁንታ ጋር ለማስታረቅ ወደ ኢትዮጵያ ይግዋዛሉ በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰተኛ ነዉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ ማስከበር ርምጃው ላይ ድርድር የማይታሰብ መሆኑን ግልፅ ማደረጋቸውም ይታወሳል::
************
(ኢፕድ)
የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ላይ እንደተጠቀሰው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሲሪል ራማፎሳ ልዑካኖችን በመቀበል ታነጋገራለች:: ይህ የልዑካን ቡድኑን መቀበል እና የማነጋገር ሂደት በየተናጠል ከልዑካን ቡድኑ አባላት ጋር ብቻ የሚካሄድ ነዉ::
መልእክተኞቹ የፌዴራል መንግስትን ክህወሓት ጁንታ ጋር ለማስታረቅ ወደ ኢትዮጵያ ይግዋዛሉ በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰተኛ ነዉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ ማስከበር ርምጃው ላይ ድርድር የማይታሰብ መሆኑን ግልፅ ማደረጋቸውም ይታወሳል::
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደነበረ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ
******************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እንደነበረና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደሆነ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ።
የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ኢትዮጵያ ለገባችበት ችግር ዘራፊው ህወሓት እና የእሱ ወዳጆች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ላይ ራሳቸው የበላይ በማድረጋቸው እና በአገሪቱም “ሀሰተኛ” የፌዴራል ስርዓት በመመስረታቸው ነው ብለዋል።
በ 1991 በጎሳዎች ላይ የተመሠረተ የክልሎች ስርዓት በኢትዮጵያ የተቋቋመ ቢሆንም ስርዓቱ የውሸት በመሆኑ ከትግራይ ውጪ ያሉ ክልሎች አንዳቸውም ቢሆኑ በአገሪቱ ላይ የመወሰን መብት አልነበራቸውም ያሉት ኸርማን ኮኸን፤ ሂደቱ የአንድ ፓርቲ የበላይነትን ያነገሰበት ከበርካታ ዓመታት በፊት በአፍሪካ ተሞክሮ የወደቀ አካሄድን የተከተለ ነው ብለዋል።
ጥቂት የህወሓት አባላት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ብቻቸውን በበላይነት በመቆጣጠራቸው ምክንያት ጥቅማ ጥቅሞችን ለእነርሱና እነርሱን ለሚመስሏቸው ብቻ ሲያደርጉ መኖራቸውን የጠቀሱት ኸርማን ኮኸን ፤ በዚህም ምክንያት ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጫና ተፈጥሮባቸዋል፤ የመሰረተ ልማትም ፍትሃዊነት በጎደለው መልኩ ለራሳቸው አድርገውታል፤ ይህ አይነት አካሄድ በሌሎች ላይ ቁጭትና ጫና ፈጥሮባቸዋል ብለዋል አምባሳደሩ።
ይሄንን አይነት በደለን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነትን ተቃውመው ሰልፍ በሚወጡ ባልታጠቁ ሰልፈኞች ላይ የህወሃት ኃይል የሚወስዳቸው እርምጃዎችም ያልተመጣጠነ እንደነበር ኸርማን ኮኸን አብራርተዋል።
ይህን ሁሉ የሰብጻዊ መብት ጥሰት ይፈጽም ለነበረ አካል አሜሪካ ለምንድን ነበር የምትደግፈው ተብለው የተጠየቁት አምባሳደሩ፤ “ ስትራቴጂካዊ ፍላጎታችንን ለማሟላት ስንል ይህን ታግሰናል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
******************
(ኢ ፕ ድ)
ላለፉት 27 አመታት የተተገበረው ፌዴራሊዝም የውሸት እንደነበረና የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት እንደሆነ የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ተናገሩ።
የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ኸርማን ኮኸን ኢትዮጵያ ለገባችበት ችግር ዘራፊው ህወሓት እና የእሱ ወዳጆች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ላይ ራሳቸው የበላይ በማድረጋቸው እና በአገሪቱም “ሀሰተኛ” የፌዴራል ስርዓት በመመስረታቸው ነው ብለዋል።
በ 1991 በጎሳዎች ላይ የተመሠረተ የክልሎች ስርዓት በኢትዮጵያ የተቋቋመ ቢሆንም ስርዓቱ የውሸት በመሆኑ ከትግራይ ውጪ ያሉ ክልሎች አንዳቸውም ቢሆኑ በአገሪቱ ላይ የመወሰን መብት አልነበራቸውም ያሉት ኸርማን ኮኸን፤ ሂደቱ የአንድ ፓርቲ የበላይነትን ያነገሰበት ከበርካታ ዓመታት በፊት በአፍሪካ ተሞክሮ የወደቀ አካሄድን የተከተለ ነው ብለዋል።
ጥቂት የህወሓት አባላት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ብቻቸውን በበላይነት በመቆጣጠራቸው ምክንያት ጥቅማ ጥቅሞችን ለእነርሱና እነርሱን ለሚመስሏቸው ብቻ ሲያደርጉ መኖራቸውን የጠቀሱት ኸርማን ኮኸን ፤ በዚህም ምክንያት ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጫና ተፈጥሮባቸዋል፤ የመሰረተ ልማትም ፍትሃዊነት በጎደለው መልኩ ለራሳቸው አድርገውታል፤ ይህ አይነት አካሄድ በሌሎች ላይ ቁጭትና ጫና ፈጥሮባቸዋል ብለዋል አምባሳደሩ።
ይሄንን አይነት በደለን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነትን ተቃውመው ሰልፍ በሚወጡ ባልታጠቁ ሰልፈኞች ላይ የህወሃት ኃይል የሚወስዳቸው እርምጃዎችም ያልተመጣጠነ እንደነበር ኸርማን ኮኸን አብራርተዋል።
ይህን ሁሉ የሰብጻዊ መብት ጥሰት ይፈጽም ለነበረ አካል አሜሪካ ለምንድን ነበር የምትደግፈው ተብለው የተጠየቁት አምባሳደሩ፤ “ ስትራቴጂካዊ ፍላጎታችንን ለማሟላት ስንል ይህን ታግሰናል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬ ከተማ ከገባ በኋላ ከችግርና ውጥረት ታድጎናል- የሽሬ ከተማ ነዋሪዎች
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣ አድርጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የህወሃት ቡድን ቀደም ሲል በክልሉ "ወራሪ፣ ዘራፊና የትግራይን ህዝብ የሚያጠፋ ሃይል እየመጣ ነው" በሚል ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጭ ነበር ይላሉ ነዋሪዎቹ።
በዚህም በርካቶች ፍርሃት አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ግን እውነታውን ተረድተነዋል ብለዋል።
ሰራዊቱ ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ብዙዎቻችን ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ወጥተን ወደ ሰላማዊ ህይወት ገብተናል ነው ያሉት።
ህወሃት ሲያሰራጨው በነበረው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ፍራቻ አድሮብን የነበረ ቢሆንም፤ ሰራዊቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር ህዝባዊነቱንና አብሮነቱን አሳይቶናል ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂ ቡድን ከሽሬ በመውጣቱ ከተማዋ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷንና የተለያዩ አገልግሎቶችም መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት በሽሬ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የከተማዋን ነዋሪዎችን ሰብስቦ በማናገሩም ተደስተናል ብለዋል።
ሰራዊቱ ክልሉን ከዘራፊዎችና ግለኞች ነፃ በማውጣት የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የመጣ መሆኑንም ተረድተናል ነው ያሉት።
በህወሃት ካድሬዎች ፕሮፓጋንዳ ከአካባቢው ርቀው የነበሩ የከተማዋ ነዋሪዎችም ሰላም መሆኑን በመረዳት ወደ ቤታቸው እየተመለሱ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝቡ ንብረት በዘራፊዎች አንዳይወሰድ የአገር መከላከያ ሰራዊት የተቆጣጠረባቸው አካባቢዎች ላይ ጥብቅ ጥበቃና ክትትል በማድረጉም ተደስተናል ብለዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ተላቀናል በቀጣይ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ሰላማችንን እናስጠብቃለን ሲሉም ነው የተናገሩት።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች አሁን ላይ ለሰራዊቱ መረጃ በመስጠትና የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ፍቅሩን አሳይቶናል፣ አረጋግቶናል፣ ህወሃት ከፈጠረብን ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣም አድርጎናል በማለት ገልጸዋል።
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣ አድርጎናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የህወሃት ቡድን ቀደም ሲል በክልሉ "ወራሪ፣ ዘራፊና የትግራይን ህዝብ የሚያጠፋ ሃይል እየመጣ ነው" በሚል ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጭ ነበር ይላሉ ነዋሪዎቹ።
በዚህም በርካቶች ፍርሃት አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ግን እውነታውን ተረድተነዋል ብለዋል።
ሰራዊቱ ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ብዙዎቻችን ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ወጥተን ወደ ሰላማዊ ህይወት ገብተናል ነው ያሉት።
ህወሃት ሲያሰራጨው በነበረው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ፍራቻ አድሮብን የነበረ ቢሆንም፤ ሰራዊቱ ከተማዋን ሲቆጣጠር ህዝባዊነቱንና አብሮነቱን አሳይቶናል ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂ ቡድን ከሽሬ በመውጣቱ ከተማዋ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷንና የተለያዩ አገልግሎቶችም መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት በሽሬ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የከተማዋን ነዋሪዎችን ሰብስቦ በማናገሩም ተደስተናል ብለዋል።
ሰራዊቱ ክልሉን ከዘራፊዎችና ግለኞች ነፃ በማውጣት የህዝብን ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የመጣ መሆኑንም ተረድተናል ነው ያሉት።
በህወሃት ካድሬዎች ፕሮፓጋንዳ ከአካባቢው ርቀው የነበሩ የከተማዋ ነዋሪዎችም ሰላም መሆኑን በመረዳት ወደ ቤታቸው እየተመለሱ መሆኑን ገልጸዋል።
የህዝቡ ንብረት በዘራፊዎች አንዳይወሰድ የአገር መከላከያ ሰራዊት የተቆጣጠረባቸው አካባቢዎች ላይ ጥብቅ ጥበቃና ክትትል በማድረጉም ተደስተናል ብለዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ሽሬን ከተቆጣጠረ በኋላ ከችግር፣ ውጥረትና ፍርሃት ተላቀናል በቀጣይ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን ሰላማችንን እናስጠብቃለን ሲሉም ነው የተናገሩት።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች አሁን ላይ ለሰራዊቱ መረጃ በመስጠትና የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
የአገር መከላከያ ሰራዊት ፍቅሩን አሳይቶናል፣ አረጋግቶናል፣ ህወሃት ከፈጠረብን ውጥረትና ፍርሃት አንድንወጣም አድርጎናል በማለት ገልጸዋል።