የሶስቱ ቀናት ፈታኝ ተጋድሎ በጀኔራሉ አንደበት
****************************
(ኢ ፕ ድ)
ዳንሻ ከተማ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ካምፕ ጊቢ ውስጥ የመከላከያ መኪናዎች በጥይት ተበሳስተው ይታያሉ፡፡መስታወታቸው ረግፏል፤ዛፎቹም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፤ መጥረቢያ እንጂ የጥይት ውርጅብኝ የቆረጣቸው አይመስሉም።የግንብና ቆርቆሮ ቤቶች እንደ ወንፊት ተበሳስተዋል፡፡የጥይቶች ቀላሃ እንደ ጠጠር ተብትኗል፡፡
ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በዳንሻ ከተማ ያልተጠበቀ፣አሳዛኝ፣አስደጋጭ ድርጊት ነው የተፈጸመው፡፡በከተማዋ የሚገኘው የሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር የተደገሰለትን ጥቃት አያውቅም።በመካናይዝድ ክፍለ ጦሩ ስታፍ ውስጥ የሚሰሩት መደበኛ ስራቸውን ከውነው እንቅልፍ ላይ ናቸው፡፡
በዚህ ምሽት ግን የትግራይ ልዩ ሀይል አባላት ወደ ካምፑ ዘለቁ፤ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱን እንደሚፈልጉትና እንዲጠራላችሁ የበር ጥበቃዎችን ይጠይቃሉ።ጀኔራሉም እንደማይመጡ ሲነገራቸው ተመልሰው ይሄዱና ተጨማሪ
ሀይል ይዘው መጥተው በካምፑ ላይ የጥይት መአት ማውረድ ይጀምራሉ፡፡ውስጥ የነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላትም በጽናት የመመከት ስራ ውስጥ ገቡ፤ለሶስት ቀንና ሌሊት በጽናት ታገሉ፡፡
አንድ የመከላከያ ሰራዊት የመረጃ ሰራተኛ ወደ ጀነራሉ ጆሮ ተጠግቶ አካባቢውን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ከቦታል፡፡ፍላጎት ካለህ ሽማግሌዎቹ ከአካባቢው እናስወጣው ብለው ነግረውኛል፤ ውሳኔህ ምንድነው ሲል ጠየቀኝ ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ፣ የእነሱ ፍላጎት እኔም ወኔዬን ተሰልቤ የሲቪል ልብስ ለብሼ ተደብቄ ወደ አማራ ክልል እንድወጣ አልያም እኔን አታለው እንድያዝ በማድረግ ካምፕ ውስጥና በአቅራቢያው ባለው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ለመሰንዘር ያቀዱትን ጥቃት የመከላከልና የመመከት ስራ ለማሰናከል ነው፡፡በዚህም በቀላሉ ሰራዊቱንና መሳሪያውን በቁጥጥር ስር ለማዋል አስበው መሆኑን ገለጹልን፡፡
እኔም ምላሼ ሽምግልናውን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን የመረጃ ሰራተኛው ከሽማግሌዎቹ ጋር ለጥሩም ይሁን ለመጥፎ መገናኘት እንደሌለበት አስጠንቅቄ ነገርኩት ።አሁን ይህን ያለኝ ልጅ ቆስሎ ለህክምና ወደ ጎንደር ሄዷል።ሲመጣ ጠይቄ ዓላማቸው ምን እንደነበር የምረዳው ይሆናል፡፡ተመትቶ ስለነበረ እኔም እንዳልሞት አስቦ ይሆናል የሚል ግምት አለኝ ብለውናል።
የሶስት ቀን ከበባው በጣም አስቸጋሪ ነበር።24 ሰዓት ተኩስ ነው፡፡ያጠቃሉ እኛ እንከላከላለን፤ይሄዱና ምግብ በልተው ሀይል ጨምረው ያጠቃሉ፤ሲታኩሱ የነበሩት ልዩ ሀይሎች ወደ ካምፓቸው ሄደው አርፈውና ጥይት ጭነው ይመጣሉ፡፡እኛ ካለንበት ቦታ ውጭ መፈናፈኛ ስፍራ የለንም፡፡እንደ ቀለበት ዙሪያውን ከበውና ውሃ ፣ምግብ፣ጥይት የለም፡፡ያለችንን ነው በቁጠባ የምንጠቀመው ሲሉ ያብራሩት ጀነራሉ፣እኔም አልፎ አልፎ እንደ ምሽግ ከተጠቀምኩበት ግንብ ቤት እየወጣሁ ለወታደሮቼ ጥይት በቁጠባ ተጠቀሙ እያልኩ አሳስብ ነበር ሲሉ ይገልጻሉ፡፡እነሱም አላሳፈሩኝም በጽናት ተዋደቁ።የሰራዊታችን በጽናት የመከላከል ሞራል የሚገርም፣ የሚደነቅና ታምር የሚያስብል ነው ይላሉ፡፡
አርቢጂ፣ቦንብ፣መትረየስ ፤ክላሽ እንደ ዝናብ ቢያርከፈክፉብንም ለሶስት ቀናት ቀንና ሌሊት መክተናል፡፡በፍጹም እንተርፋለን ብለን አላሰብነም ፤ከቻልን እስከ መጨረሻው እንከላከላለን ፤ካልቻልን ደግሞ በመጨረሻ ላይ ራሳችንን እናጠፋለን የሚል አቋም ነበርን፡፡ግን በእግዜአብሄር ቸርነት፤በመከላከያ ሰራዊት ፈጥኖ ደራሽነት ቀለበቱ ተሰብሮ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል ብለውናል፡፡ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም፡፡
ድርጊቱ የሚያሳዝን ነው፤ በህወሓት ከሀዲ ቡድን እንዲህ አይነት ጥቃት ይፈጸምብናል ብለን አስበን፤አልምንም አናውቅም የሚሉት በሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱ፤ ምክንያቱም ከኢትዮ-ኢርትራ ጦርነት ጀምሮ ትግራይ መሬት ነው እየኖርን ያለው።ህዝቡን መሪዎቹንም በደንብ እናውቃቸዋለን ብለዋል፡፡
“አብረህ እየበላህ እየጠጣህ፣ተዋልደህ ተጋምደህ፤ ትዳር መስርተህ ፣ልጆች ወልደህ፤ቤተሰብ ሆነህ በፍጹም ጥቃት ሊሰነዝርብኝ ይችላሉ ብለህ አታስብም፤ሆኖም ያልታሰበው ተፈጸመ፤ያልተጠበቀው ሆነ “ሲሉ በትግራይ ክልል ልዩ ሀይል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት አሳዛኝ ሲሉ ይገልጹታል።
ኩርፊያና የተለያዩ መገለጫዎች ይታያሉ ፡፡ይህን ተከትሎ ጥርጣሬዎች ቢኖሩም ደፍረው መከላከያ ሰራዊት ካምፕ ውስጥ ገብተው ያጠቃሉ ብለን አላሰብንም።ምክንያቱም ወንድምህ ሊያኮርፍ ይችላል እንጂ ያጠቃኛል፤ይገለኛል ብለህ ፈጸሞ አትገምትም የሚሉት ብርጋዴር ጀኔራሉ፤ግን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ዕለተ ማክሰኞ 25ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ያለምንም ርህራሄ ዙሪያውን እንደ ቀለበት ከበውን አጠቁን ፣አጠቁን እኛም በጽናት ተከላከልን፤መከትን ብለዋል፡፡
የህወሓት ቡድን ዓላማ የመከላከያ ሰራዊትን መድፎች፣ ታንኮች፣ብረት ለበሶችን መንጠቅና መከላከያን ማፍረስ ነው፡፡ በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም ፤በራሳችን መሳሪያ ተመልሰው እኛን ለመውጋት ነበር ዕቅዳቸው፡፡ይህ አልተሳካላቸውም፡፡እኛም በያለንበት በጽናት ተዋግተን መክተናል፡፡አሁን እነሱ ባሰቡት ሳይሆን እኛ ባሰብነው መንገድ እየሄደ ነው፡፡በአጭር ጊዜ ውስጥ ጦርነቱ ይቋጫል ብለን እናስባለን ሲሉ ገልጸውልናል።
ብረጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንድ የሚገርማቸው የሚደንቃቸው ነገር አለ፡፡”እኔ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊና ተራ ጄነራል ነኝ፣በአንድ ክላሽ ጥይት ግፋ ቢል ደግሞ በስናይፐር መግደል ይችላሉ፤ ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ አርቢጂ ነው የተኮሱብን ።አርቢጂ የሚባለው መሳሪያ ደግሞ ለታንክ ወይም ለጠንካራ ምሽግ ነው የሚተኮሰው፤የእኔን ቤት ለማፍረስ ግን አርቢጂ ነው የተኮሱት ሲሉ የከሀዲው ቡድን የጭካኔ ጥግ ምን ያህል እንደሆነ ይናገራሉ ፡፡
እኔ ብሞትም ቤቱ የእነሱና የህዝቡ ንብረት ነው። ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ጸጥታ ለቆምኩ፣ለአገር ሉዋላዊነትና ለህዝብ ሰላም ውድ ህይወቴን ለመስጠት በተሰለፍኩ የክህደታቸው፣የክፋታቸው ጥልቀት እኔን በአርቢጂና በቦንብ ነው ያጠቁት ሲሉ የድርጊቱን ክፋት ገልጸውታል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ህዝብ ጋር አብሮ እየኖረ ያለ፣ለህዝቡ የልማት ስራዎች ወደ ኋላ የማይል፣ በማህበራዊ ድጋፎች የሚሳተፍ፣ ሁልጊዜ በየዓመቱ ለአቅመ ደካሞች የሚያርስ፣የሚያርም፣የሚያጭድና አንበጣ የሚከላከል ነው። በትምህርት ቤቶች፣በጤና ጣቢያዎች፣በመንገድ ግንባታዎች በሚሳተፍ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈጸም የህወሓት ቡድን እወክለዋለሁ ቆሜለታለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ እንደሌለው ያሳያል ይላሉ፡፡
የአገሩን ዳር ድንበር የሚጠብቀውን፤የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች ስብስብ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊት ለማውድምና ለማጥፋት ነው ጥቃቱን የሰነዘሩት ፡፡እነዚህ ሰዎች ከዚህ በኋላ ስለኢትዮጵያዊነት፣ብሄሮች ፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቢሰብኩ፣ቢለፈልፉ፣ቢቀሰቅሱ ማን ጀሮ ይሰጣቸዋል ፡፡ምክንያቱም ጥቃቱን በጽናት ለመመከት የተዋደቁት ከኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የተወጣጡ ወታደሮች ናቸው ብለዋል፡፡
****************************
(ኢ ፕ ድ)
ዳንሻ ከተማ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ካምፕ ጊቢ ውስጥ የመከላከያ መኪናዎች በጥይት ተበሳስተው ይታያሉ፡፡መስታወታቸው ረግፏል፤ዛፎቹም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፤ መጥረቢያ እንጂ የጥይት ውርጅብኝ የቆረጣቸው አይመስሉም።የግንብና ቆርቆሮ ቤቶች እንደ ወንፊት ተበሳስተዋል፡፡የጥይቶች ቀላሃ እንደ ጠጠር ተብትኗል፡፡
ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በዳንሻ ከተማ ያልተጠበቀ፣አሳዛኝ፣አስደጋጭ ድርጊት ነው የተፈጸመው፡፡በከተማዋ የሚገኘው የሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር የተደገሰለትን ጥቃት አያውቅም።በመካናይዝድ ክፍለ ጦሩ ስታፍ ውስጥ የሚሰሩት መደበኛ ስራቸውን ከውነው እንቅልፍ ላይ ናቸው፡፡
በዚህ ምሽት ግን የትግራይ ልዩ ሀይል አባላት ወደ ካምፑ ዘለቁ፤ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱን እንደሚፈልጉትና እንዲጠራላችሁ የበር ጥበቃዎችን ይጠይቃሉ።ጀኔራሉም እንደማይመጡ ሲነገራቸው ተመልሰው ይሄዱና ተጨማሪ
ሀይል ይዘው መጥተው በካምፑ ላይ የጥይት መአት ማውረድ ይጀምራሉ፡፡ውስጥ የነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላትም በጽናት የመመከት ስራ ውስጥ ገቡ፤ለሶስት ቀንና ሌሊት በጽናት ታገሉ፡፡
አንድ የመከላከያ ሰራዊት የመረጃ ሰራተኛ ወደ ጀነራሉ ጆሮ ተጠግቶ አካባቢውን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ከቦታል፡፡ፍላጎት ካለህ ሽማግሌዎቹ ከአካባቢው እናስወጣው ብለው ነግረውኛል፤ ውሳኔህ ምንድነው ሲል ጠየቀኝ ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ፣ የእነሱ ፍላጎት እኔም ወኔዬን ተሰልቤ የሲቪል ልብስ ለብሼ ተደብቄ ወደ አማራ ክልል እንድወጣ አልያም እኔን አታለው እንድያዝ በማድረግ ካምፕ ውስጥና በአቅራቢያው ባለው የመከላከያ ሰራዊት ላይ ለመሰንዘር ያቀዱትን ጥቃት የመከላከልና የመመከት ስራ ለማሰናከል ነው፡፡በዚህም በቀላሉ ሰራዊቱንና መሳሪያውን በቁጥጥር ስር ለማዋል አስበው መሆኑን ገለጹልን፡፡
እኔም ምላሼ ሽምግልናውን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን የመረጃ ሰራተኛው ከሽማግሌዎቹ ጋር ለጥሩም ይሁን ለመጥፎ መገናኘት እንደሌለበት አስጠንቅቄ ነገርኩት ።አሁን ይህን ያለኝ ልጅ ቆስሎ ለህክምና ወደ ጎንደር ሄዷል።ሲመጣ ጠይቄ ዓላማቸው ምን እንደነበር የምረዳው ይሆናል፡፡ተመትቶ ስለነበረ እኔም እንዳልሞት አስቦ ይሆናል የሚል ግምት አለኝ ብለውናል።
የሶስት ቀን ከበባው በጣም አስቸጋሪ ነበር።24 ሰዓት ተኩስ ነው፡፡ያጠቃሉ እኛ እንከላከላለን፤ይሄዱና ምግብ በልተው ሀይል ጨምረው ያጠቃሉ፤ሲታኩሱ የነበሩት ልዩ ሀይሎች ወደ ካምፓቸው ሄደው አርፈውና ጥይት ጭነው ይመጣሉ፡፡እኛ ካለንበት ቦታ ውጭ መፈናፈኛ ስፍራ የለንም፡፡እንደ ቀለበት ዙሪያውን ከበውና ውሃ ፣ምግብ፣ጥይት የለም፡፡ያለችንን ነው በቁጠባ የምንጠቀመው ሲሉ ያብራሩት ጀነራሉ፣እኔም አልፎ አልፎ እንደ ምሽግ ከተጠቀምኩበት ግንብ ቤት እየወጣሁ ለወታደሮቼ ጥይት በቁጠባ ተጠቀሙ እያልኩ አሳስብ ነበር ሲሉ ይገልጻሉ፡፡እነሱም አላሳፈሩኝም በጽናት ተዋደቁ።የሰራዊታችን በጽናት የመከላከል ሞራል የሚገርም፣ የሚደነቅና ታምር የሚያስብል ነው ይላሉ፡፡
አርቢጂ፣ቦንብ፣መትረየስ ፤ክላሽ እንደ ዝናብ ቢያርከፈክፉብንም ለሶስት ቀናት ቀንና ሌሊት መክተናል፡፡በፍጹም እንተርፋለን ብለን አላሰብነም ፤ከቻልን እስከ መጨረሻው እንከላከላለን ፤ካልቻልን ደግሞ በመጨረሻ ላይ ራሳችንን እናጠፋለን የሚል አቋም ነበርን፡፡ግን በእግዜአብሄር ቸርነት፤በመከላከያ ሰራዊት ፈጥኖ ደራሽነት ቀለበቱ ተሰብሮ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል ብለውናል፡፡ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም፡፡
ድርጊቱ የሚያሳዝን ነው፤ በህወሓት ከሀዲ ቡድን እንዲህ አይነት ጥቃት ይፈጸምብናል ብለን አስበን፤አልምንም አናውቅም የሚሉት በሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱ፤ ምክንያቱም ከኢትዮ-ኢርትራ ጦርነት ጀምሮ ትግራይ መሬት ነው እየኖርን ያለው።ህዝቡን መሪዎቹንም በደንብ እናውቃቸዋለን ብለዋል፡፡
“አብረህ እየበላህ እየጠጣህ፣ተዋልደህ ተጋምደህ፤ ትዳር መስርተህ ፣ልጆች ወልደህ፤ቤተሰብ ሆነህ በፍጹም ጥቃት ሊሰነዝርብኝ ይችላሉ ብለህ አታስብም፤ሆኖም ያልታሰበው ተፈጸመ፤ያልተጠበቀው ሆነ “ሲሉ በትግራይ ክልል ልዩ ሀይል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት አሳዛኝ ሲሉ ይገልጹታል።
ኩርፊያና የተለያዩ መገለጫዎች ይታያሉ ፡፡ይህን ተከትሎ ጥርጣሬዎች ቢኖሩም ደፍረው መከላከያ ሰራዊት ካምፕ ውስጥ ገብተው ያጠቃሉ ብለን አላሰብንም።ምክንያቱም ወንድምህ ሊያኮርፍ ይችላል እንጂ ያጠቃኛል፤ይገለኛል ብለህ ፈጸሞ አትገምትም የሚሉት ብርጋዴር ጀኔራሉ፤ግን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ዕለተ ማክሰኞ 25ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ያለምንም ርህራሄ ዙሪያውን እንደ ቀለበት ከበውን አጠቁን ፣አጠቁን እኛም በጽናት ተከላከልን፤መከትን ብለዋል፡፡
የህወሓት ቡድን ዓላማ የመከላከያ ሰራዊትን መድፎች፣ ታንኮች፣ብረት ለበሶችን መንጠቅና መከላከያን ማፍረስ ነው፡፡ በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም ፤በራሳችን መሳሪያ ተመልሰው እኛን ለመውጋት ነበር ዕቅዳቸው፡፡ይህ አልተሳካላቸውም፡፡እኛም በያለንበት በጽናት ተዋግተን መክተናል፡፡አሁን እነሱ ባሰቡት ሳይሆን እኛ ባሰብነው መንገድ እየሄደ ነው፡፡በአጭር ጊዜ ውስጥ ጦርነቱ ይቋጫል ብለን እናስባለን ሲሉ ገልጸውልናል።
ብረጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንድ የሚገርማቸው የሚደንቃቸው ነገር አለ፡፡”እኔ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊና ተራ ጄነራል ነኝ፣በአንድ ክላሽ ጥይት ግፋ ቢል ደግሞ በስናይፐር መግደል ይችላሉ፤ ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ አርቢጂ ነው የተኮሱብን ።አርቢጂ የሚባለው መሳሪያ ደግሞ ለታንክ ወይም ለጠንካራ ምሽግ ነው የሚተኮሰው፤የእኔን ቤት ለማፍረስ ግን አርቢጂ ነው የተኮሱት ሲሉ የከሀዲው ቡድን የጭካኔ ጥግ ምን ያህል እንደሆነ ይናገራሉ ፡፡
እኔ ብሞትም ቤቱ የእነሱና የህዝቡ ንብረት ነው። ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ጸጥታ ለቆምኩ፣ለአገር ሉዋላዊነትና ለህዝብ ሰላም ውድ ህይወቴን ለመስጠት በተሰለፍኩ የክህደታቸው፣የክፋታቸው ጥልቀት እኔን በአርቢጂና በቦንብ ነው ያጠቁት ሲሉ የድርጊቱን ክፋት ገልጸውታል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ህዝብ ጋር አብሮ እየኖረ ያለ፣ለህዝቡ የልማት ስራዎች ወደ ኋላ የማይል፣ በማህበራዊ ድጋፎች የሚሳተፍ፣ ሁልጊዜ በየዓመቱ ለአቅመ ደካሞች የሚያርስ፣የሚያርም፣የሚያጭድና አንበጣ የሚከላከል ነው። በትምህርት ቤቶች፣በጤና ጣቢያዎች፣በመንገድ ግንባታዎች በሚሳተፍ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈጸም የህወሓት ቡድን እወክለዋለሁ ቆሜለታለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ እንደሌለው ያሳያል ይላሉ፡፡
የአገሩን ዳር ድንበር የሚጠብቀውን፤የኢትዮጵያ ብሄሮችና ብሄረሰቦች ስብስብ የሆነውን የመከላከያ ሰራዊት ለማውድምና ለማጥፋት ነው ጥቃቱን የሰነዘሩት ፡፡እነዚህ ሰዎች ከዚህ በኋላ ስለኢትዮጵያዊነት፣ብሄሮች ፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቢሰብኩ፣ቢለፈልፉ፣ቢቀሰቅሱ ማን ጀሮ ይሰጣቸዋል ፡፡ምክንያቱም ጥቃቱን በጽናት ለመመከት የተዋደቁት ከኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የተወጣጡ ወታደሮች ናቸው ብለዋል፡፡
ጀኔራሉ በ1980ዓ.ም በወቅቱ ኢህዲን ተብሎ የሚጠራውን ትግል የተቀላቀሉ ናቸው፡፡ከዚሁ ዓመት ጀምሮ ደርግ እስኪደመሰስ ድረስ በተደረጉ ውጊያዎች ተሳትፈዋል።ቆቦ አካባቢ በተካሄደው ሰላም በትግል ኦፕሬሽን፤ሰሜን ሸዋ መራኛ፣ ጁሁርና መራቤቴ አውድ ውጊያዎች ተሳትፈዋል፡፡በጎጃም ደጀን፣አምቦ፣ነቀምት፣ጅማ፣ቡሌሆራ(አገረ ማርያም) ሞያሌ ድረስ በዘለቀው አውድ ውጊያ ተሳትፈዋል፡፡በሀረርም ጸረ ሰላም ሀይሎችን በመከላከልና በማጥቃት ዘመቻ ተሳትፈዋል፡፡በሩዋንዳ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በ1986ዓ.ም ግድጃቸውን በስኬት አጠናቀው ተመልሰዋል፡፡
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሲቋቋምም 20ኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ብርጌድ አንደኛ ሻለቃ አዛዥ ሆነው አገልግለዋል፡፡በኢትዮ-ኢርትራ ጦርነትም ትምህርታቸውን አቋርጠው በመሄድ ብርጌድ አዛዥ በመሆን በጾረና፣በባድመ፣በሽራሮ አዲኋላ ግንባር ተሳትፈዋል፡፡
አሁንም በዳንሻ ከተማ በትግራይ ልዩ ሀይል የተካሄደውን ከበባና ሶስት ቀናት የዘለቀ ጥቃት ወስን ወታደሮችን መርተውና አዋግተው በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ዕገዛ መከላከሉን በድል አጠናቀው የማጥቃቱን ተልዕኮ በድል እየተወጡ ይገኛሉ።
አዲስ ዘመን ህዳር 1/2013
የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሲቋቋምም 20ኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ብርጌድ አንደኛ ሻለቃ አዛዥ ሆነው አገልግለዋል፡፡በኢትዮ-ኢርትራ ጦርነትም ትምህርታቸውን አቋርጠው በመሄድ ብርጌድ አዛዥ በመሆን በጾረና፣በባድመ፣በሽራሮ አዲኋላ ግንባር ተሳትፈዋል፡፡
አሁንም በዳንሻ ከተማ በትግራይ ልዩ ሀይል የተካሄደውን ከበባና ሶስት ቀናት የዘለቀ ጥቃት ወስን ወታደሮችን መርተውና አዋግተው በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ዕገዛ መከላከሉን በድል አጠናቀው የማጥቃቱን ተልዕኮ በድል እየተወጡ ይገኛሉ።
አዲስ ዘመን ህዳር 1/2013
የበረሃ አንበጣ የመከላከል ስራን በድሮን ቴክኖሎጂ ለመደገፍ የእስራኤል መንግስት የባለሙያዎች ስልጠና እና 27 ድሮኖችን ድጋፍ አደረገ
************************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ የመከላከል ስራን በድሮን ቴክኖሎጂ ለመደገፍ የእስራኤል መንግስት የባለሙያዎች ስልጠናና 27 ድሮኖች ድጋፍ ማድረጉን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ድጋፍ በተደረገበት ወቅት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ ኡመር ሁሴን እንደገለጹት፤ የበረሃ አንበጣውን ለመከላከል የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ ይገኛል። የእስራኤል መንግስትም ከዚህ በፊት በገቡት ቃል መሰረት በተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ መከላከል የሚያስችሉ ድሮኖችን ድጋፍ አድርጓል።
እነዚህን ድሮኖች በመጠቀም በሌሊት ርጭት በማድረግ የመከላከል ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ በድሮኖቹ በመታገዝም የዳሰሳ ጥናት በማድረግ መረጃዎችን በመሰብሰብ ውጤታማ የመከላከል ስራ ለመስራት ያስችላል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ራፋኤል ሞራፍ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ለመከላከል በድሮኖችን የታገዘ መረጃ የመሰብስብና በሌሊት ርጭት በማካሄድ የመከላከል ስራ መስራት ያስችላል ብለዋል፡፡
የእስራኤል ሉኡካን ቡድንም በሱማሌ ክልል በመገኘት ስልጠናውን ተግባር ተኮር በሆነ መልኩ ለባለሙያዎች ከሰጡ በኋላ 27 ድሮኖችንና ሁለት ጀኔሬተሮችን ለስራዉ ድጋፍ በማድረግ የመከላከል ስራውን በአግባቡ ለመተግበር እንዲያስችል ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡
በመጨረሻም ስልጠናው በሀገራችን የሚገኙ ባለሙያዎችን በቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁ ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ሚና እንዳለው የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ ኡመር ሁሴን ገልጸዋል፡፡
************************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ የመከላከል ስራን በድሮን ቴክኖሎጂ ለመደገፍ የእስራኤል መንግስት የባለሙያዎች ስልጠናና 27 ድሮኖች ድጋፍ ማድረጉን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ድጋፍ በተደረገበት ወቅት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ ኡመር ሁሴን እንደገለጹት፤ የበረሃ አንበጣውን ለመከላከል የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ ይገኛል። የእስራኤል መንግስትም ከዚህ በፊት በገቡት ቃል መሰረት በተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ መከላከል የሚያስችሉ ድሮኖችን ድጋፍ አድርጓል።
እነዚህን ድሮኖች በመጠቀም በሌሊት ርጭት በማድረግ የመከላከል ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ በድሮኖቹ በመታገዝም የዳሰሳ ጥናት በማድረግ መረጃዎችን በመሰብሰብ ውጤታማ የመከላከል ስራ ለመስራት ያስችላል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ራፋኤል ሞራፍ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ለመከላከል በድሮኖችን የታገዘ መረጃ የመሰብስብና በሌሊት ርጭት በማካሄድ የመከላከል ስራ መስራት ያስችላል ብለዋል፡፡
የእስራኤል ሉኡካን ቡድንም በሱማሌ ክልል በመገኘት ስልጠናውን ተግባር ተኮር በሆነ መልኩ ለባለሙያዎች ከሰጡ በኋላ 27 ድሮኖችንና ሁለት ጀኔሬተሮችን ለስራዉ ድጋፍ በማድረግ የመከላከል ስራውን በአግባቡ ለመተግበር እንዲያስችል ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡
በመጨረሻም ስልጠናው በሀገራችን የሚገኙ ባለሙያዎችን በቴክኖሎጂ ሽግግር ብቁ ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ሚና እንዳለው የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ ኡመር ሁሴን ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቀረቡ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቀረቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‹‹የጁንታው ፀሐይ እየጠለቀች ነው›፤ ይሄን መርዶ ጁንታው በቁሙ ተረድቶታል›› ብለዋል።
‹‹ጁንታው አሁን የሚይዘውን የሚጨብጠውን የሚያጣበት ጊዜ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ‹‹በመሆኑም በጣዕር መንፈስ በየቦታው የመጨረሻውን የጥፋት ድግስ ይደግስ ይሆናል›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በመሆኑም ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወገኖች በየአካባቢው ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳይደርስባቸው ሁሉም የወንድሞቹ ጠባቂ እንዲሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።
‹‹የኢትዮጵያ ጠላት ስግብግቡ ጁንታ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትግራይ ሕዝብ እንደሌላው ሕዝብ በጁንታው መከራ ያየ ሕዝብ መሆኑን አስታውሰዋል።
‹‹ጁንታው ለፍርድ እንዲቀርብ የትግራይ ሕዝብም ከመከላከያ ሠራዊት ጋር አብሮ እየተዋጋ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹‹ሕዝቡ አካባቢዬን እጠብቃለሁ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የመከራ ቀንበር እሰብራለሁ፤ ጁንታውን ለፍርድ አቀርባለሁ›› ቃል ኪዳኑ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቀረቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‹‹የጁንታው ፀሐይ እየጠለቀች ነው›፤ ይሄን መርዶ ጁንታው በቁሙ ተረድቶታል›› ብለዋል።
‹‹ጁንታው አሁን የሚይዘውን የሚጨብጠውን የሚያጣበት ጊዜ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ‹‹በመሆኑም በጣዕር መንፈስ በየቦታው የመጨረሻውን የጥፋት ድግስ ይደግስ ይሆናል›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በመሆኑም ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወገኖች በየአካባቢው ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳይደርስባቸው ሁሉም የወንድሞቹ ጠባቂ እንዲሆን መልዕክት አስተላልፈዋል።
‹‹የኢትዮጵያ ጠላት ስግብግቡ ጁንታ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትግራይ ሕዝብ እንደሌላው ሕዝብ በጁንታው መከራ ያየ ሕዝብ መሆኑን አስታውሰዋል።
‹‹ጁንታው ለፍርድ እንዲቀርብ የትግራይ ሕዝብም ከመከላከያ ሠራዊት ጋር አብሮ እየተዋጋ ነው›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹‹ሕዝቡ አካባቢዬን እጠብቃለሁ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የመከራ ቀንበር እሰብራለሁ፤ ጁንታውን ለፍርድ አቀርባለሁ›› ቃል ኪዳኑ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
ህግን የማስከበር ዘመቻው በስፋት እና በድል ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ጎንደር፡- ህግን የማስከበር ዘመቻው በስፋት እና በድል ተጠናክሮ መቀጠሉን የሰሜን እዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል በላይ ስዩም ገለፁ። ስራዊቱ ዳንሻ፣ ትርካን፣ ዲቪዥን፣ ባእኸር፣ ራውያንን እና ሁመራን መቆጣጠሩንም አስታወቁ ።
ሜጀር ጄኔራል በላይ በስፍራው ለሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋዜጠኛ እንዳስታወቁት ፤ የኢፌዴሪ መከላከያ ኃይል በምዕራብ ትግራይ ግንባር ትናንት በወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ 550 የህወሓት ታጥቂ ቡድን አባላት ተደምስሰዋል። 29 የልዩ ሃይል እና ሚሊሻ አባላትም እጃቸውን ሰጥተዋል።
ሰራዊቱ ባካሄደው ህግን የማስከበር ኦፕሬሽን በፅንፈኛው የህወሓት ታጣቂ ቡድን ከፍተኛ ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን አመልክተው፣ 115 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 11 መትረየስ፣ 2 ድሽቃ፣ 8 አር ፒጂ ከባድ መሳሪያ፣ 152 የእጅ ቦንብ፣ 2 ስናይፐር፣ 4 ኤም-14 ጦር መሳሪያ፣ 2 ኢንኮም ሬድዮ መማረኩን አስታውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም 21ሺህ 650 የክላሽ ጥይት፣ 14ሺህ 730 የመትረየስ ጥይት 1 የጦር ሜዳ መነፅር፣ 64 የጦር ሜዳ ቀበቶ፤ 6 የአር ፒ ጂ ቅንቡላ፣ 90 የክላሽ መጋዘን እና 10 የመትረየስ ዝናር መማረኩን አመልክተዋል።
በምዕራብ ትግራይ ግንባር እየተከናወነ ያለው ህግን የማስከበር ዘመቻ ሰራዊቱ ዳንሻ፣ ትርካን፣ ዲቪዥን፣ ባእኸር፣ ራውያንን እና ሁመራን መቆጣጠሩንም ተናግረዋል። የሰራዊቱ ተልዕኮን የመፈፀም ብቃት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
አዲስ ዘመን ህዳር 2 ቀን 2013 ዓ.ም
በጌትነት ምህረቴ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ጎንደር፡- ህግን የማስከበር ዘመቻው በስፋት እና በድል ተጠናክሮ መቀጠሉን የሰሜን እዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል በላይ ስዩም ገለፁ። ስራዊቱ ዳንሻ፣ ትርካን፣ ዲቪዥን፣ ባእኸር፣ ራውያንን እና ሁመራን መቆጣጠሩንም አስታወቁ ።
ሜጀር ጄኔራል በላይ በስፍራው ለሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋዜጠኛ እንዳስታወቁት ፤ የኢፌዴሪ መከላከያ ኃይል በምዕራብ ትግራይ ግንባር ትናንት በወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ 550 የህወሓት ታጥቂ ቡድን አባላት ተደምስሰዋል። 29 የልዩ ሃይል እና ሚሊሻ አባላትም እጃቸውን ሰጥተዋል።
ሰራዊቱ ባካሄደው ህግን የማስከበር ኦፕሬሽን በፅንፈኛው የህወሓት ታጣቂ ቡድን ከፍተኛ ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን አመልክተው፣ 115 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 11 መትረየስ፣ 2 ድሽቃ፣ 8 አር ፒጂ ከባድ መሳሪያ፣ 152 የእጅ ቦንብ፣ 2 ስናይፐር፣ 4 ኤም-14 ጦር መሳሪያ፣ 2 ኢንኮም ሬድዮ መማረኩን አስታውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም 21ሺህ 650 የክላሽ ጥይት፣ 14ሺህ 730 የመትረየስ ጥይት 1 የጦር ሜዳ መነፅር፣ 64 የጦር ሜዳ ቀበቶ፤ 6 የአር ፒ ጂ ቅንቡላ፣ 90 የክላሽ መጋዘን እና 10 የመትረየስ ዝናር መማረኩን አመልክተዋል።
በምዕራብ ትግራይ ግንባር እየተከናወነ ያለው ህግን የማስከበር ዘመቻ ሰራዊቱ ዳንሻ፣ ትርካን፣ ዲቪዥን፣ ባእኸር፣ ራውያንን እና ሁመራን መቆጣጠሩንም ተናግረዋል። የሰራዊቱ ተልዕኮን የመፈፀም ብቃት ከየትኛውም ጊዜ በላይ አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
አዲስ ዘመን ህዳር 2 ቀን 2013 ዓ.ም
በጌትነት ምህረቴ
ከሀዲው የህወሃት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ለማውገዝና እየፈጸመው ያለውን ግፍ ለመላው ዓለም ለማሳወቅ በአዲስ አበባ፣ በአማራና በኦሮሚያ ከተሞች ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
መቀሌ የመሸገው የህወሀሓት ከሀዲና ዘራፊ ቡድን በአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ለማውገዝና ቡድኑ በንጹሀን ዜጎች ላይ እየፈጸመው ያለውን የጅምላ ግድያ ለዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ በአዲስ አበባ እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ከተሞች የድጋፍ ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በከተሞቹ የሚካሄዱት ሰልፎች፤ የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ጀግኖች የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፈጸመውን ክህደትና ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለማውገዝና በመከላከያ ሰራዊትና በአማራ ልዩ ሃይል እየተወሰደ ያለወን ህግ የማስከበር እርምጃ የመደገፍ ዓላማ እንዳለው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ አንቺነሽ ተስፋዬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የመከላከያ ሠራዊቱ የጽንፈኛው የህወሓት ቡድንን ወደ ህግ ለማምጣት እያደረገ ባለው ጥረት ህብረተሰቡ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆናቸውን የሚገልጹበትን የድጋፍ ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ በመቀበሉን ተናግረዋል።
ከነገ ጀምሮ በሚካሄደው የደም ልገሳ መርሃግብር ደማችን ለወገናችን እና ደማችን ለመከላከያ ሰራዊታችን በሚሉ እንደሚካሄድ ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን መሆናቸውን ለመግለጽ ሠላማዊ ሰልፍ የሚደረግ ሲሆን በሰልፉም የፀጥታ ችግሮች እንዳይፈጠር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከኦሮሚያ የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር በተገበው መንገድ ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት ስራ መደረጉን አንቺነሽ አመልክተዋል።
በተጨማሪም ህብረተሰቡ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆኑን ለማሳየት እንዲሁም ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ላሉ ሚሊሻዎች በገንዘብ እና ቁሳቁስ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም የኦሮሚያ ዞኖች፣ ከተሞች እና ወረዳዎችም ሰላማዊ ሰልፎች ለማድረግ በርካታ ጥያቄዎች በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ ገልጸዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፎቹ ከነገ ህዳር 3 ቀን 2013 ጀምሮ እንዲደረጉ መፈቀዱን አቶ አዲሱ ገልጸዋል፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
እንደገለጹት፤ ህዝቡ ከሀዲው የህወሓት ቡድን እያደረሰ ያለውን ግፍ በአደባባይ ለመቃወም በተለያየ መንገድ ጥያቄውን ሲያቀርብ ቆይቷል።
የሰልፉ ዓላማ ህገ ወጡ የትህነግ መንግሥት እየፈጸመው ያለውን ግፍና በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ ያደረሰውን ክህደት ለመላው ዓለም ለማሳወቅ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ሰልፉ የሚካሄደውም በባህር ዳር፣ ፍኖተ ሰላም፣ እንጅባራ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃን፣ ኮምቦልቻ፣ ደሴ፣ ደብረ ታቦር ከተሞች ብቻ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከእነዚህ ከተሞች ውጭ ባሉ የክልሉ ከተሞች ሰልፉ የማይካሄደው ከሀዲውን ቡድን በህግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል በሚደረገው ውጊያ ልዩ የጸጥታ ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ አንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊትና በአማራ ክልል ልዩ ሀይል በጋራ እያደረጉት ባለው ህግን የማስከበር ስራ የከሀዲው የህወሓት ቡድን ልዩ ሀይልና ሚሊሻ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት አካባቢው ጥሎ እየሸሸ ሲሆን፤ ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ሌሊቱን የማይካንድራ ከተማን ለቅቆ ከመሸሹ በፊት በርካታ ንጹሀንን ጨፍጭፎ መውጣቱ ይታወሳል።
****************************
(ኢ ፕ ድ)
መቀሌ የመሸገው የህወሀሓት ከሀዲና ዘራፊ ቡድን በአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ለማውገዝና ቡድኑ በንጹሀን ዜጎች ላይ እየፈጸመው ያለውን የጅምላ ግድያ ለዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ በአዲስ አበባ እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ከተሞች የድጋፍ ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በከተሞቹ የሚካሄዱት ሰልፎች፤ የህወሓት ጁንታ በሰሜን ዕዝ ጀግኖች የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፈጸመውን ክህደትና ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለማውገዝና በመከላከያ ሰራዊትና በአማራ ልዩ ሃይል እየተወሰደ ያለወን ህግ የማስከበር እርምጃ የመደገፍ ዓላማ እንዳለው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ አንቺነሽ ተስፋዬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የመከላከያ ሠራዊቱ የጽንፈኛው የህወሓት ቡድንን ወደ ህግ ለማምጣት እያደረገ ባለው ጥረት ህብረተሰቡ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆናቸውን የሚገልጹበትን የድጋፍ ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ በመቀበሉን ተናግረዋል።
ከነገ ጀምሮ በሚካሄደው የደም ልገሳ መርሃግብር ደማችን ለወገናችን እና ደማችን ለመከላከያ ሰራዊታችን በሚሉ እንደሚካሄድ ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን መሆናቸውን ለመግለጽ ሠላማዊ ሰልፍ የሚደረግ ሲሆን በሰልፉም የፀጥታ ችግሮች እንዳይፈጠር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከኦሮሚያ የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር በተገበው መንገድ ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት ስራ መደረጉን አንቺነሽ አመልክተዋል።
በተጨማሪም ህብረተሰቡ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሆኑን ለማሳየት እንዲሁም ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ላሉ ሚሊሻዎች በገንዘብ እና ቁሳቁስ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይም የኦሮሚያ ዞኖች፣ ከተሞች እና ወረዳዎችም ሰላማዊ ሰልፎች ለማድረግ በርካታ ጥያቄዎች በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ ገልጸዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፎቹ ከነገ ህዳር 3 ቀን 2013 ጀምሮ እንዲደረጉ መፈቀዱን አቶ አዲሱ ገልጸዋል፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
እንደገለጹት፤ ህዝቡ ከሀዲው የህወሓት ቡድን እያደረሰ ያለውን ግፍ በአደባባይ ለመቃወም በተለያየ መንገድ ጥያቄውን ሲያቀርብ ቆይቷል።
የሰልፉ ዓላማ ህገ ወጡ የትህነግ መንግሥት እየፈጸመው ያለውን ግፍና በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ ያደረሰውን ክህደት ለመላው ዓለም ለማሳወቅ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ሰልፉ የሚካሄደውም በባህር ዳር፣ ፍኖተ ሰላም፣ እንጅባራ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃን፣ ኮምቦልቻ፣ ደሴ፣ ደብረ ታቦር ከተሞች ብቻ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከእነዚህ ከተሞች ውጭ ባሉ የክልሉ ከተሞች ሰልፉ የማይካሄደው ከሀዲውን ቡድን በህግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል በሚደረገው ውጊያ ልዩ የጸጥታ ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ አንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊትና በአማራ ክልል ልዩ ሀይል በጋራ እያደረጉት ባለው ህግን የማስከበር ስራ የከሀዲው የህወሓት ቡድን ልዩ ሀይልና ሚሊሻ ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት አካባቢው ጥሎ እየሸሸ ሲሆን፤ ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ሌሊቱን የማይካንድራ ከተማን ለቅቆ ከመሸሹ በፊት በርካታ ንጹሀንን ጨፍጭፎ መውጣቱ ይታወሳል።
ተሸናፊው የህወሓት ከሀዲ ቡድን በማይካድራ ከተማ የፈጸመው ጭፍጨፋ ዋና ዓላማ በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማሰብ ነው ሲል የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ
**********************
(ኢ.ፕ.ድ)
ተሸናፊው የህወሓት ከሀዲ ቡድን በማይካድራ ከተማ ነዋሪ በሆኑ የአማራ ተወላጆች ላይ የፈጸመው ጭፍጨፋ ዋና ዓላማ በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማሰብ ነው ሲል የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።
“እየሞትንም ቢሆን እናሸንፋለን” በሚል ርዕስ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ “ወገኖቻችን ላይ በተሸናፊው የትህነግ ጦር አማካኝነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሞባቸዋል” ያለው ፓርቲው፤ ድርጊቱ በዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የሚያስጠይቅ ወንጀል ነው ሲል አስታውቋል።
“ተሸናፊው ትህነግ በወገኖቻችን ላይ ይሄን አሰቃቂ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመው በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት (Civil War) እንዲቀሰቀስ አስቦ መሆኑን እናውቃለን” ያለው ፓርቲው፤ ለአማራ ህዝብ ባቀረበው ጥሪም፤ “በተለመደው አስተዋይ ባህሪህ ምስኪኑ የትግራይ ህዝብ እንደ ትላንቱ ሁሉ ዛሬም ከየትኛውም ጥቃት ጥላ ከለላ ሁነህ ይህን ጊዜ እንድታሳልፈው ይሁን” ሲል አሳስቧል።
“በባህል፣ በሃይማኖት፣ በማህበራዊ ትስስር፣ አልፎም በረዥሙ የአገር ግንባታ ጉዞ ከአማራ ሕዝብ ጋር የጋራ ታሪክ ያለውን የትግራይ ሕዝብ መከታና ጋሻ ሆነህ አስተዋይነትና አብሮነት የምንጊዜም ምርጫህ እንደሆነ ለመላ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በተግባር እንድታሳይ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን” ሲልም ነው ፓርቲው መልዕክትን ለአማራ ህዝብ ያቀረበው።
የትግራይ ሕዝብ እንደትላንቱ ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ አብሮህ ይኖራል። ዝንታለም ጠላትህ ትህነግና ወገኖችህን የጨረሰው የትህነግ ሰራዊት ነው፤ ያለው ፓርቲው፤ “ስለዚህ ትህነግ ካጠመደልህ ወጥመድ ሳትገባ፤ የወገኖችህን ደም የምትመልሰው ትህነግንና ገዳይ ሰራዊቱን እስከመጨረሻው በመፋለም መደምሰስ ሲቻል መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን” ብሏል።
የትህነግ ዘራፊ ቡድን ዓላማ ማስፈጸሚያ የሆኑት ልዩ ሃይል እና ሳምሪ የተባለው ገዳይ ቡድን በማይካድራ ከተማ የሚገኙ ንጹኀን ሰላማዊ ዜጎችን በጂምላ መጨፍጨፉ ይታወሳል።
በርካታ ንጹሀን አማራዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት በቦታው ተገኝቶ አረጋግጧል።
**********************
(ኢ.ፕ.ድ)
ተሸናፊው የህወሓት ከሀዲ ቡድን በማይካድራ ከተማ ነዋሪ በሆኑ የአማራ ተወላጆች ላይ የፈጸመው ጭፍጨፋ ዋና ዓላማ በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማሰብ ነው ሲል የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።
“እየሞትንም ቢሆን እናሸንፋለን” በሚል ርዕስ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ “ወገኖቻችን ላይ በተሸናፊው የትህነግ ጦር አማካኝነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሞባቸዋል” ያለው ፓርቲው፤ ድርጊቱ በዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የሚያስጠይቅ ወንጀል ነው ሲል አስታውቋል።
“ተሸናፊው ትህነግ በወገኖቻችን ላይ ይሄን አሰቃቂ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈፀመው በህዝቦች መካከል የእርስ በርስ ጦርነት (Civil War) እንዲቀሰቀስ አስቦ መሆኑን እናውቃለን” ያለው ፓርቲው፤ ለአማራ ህዝብ ባቀረበው ጥሪም፤ “በተለመደው አስተዋይ ባህሪህ ምስኪኑ የትግራይ ህዝብ እንደ ትላንቱ ሁሉ ዛሬም ከየትኛውም ጥቃት ጥላ ከለላ ሁነህ ይህን ጊዜ እንድታሳልፈው ይሁን” ሲል አሳስቧል።
“በባህል፣ በሃይማኖት፣ በማህበራዊ ትስስር፣ አልፎም በረዥሙ የአገር ግንባታ ጉዞ ከአማራ ሕዝብ ጋር የጋራ ታሪክ ያለውን የትግራይ ሕዝብ መከታና ጋሻ ሆነህ አስተዋይነትና አብሮነት የምንጊዜም ምርጫህ እንደሆነ ለመላ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በተግባር እንድታሳይ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን” ሲልም ነው ፓርቲው መልዕክትን ለአማራ ህዝብ ያቀረበው።
የትግራይ ሕዝብ እንደትላንቱ ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ አብሮህ ይኖራል። ዝንታለም ጠላትህ ትህነግና ወገኖችህን የጨረሰው የትህነግ ሰራዊት ነው፤ ያለው ፓርቲው፤ “ስለዚህ ትህነግ ካጠመደልህ ወጥመድ ሳትገባ፤ የወገኖችህን ደም የምትመልሰው ትህነግንና ገዳይ ሰራዊቱን እስከመጨረሻው በመፋለም መደምሰስ ሲቻል መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን” ብሏል።
የትህነግ ዘራፊ ቡድን ዓላማ ማስፈጸሚያ የሆኑት ልዩ ሃይል እና ሳምሪ የተባለው ገዳይ ቡድን በማይካድራ ከተማ የሚገኙ ንጹኀን ሰላማዊ ዜጎችን በጂምላ መጨፍጨፉ ይታወሳል።
በርካታ ንጹሀን አማራዎች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት በቦታው ተገኝቶ አረጋግጧል።
ኦነግ ሸኔ ከከሀዲው ቡድን ጋር በመሆን በውጊያው ላይ አየተሳተፈ መሆኑ ተገለፀ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአገር መከላከያ ሰራዊትና በአማራ ክልል ልዩ ሀይል ጥምረት በከሀዲው የህወሓት ጁንታ ላይ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር ስራ ላይ ኦነግ ሸኔ ከከሀዲው ቡድን ጋር በመሆን በውጊያው እየተሳተፈ መሆኑ ተገለጸ።
ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፤ በአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ክህደት የፈጸመውና ለመናገር የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ በፈጸመው የህወሓት ዘራፊ ቡድን ላይ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር ስራ ላይ የኦነግ ባንዲራን የያዙ የሸኔ አባላት በጦርነቱ እየተሳተፉ መሆናቸው ተረጋግጧል።
ሀገሩንና ህዝቡን በማገልገል ላይ በለው ሰራዊት ላይ ከሀዲው ቡድን ከኦነግ ሸኔ ጋር አብሮ በውጊያው ላይ መሳተፉ እንዳስገረማቸውም ነው ሌተናል ጄኔራል ባጫ የገለጹት።
የኦነግ ሸኔ አባላት በሁሉም ቦታዎች ላይ የሚታወቀውን የኦነግን ባንዲራ በመያዝ ከከሃዲው የህወሓት ቡድን ጋር በመሆን በሽራሮ፣ በራማ፣ በፆረና፣ እና በዛላንበሳ በኩል ውጊያ መግጠማቸውን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ አስታውቀዋል።
ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች በንጹሀን ላይ ከሚፈጸሙ ጥቃቶች ጀርባ ዘራፊው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ እጃቸው አለበት ሲል መንግስት በተደጋጋሚ ማስታወቁ ይታወሳል።
በሀይማኖት ከበደ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአገር መከላከያ ሰራዊትና በአማራ ክልል ልዩ ሀይል ጥምረት በከሀዲው የህወሓት ጁንታ ላይ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር ስራ ላይ ኦነግ ሸኔ ከከሀዲው ቡድን ጋር በመሆን በውጊያው እየተሳተፈ መሆኑ ተገለጸ።
ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፤ በአገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ክህደት የፈጸመውና ለመናገር የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ በፈጸመው የህወሓት ዘራፊ ቡድን ላይ እየተወሰደ ባለው ህግ የማስከበር ስራ ላይ የኦነግ ባንዲራን የያዙ የሸኔ አባላት በጦርነቱ እየተሳተፉ መሆናቸው ተረጋግጧል።
ሀገሩንና ህዝቡን በማገልገል ላይ በለው ሰራዊት ላይ ከሀዲው ቡድን ከኦነግ ሸኔ ጋር አብሮ በውጊያው ላይ መሳተፉ እንዳስገረማቸውም ነው ሌተናል ጄኔራል ባጫ የገለጹት።
የኦነግ ሸኔ አባላት በሁሉም ቦታዎች ላይ የሚታወቀውን የኦነግን ባንዲራ በመያዝ ከከሃዲው የህወሓት ቡድን ጋር በመሆን በሽራሮ፣ በራማ፣ በፆረና፣ እና በዛላንበሳ በኩል ውጊያ መግጠማቸውን ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ አስታውቀዋል።
ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች በንጹሀን ላይ ከሚፈጸሙ ጥቃቶች ጀርባ ዘራፊው የህወሓት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ እጃቸው አለበት ሲል መንግስት በተደጋጋሚ ማስታወቁ ይታወሳል።
በሀይማኖት ከበደ
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ መልዕክት
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ለስግብግቡ ጁንታ ግፍ እስትንፋሱ፣ ጭካኔ ነፍሱ ነው። ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ሽራሮን ሲቆጣጠር፣ እጅና እግራቸውን የፊጥኝ ታሥረው የተረሸኑ የመከላከያ አባላትን አግኝቷል። ጭካኔው ልብ ሰባሪ ነበር።
ዓላማው ኢትዮጵያን መስበር ነው።
አላወቁም ከአልማዝ የጠነከረች መሆኗን።
ዓላማው ሠራዊታችንንና ሕዝቡን አስቆጥቶ ለበቀል ርምጃ ማነሣሣት ነው።
አላወቁም ልበ ሰፊ ሕዝብና ሠራዊት እንዳለን።
በየቦታው ስንደርስ ከዚህ የከፋ ጭካኔና ግፍ ሊገጥመን ይችላል። ይህ ግን ለዚህ ጁንታ የመጨረሻው ነው። ጥንቃቄያችን 'ሙት ይዞን እንዳይሞት' ነው። መፍጠን አለብን፤ የተረፉትን ለመታደግና ግፍ የተፈጸመባቸውንም ለዓለም ለማጋለጥ።
የምዕራቡን የትግራይ ክልል ቀጣና ነጻ ወጥቷል። በዚያ ቀጣና ሠራዊቱ ሰብዓዊ ርዳታና አገልግሎት እየሰጠ ነው። ነጻ ባወጣቸው አካባቢዎች ሕዝቡን እየመገበ፣ እያከመና እየተንከባከበ ነው።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ለስግብግቡ ጁንታ ግፍ እስትንፋሱ፣ ጭካኔ ነፍሱ ነው። ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ሽራሮን ሲቆጣጠር፣ እጅና እግራቸውን የፊጥኝ ታሥረው የተረሸኑ የመከላከያ አባላትን አግኝቷል። ጭካኔው ልብ ሰባሪ ነበር።
ዓላማው ኢትዮጵያን መስበር ነው።
አላወቁም ከአልማዝ የጠነከረች መሆኗን።
ዓላማው ሠራዊታችንንና ሕዝቡን አስቆጥቶ ለበቀል ርምጃ ማነሣሣት ነው።
አላወቁም ልበ ሰፊ ሕዝብና ሠራዊት እንዳለን።
በየቦታው ስንደርስ ከዚህ የከፋ ጭካኔና ግፍ ሊገጥመን ይችላል። ይህ ግን ለዚህ ጁንታ የመጨረሻው ነው። ጥንቃቄያችን 'ሙት ይዞን እንዳይሞት' ነው። መፍጠን አለብን፤ የተረፉትን ለመታደግና ግፍ የተፈጸመባቸውንም ለዓለም ለማጋለጥ።
የምዕራቡን የትግራይ ክልል ቀጣና ነጻ ወጥቷል። በዚያ ቀጣና ሠራዊቱ ሰብዓዊ ርዳታና አገልግሎት እየሰጠ ነው። ነጻ ባወጣቸው አካባቢዎች ሕዝቡን እየመገበ፣ እያከመና እየተንከባከበ ነው።
የከሀዲው የህወሓት ቡድን መሪዎች ያለመከሰስ መብታቸው ተነሳ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ።
በዚህም መሰረት፦
1. ዶክተር ደብረጸዮን ገብረሚካኤል
2. አቶ አስመላሽ ወልደሰንብት
3. አቶ አባይ ፀሃዬ
4. ዶክተር አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ
5. አቶ ጌታቸው ረዳ
6. አቶ አፅበሃ አረጋዊ
7. አቶ ገብር እግዚአብሄር አርአያ እና ሌሎችም ላይ የቀረበው ያለመከሰስ
መብት የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበት ወንጀሎችም ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣
የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና
አድራጊነት ነው መሆኑ ታውቋል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ።
በዚህም መሰረት፦
1. ዶክተር ደብረጸዮን ገብረሚካኤል
2. አቶ አስመላሽ ወልደሰንብት
3. አቶ አባይ ፀሃዬ
4. ዶክተር አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ
5. አቶ ጌታቸው ረዳ
6. አቶ አፅበሃ አረጋዊ
7. አቶ ገብር እግዚአብሄር አርአያ እና ሌሎችም ላይ የቀረበው ያለመከሰስ
መብት የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበት ወንጀሎችም ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣
የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና
አድራጊነት ነው መሆኑ ታውቋል።
ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ስም ዝርዝር
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እነማን ናቸው?
1. ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል
2. አቶ አስመላሽ ወ/ስላሴ
3. አቶ አባይ ጸሀዬ
4. አምባሳደር ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ
5. አቶ ጌታቸው ረዳ
6. አቶ አጽብሃ አረጋዊ
7. አቶ ታደሰ ሀይሌ
8. ዶ/ር መብራቱ መለስ
9. ወ/ሮ ለምለም ሀድጉ
10. አቶ ገ/እግዚአብሄር አርኣያ
11. አቶ ሀለፎም ግደይ
12. አቶ ሀዱሽ አዛነው
13. ወ/ሮ መብራት ገ/ጊዮርጊስ
14. ወ/ሮ ሙሉ ገ/እግዚአብሄር
15. ወ/ሪት ልዕልቲ ጸጋዬ
16. ወ/ሮ ማሚት ተስፋይ
17. ወ/ሮ ማና አብርሃ
18. አቶ ካላዩ ገ/ህይወት
19. አቶ ጌዲዮን ሀ/ስላሴ
20. መ/ር በርሄ ዝግታ
21. አቶ ታደለ አሰፋ
22. አቶ ነጋ አሰፋ
23. ወ/ሮ ናፈቁሽ ደሴ
24. ወ/ሮ ሽሻይ ሀ/ሰላሴ
25. ወ/ሮ አልማዝ አርኣያ
26. ወ/ሮ አሰለፈች በቀለ
27. ወ/ሮ አስቴር አማረ
28. አቶ አለምሰገድ ወረታ
29. ዶ/ር አድሃና ሃይለ
30. አቶ ኪሮስ ወ/ሚካኤል
31. አቶ ሹምዬ ገብሬ
32. አቶ ካሳ ጉግሳ
33. ወ/ሮ አበራሽ አድማሱ
34. አቶ ዮሀንስ በቀለ
35. አቶ ዳኘው በለጠ
36. ወ/ሮ ፅዋሃብ ታደሰ
37. አቶ ዊንታ ተክሉ እና
38. አቶ ግርማይ ሻዲ ናቸው፡፡
(ምንጭ፡- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት )
***********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እነማን ናቸው?
1. ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል
2. አቶ አስመላሽ ወ/ስላሴ
3. አቶ አባይ ጸሀዬ
4. አምባሳደር ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ
5. አቶ ጌታቸው ረዳ
6. አቶ አጽብሃ አረጋዊ
7. አቶ ታደሰ ሀይሌ
8. ዶ/ር መብራቱ መለስ
9. ወ/ሮ ለምለም ሀድጉ
10. አቶ ገ/እግዚአብሄር አርኣያ
11. አቶ ሀለፎም ግደይ
12. አቶ ሀዱሽ አዛነው
13. ወ/ሮ መብራት ገ/ጊዮርጊስ
14. ወ/ሮ ሙሉ ገ/እግዚአብሄር
15. ወ/ሪት ልዕልቲ ጸጋዬ
16. ወ/ሮ ማሚት ተስፋይ
17. ወ/ሮ ማና አብርሃ
18. አቶ ካላዩ ገ/ህይወት
19. አቶ ጌዲዮን ሀ/ስላሴ
20. መ/ር በርሄ ዝግታ
21. አቶ ታደለ አሰፋ
22. አቶ ነጋ አሰፋ
23. ወ/ሮ ናፈቁሽ ደሴ
24. ወ/ሮ ሽሻይ ሀ/ሰላሴ
25. ወ/ሮ አልማዝ አርኣያ
26. ወ/ሮ አሰለፈች በቀለ
27. ወ/ሮ አስቴር አማረ
28. አቶ አለምሰገድ ወረታ
29. ዶ/ር አድሃና ሃይለ
30. አቶ ኪሮስ ወ/ሚካኤል
31. አቶ ሹምዬ ገብሬ
32. አቶ ካሳ ጉግሳ
33. ወ/ሮ አበራሽ አድማሱ
34. አቶ ዮሀንስ በቀለ
35. አቶ ዳኘው በለጠ
36. ወ/ሮ ፅዋሃብ ታደሰ
37. አቶ ዊንታ ተክሉ እና
38. አቶ ግርማይ ሻዲ ናቸው፡፡
(ምንጭ፡- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት )
በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ መወሰኑን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ፖሊስ ኮሚሽኑ እንዳለው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አንዳንድ የግል የጥበቃ ኤጀንሲዎች የተቋቋሙበትን ዓላማ ወደ ጎን በመተው ለሌላ እኩይ ተግባር የመረጡዋቸውን በመመልመል፣ ለተቋም ጥበቃ የተሰጣቸውን የጦር መሳሪያ በማስታጠቅና በማሰማራት በህዝብና በመንግስት ተቋማት እንዲሁም በተለያዩ አካላት ላይ ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተደርሶባቸዋል ፡፡
ካለፈው ዓመት ጀምሮ ኤጀንሲዎቹ ባንኮችንና የተለያዩ ድርጅቶችን ሲዘርፉና ሲያዘርፉ ቆይተዋል። በዚህም ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ገንዘብና ንብረት ዘርፈዋል፤ እንዲዘረፍም አድርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ተቋማቱን እንዲጠብቁበት የታጠቁትን በርካታ የጦር መሳሪያ ይዘው እንደጠፉም ተረጋግጧል። እነዚህ ከተልዕኮአቸው ውጭ እንደሚንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ይህም አልበቃ ብሏቸው አሁን ባለው ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ በጁንታው የህዋሃት ወንበዴ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈፀም የተለያዩ ግለሰቦችን ወደ ኤጀንሲዎቹ አስርገው በማስገባትና የጦር መሳሪያ በማስታጠቅ በህብረተሰቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ጥቃት ለመፈፀም እያሴሩ መሆኑ ተደርሶበታል ብሏል ፖሊስ ።
ስለሆነም ከዚህ ቀጥሎ ስማቸው የተገለፀው የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች፦
1. ንስር የሰው ሃይል እና የጥበቃ አገ/ሃ/የተ/የግ/ማ
2. አጋር የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
3. ስብኃቱና ልጆቹ የንብረት አስ/ጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
4. ሰላም ሴኩሪቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ
5. ኃይሌ ተክላይ እና ጓደኞቻቸው የጥበቃ አገልግሎት ህ/ስ/ማ
6. ክፍሌ ጎሳዬ ሃጎስ እና ወ/ገብርኤል የጥበቃ አገልግሎት ሽርክና /ማ
7. ዮናስ፣ ሮዛ እና መብርሂት የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሽ/ማ
8. ሃየሎም እና ብርሃኔ የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሸ/ማ
9. ደመላሽ፣ ሃፍቱ እና ጓደኞቻቸው የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሸ/ማ
10. ህሉፍና ሃለፎም የጥበቃ አገ/ህ/ሽ/ማ
11. ዋልታ የጥበቃ የሰው ኃይልና ኮሚሽን ኃ/የተ/የግ/ማ
12. ሴፍ የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
13. አትላስ ጠቅላላ አገ/ኃ/የተ/የግ/ማ
14. ጎህ የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
ለሀገርና ለዜጎች ሰላምና ደህንነት ሲባል ስራቸውን እንዲያቆሙ የተወሰነና እስከአሁን ባለው አገር የማተራመስና ህገ-ወጥ ስራቸው በህግ የሚጠየቁ መሆኑን እየገለጽን ስማቸው ከላይ የተገለፀው የጥበቃ ተቋማት በአስቸኳይ ስራቸውን አቁመው ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት እንዲያደርጉ እናሳውቃለን፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የግልም ሆነ የመንግስት አካል ከነዚህ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ምንም ዓይነት ቅጥር እንዳይፈፅም የተከለከለ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ስማቸው በተገለፀው የግል ጥበቃ ኤጀንሲ ስር ተቀጥረው ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ያሉ ሰራተኞችን በተመለከተ ማስተካከያ እስኪወሰድ የጥበቃ ስራቸውን አጠናክረው እንዲሰሩ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አሳስቧል፡፡
ፖሊስ ኮሚሽኑ እንዳለው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አንዳንድ የግል የጥበቃ ኤጀንሲዎች የተቋቋሙበትን ዓላማ ወደ ጎን በመተው ለሌላ እኩይ ተግባር የመረጡዋቸውን በመመልመል፣ ለተቋም ጥበቃ የተሰጣቸውን የጦር መሳሪያ በማስታጠቅና በማሰማራት በህዝብና በመንግስት ተቋማት እንዲሁም በተለያዩ አካላት ላይ ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተደርሶባቸዋል ፡፡
ካለፈው ዓመት ጀምሮ ኤጀንሲዎቹ ባንኮችንና የተለያዩ ድርጅቶችን ሲዘርፉና ሲያዘርፉ ቆይተዋል። በዚህም ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ገንዘብና ንብረት ዘርፈዋል፤ እንዲዘረፍም አድርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ተቋማቱን እንዲጠብቁበት የታጠቁትን በርካታ የጦር መሳሪያ ይዘው እንደጠፉም ተረጋግጧል። እነዚህ ከተልዕኮአቸው ውጭ እንደሚንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ይህም አልበቃ ብሏቸው አሁን ባለው ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ በጁንታው የህዋሃት ወንበዴ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈፀም የተለያዩ ግለሰቦችን ወደ ኤጀንሲዎቹ አስርገው በማስገባትና የጦር መሳሪያ በማስታጠቅ በህብረተሰቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ጥቃት ለመፈፀም እያሴሩ መሆኑ ተደርሶበታል ብሏል ፖሊስ ።
ስለሆነም ከዚህ ቀጥሎ ስማቸው የተገለፀው የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች፦
1. ንስር የሰው ሃይል እና የጥበቃ አገ/ሃ/የተ/የግ/ማ
2. አጋር የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
3. ስብኃቱና ልጆቹ የንብረት አስ/ጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
4. ሰላም ሴኩሪቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ
5. ኃይሌ ተክላይ እና ጓደኞቻቸው የጥበቃ አገልግሎት ህ/ስ/ማ
6. ክፍሌ ጎሳዬ ሃጎስ እና ወ/ገብርኤል የጥበቃ አገልግሎት ሽርክና /ማ
7. ዮናስ፣ ሮዛ እና መብርሂት የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሽ/ማ
8. ሃየሎም እና ብርሃኔ የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሸ/ማ
9. ደመላሽ፣ ሃፍቱ እና ጓደኞቻቸው የጥበቃ አገልግሎት ህ/ሸ/ማ
10. ህሉፍና ሃለፎም የጥበቃ አገ/ህ/ሽ/ማ
11. ዋልታ የጥበቃ የሰው ኃይልና ኮሚሽን ኃ/የተ/የግ/ማ
12. ሴፍ የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
13. አትላስ ጠቅላላ አገ/ኃ/የተ/የግ/ማ
14. ጎህ የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ
ለሀገርና ለዜጎች ሰላምና ደህንነት ሲባል ስራቸውን እንዲያቆሙ የተወሰነና እስከአሁን ባለው አገር የማተራመስና ህገ-ወጥ ስራቸው በህግ የሚጠየቁ መሆኑን እየገለጽን ስማቸው ከላይ የተገለፀው የጥበቃ ተቋማት በአስቸኳይ ስራቸውን አቁመው ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት እንዲያደርጉ እናሳውቃለን፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የግልም ሆነ የመንግስት አካል ከነዚህ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች ምንም ዓይነት ቅጥር እንዳይፈፅም የተከለከለ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ስማቸው በተገለፀው የግል ጥበቃ ኤጀንሲ ስር ተቀጥረው ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ያሉ ሰራተኞችን በተመለከተ ማስተካከያ እስኪወሰድ የጥበቃ ስራቸውን አጠናክረው እንዲሰሩ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አሳስቧል፡፡
የአብረኸት እንባ
👉150 ጥይት ተስጥቶኝ አንድም ጥይት ሳልተኩስ ነው እጄን የሰጠሁት፤
ምክንያቱም በዚህ ውጊያ አላምንበትም
********************
(ኢ ፕ ድ)
አብረኸት የጁንታው ታጣቂ የነበረችና እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት ከሰጡ ውስጥ አንዷ ነች። ገና የ21 አመት ወጣት ናት፡፡ ወጣቷ በ2011 ዓ.ም የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል በብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ስልጠና ወስዳለች፡፡ የኢትዮጵያ መካላከያ ሰራዊት አባል ሁና ነገሌ ቦረና ተመድባም ግዳጇን እየተወጣች ሳለ በጠና ታማ ከውትድርናው ዓለም ተሰናብታ ወደ ቤተሰቦቿ መመለሷን በስፍራው ተገኝቶ ላነጋገራት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅይ ዘጋቢ ገልጻለች።
የአብረኸት ህመም መጥናት ከምትወደው መከላከያ ቢለያትም ከጁንታው ዕይታ ግን መሰወር አልቻለችም። በጠላ ንግድ የሚተዳደሩትን እናቷን እያገዘች ኑሮን ብትቀጥልም፤ የጁንታው አባላት የአብረኸትን ወታደርነት ያውቁ ነበርና የጁንታውን ታጣቂ እንድትቀላቀል በእናቷ በኩል ግፊት ማድረግ ጀመሩ። ጁንታው የአብረኸትን እናት ሌት ተቀን በማስፈራራታቸው ልጃቸውን ሳይወዱ በግድ ለታጣቂው አስረከቡ፤ አብረኸትም ቤተሰቦቼን ለአደጋ ከማጋልጥ በሚል ታጣቂውን ተቀላቀለች።
“ሌላ ስራ በቀላሉ ማግኘት ስላልቻልኩና ጫናውና ማስፈራሪያው ሲበዛብኝ ታጣቂውን ተቀላቀልኩ። የቤተሰቡ አባላት ሰባት ነን ፤ አባቴ በህይወት የለም፡፡ እናቴ ብቻዋን ነው ጠላ ሽጣ ያሳደገችኝ፡፡ እሷን ለማገዝ ስልም ነው ወደዚህ የገባሁት” ስትልም ነው የታጣቂው አባል የሆነችበትን አጋጣሚ የምታስታውሰው።
አብረኸት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ እየወሰዱት ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ላይ እጇን የሰጠችው አንድም ጥይት ሳትተኩስ መሆኑን ትናገራለች፤ “150 ጥይት ተስጥቶኝ አንድም ጥይት ሳልተኩስ ነው እጄን የሰጠሁኝ። ምክንያቱም በዚህ ውጊያ አላምንበትም። እየሞተ ያለውም የደሀው ልጅ ነው። እጄን ከሰጠሁ በሁዋላም ቢሆን ሶስት ቀን ሙሉ የሰራዊቱ አባላት ከሚበሉትና ከሚጠጡት እያካፈሉኝ ቆይቻለሁ።
በትግራይ ክልል በየአካባቢው ያለው ወጣት ተገዶ ወደ ግዳጅ እንዲገባ ተደርጓል የምትለው ወጣቷ፤ ስልጠና የሚሰጠውም የይድረስ ይድረስ መሆኑን አልሸሸገችም፤ “ለአጭር ጊዜ ክላሽ እንዴት እንደሚፈታና እንደሚገጠም፣ ኢላማ እንዴት እንደሚመታ አሳይተው ብቻ ነው ወደ ጦርነት የሚማግዷቸው፡፡ ይህ ደግሞ የህወሓት አመራሮች ለትግራይ እናቶችም ሆነ ወጣቶች ደንታ እንደሌላቸውና የራሳቸውን የስልጣን ጥም ለማርካት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ያሳያል” ነው ያለችው፤ አብረኸት፡፡
“የህወሓት አመራሮች፤ የትግራይን ህዝብ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች እንደሚጠላው፣ የትም ሄደው በሰላም መኖር እንደማይችሉ አድርገው ወጣቱንንም ሆነ ህጻናትን ጭምር ይሰብካሉ። ሁሉም የትግራይ ህዝብ የዚህ አይነት አስተሳብ ስላለውና ህወሓትን ስለሚፈራ የሚሉትን ለማድረግ ይገደዳል። ይህ ሰላም የማይወድ ድርጅት ውጤት ለማያመጣ ነገር ወጣቱን እያስፈጀ ነው” ብላላች፤ አብረኸት።
የህወሓት ጁንታ ወጣቱን መስዋዕት የሚያስከፍሉት የማይሆን ነገር እየሞሉት፣ እያስገደዱትና፣ በገንዘብም እያታለለሉት ጭምር መሆኑን አብረኸት ትናገራለች።
የትግራይ ህዝብ መከላከያን እንዲወጋ አይፈልግም፤ ምክንያቱም መካላከያ የትግራይ ህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ ጎን ለጎን ለህብረተሰቡ ትምህርት ቤት እየሰራ፣ ጤና ጣቢያ እየገነባ የኖረ ወገን ነው፤ የምትለው አብረኸት፤ “ወርቅ ለአበደረ ጠጠር እንዲሉ እኛን አታለው እንደ ቤተሰብ የምናየውን መከላከያ ሰራዊትን እንድንወጋ አድርገውናል” ያለችው በከፍተኛ ጸጸት ውስጥ ሆና ነው።
“የህወሓት ቡድን እንደሚለው መከላከያ እኛን ቢጠላን ኖሮ እንዴት ትግራይን ይጠብቃታል” ስትልም ትጠይቃለች። “እኛ ምንግዜም ኢትዮጵያዊ ነን፤ አጸያፊ ስራ እስካልሰራን ድረስ ህዝቡ ዝም ብሎ አይጠላንም፡፡ በመሆኑም የትግራይ ወጣቶች ዓላማ የሌለው ጦርነት ውስጥ መግባት የለባቸውም። ለመከላከያ ሰራዊት እጃቸውን በመስጠት በሰላም መኖር ይኖርባቸዋል” ስትል ሀሳቧን ቋጭታለች።
በጌትነት ምህረቴ
👉150 ጥይት ተስጥቶኝ አንድም ጥይት ሳልተኩስ ነው እጄን የሰጠሁት፤
ምክንያቱም በዚህ ውጊያ አላምንበትም
********************
(ኢ ፕ ድ)
አብረኸት የጁንታው ታጣቂ የነበረችና እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት ከሰጡ ውስጥ አንዷ ነች። ገና የ21 አመት ወጣት ናት፡፡ ወጣቷ በ2011 ዓ.ም የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል በብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ስልጠና ወስዳለች፡፡ የኢትዮጵያ መካላከያ ሰራዊት አባል ሁና ነገሌ ቦረና ተመድባም ግዳጇን እየተወጣች ሳለ በጠና ታማ ከውትድርናው ዓለም ተሰናብታ ወደ ቤተሰቦቿ መመለሷን በስፍራው ተገኝቶ ላነጋገራት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅይ ዘጋቢ ገልጻለች።
የአብረኸት ህመም መጥናት ከምትወደው መከላከያ ቢለያትም ከጁንታው ዕይታ ግን መሰወር አልቻለችም። በጠላ ንግድ የሚተዳደሩትን እናቷን እያገዘች ኑሮን ብትቀጥልም፤ የጁንታው አባላት የአብረኸትን ወታደርነት ያውቁ ነበርና የጁንታውን ታጣቂ እንድትቀላቀል በእናቷ በኩል ግፊት ማድረግ ጀመሩ። ጁንታው የአብረኸትን እናት ሌት ተቀን በማስፈራራታቸው ልጃቸውን ሳይወዱ በግድ ለታጣቂው አስረከቡ፤ አብረኸትም ቤተሰቦቼን ለአደጋ ከማጋልጥ በሚል ታጣቂውን ተቀላቀለች።
“ሌላ ስራ በቀላሉ ማግኘት ስላልቻልኩና ጫናውና ማስፈራሪያው ሲበዛብኝ ታጣቂውን ተቀላቀልኩ። የቤተሰቡ አባላት ሰባት ነን ፤ አባቴ በህይወት የለም፡፡ እናቴ ብቻዋን ነው ጠላ ሽጣ ያሳደገችኝ፡፡ እሷን ለማገዝ ስልም ነው ወደዚህ የገባሁት” ስትልም ነው የታጣቂው አባል የሆነችበትን አጋጣሚ የምታስታውሰው።
አብረኸት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ እየወሰዱት ባለው ህግ የማስከበር እርምጃ ላይ እጇን የሰጠችው አንድም ጥይት ሳትተኩስ መሆኑን ትናገራለች፤ “150 ጥይት ተስጥቶኝ አንድም ጥይት ሳልተኩስ ነው እጄን የሰጠሁኝ። ምክንያቱም በዚህ ውጊያ አላምንበትም። እየሞተ ያለውም የደሀው ልጅ ነው። እጄን ከሰጠሁ በሁዋላም ቢሆን ሶስት ቀን ሙሉ የሰራዊቱ አባላት ከሚበሉትና ከሚጠጡት እያካፈሉኝ ቆይቻለሁ።
በትግራይ ክልል በየአካባቢው ያለው ወጣት ተገዶ ወደ ግዳጅ እንዲገባ ተደርጓል የምትለው ወጣቷ፤ ስልጠና የሚሰጠውም የይድረስ ይድረስ መሆኑን አልሸሸገችም፤ “ለአጭር ጊዜ ክላሽ እንዴት እንደሚፈታና እንደሚገጠም፣ ኢላማ እንዴት እንደሚመታ አሳይተው ብቻ ነው ወደ ጦርነት የሚማግዷቸው፡፡ ይህ ደግሞ የህወሓት አመራሮች ለትግራይ እናቶችም ሆነ ወጣቶች ደንታ እንደሌላቸውና የራሳቸውን የስልጣን ጥም ለማርካት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ያሳያል” ነው ያለችው፤ አብረኸት፡፡
“የህወሓት አመራሮች፤ የትግራይን ህዝብ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች እንደሚጠላው፣ የትም ሄደው በሰላም መኖር እንደማይችሉ አድርገው ወጣቱንንም ሆነ ህጻናትን ጭምር ይሰብካሉ። ሁሉም የትግራይ ህዝብ የዚህ አይነት አስተሳብ ስላለውና ህወሓትን ስለሚፈራ የሚሉትን ለማድረግ ይገደዳል። ይህ ሰላም የማይወድ ድርጅት ውጤት ለማያመጣ ነገር ወጣቱን እያስፈጀ ነው” ብላላች፤ አብረኸት።
የህወሓት ጁንታ ወጣቱን መስዋዕት የሚያስከፍሉት የማይሆን ነገር እየሞሉት፣ እያስገደዱትና፣ በገንዘብም እያታለለሉት ጭምር መሆኑን አብረኸት ትናገራለች።
የትግራይ ህዝብ መከላከያን እንዲወጋ አይፈልግም፤ ምክንያቱም መካላከያ የትግራይ ህዝብን ደህንነት ከመጠበቅ ጎን ለጎን ለህብረተሰቡ ትምህርት ቤት እየሰራ፣ ጤና ጣቢያ እየገነባ የኖረ ወገን ነው፤ የምትለው አብረኸት፤ “ወርቅ ለአበደረ ጠጠር እንዲሉ እኛን አታለው እንደ ቤተሰብ የምናየውን መከላከያ ሰራዊትን እንድንወጋ አድርገውናል” ያለችው በከፍተኛ ጸጸት ውስጥ ሆና ነው።
“የህወሓት ቡድን እንደሚለው መከላከያ እኛን ቢጠላን ኖሮ እንዴት ትግራይን ይጠብቃታል” ስትልም ትጠይቃለች። “እኛ ምንግዜም ኢትዮጵያዊ ነን፤ አጸያፊ ስራ እስካልሰራን ድረስ ህዝቡ ዝም ብሎ አይጠላንም፡፡ በመሆኑም የትግራይ ወጣቶች ዓላማ የሌለው ጦርነት ውስጥ መግባት የለባቸውም። ለመከላከያ ሰራዊት እጃቸውን በመስጠት በሰላም መኖር ይኖርባቸዋል” ስትል ሀሳቧን ቋጭታለች።
በጌትነት ምህረቴ
"በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
**************
(ኢ ፕ ድ)
"በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም" ሰል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
ሕወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መለየት
የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ሕገ ወጥ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሜ ያረጋግጣል:: ነገር ግን ይህ ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ ያወግዛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም፡፡
በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ ሳይቀር የከፋ በደል የሚፈጽመውን ይህን የሕወሐት ጁንታ የወንጀል ሰንሰለት ለማስቆም የፌዴራሉ መንግሥት ቆርጦ ተነሥቷል፡፡
በዚህ ሕግ የማስከበር ዘመቻ የትግራይ ሕዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ለኢትዮጵያ ያለን ራእይ በብዝኃነት የሚኮሩ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን ነው። በዚህ ሕዝባችን ላይ ምንም ዓይነት ክፉ ነገር እንዲደርስ አንፈልግም። ይሄንን የሚያደርጉትንም አንታገሥም።
ኅዳር 9 ቀን 2013
አዲስ አበባ
- ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
**************
(ኢ ፕ ድ)
"በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም" ሰል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
ሕወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መለየት
የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ሕገ ወጥ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሜ ያረጋግጣል:: ነገር ግን ይህ ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ ያወግዛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም፡፡
በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ ሳይቀር የከፋ በደል የሚፈጽመውን ይህን የሕወሐት ጁንታ የወንጀል ሰንሰለት ለማስቆም የፌዴራሉ መንግሥት ቆርጦ ተነሥቷል፡፡
በዚህ ሕግ የማስከበር ዘመቻ የትግራይ ሕዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ለኢትዮጵያ ያለን ራእይ በብዝኃነት የሚኮሩ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን ነው። በዚህ ሕዝባችን ላይ ምንም ዓይነት ክፉ ነገር እንዲደርስ አንፈልግም። ይሄንን የሚያደርጉትንም አንታገሥም።
ኅዳር 9 ቀን 2013
አዲስ አበባ
የሕወሐት ጁንታ የትግራይ መሠረተ ልማቶችን እያፈረሰ ነው።
***********
(ኢ ፕ ድ)
የመከላከያ ሠራዊት ወደፊት መገሥገሡ ያስጨነቀው ጁንታ፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ መቀሌ በሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት ድልድዮችን አፍርሷቸዋል።
የተማመነባቸው ከባድ ምሽጎቹ ፈራርሰው፣ በሽሬ መንገድ የደረሰበት ሽንፈት ያንገበገበው ጁንታ፣ በሽሬና በአኩስም መካከል የሚገኘውን አስፓልት በግሬደር ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታል።
የሕወሐት ጁንታው እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪ ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋል።
ምንጭ: የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ
***********
(ኢ ፕ ድ)
የመከላከያ ሠራዊት ወደፊት መገሥገሡ ያስጨነቀው ጁንታ፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ መቀሌ በሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት ድልድዮችን አፍርሷቸዋል።
የተማመነባቸው ከባድ ምሽጎቹ ፈራርሰው፣ በሽሬ መንገድ የደረሰበት ሽንፈት ያንገበገበው ጁንታ፣ በሽሬና በአኩስም መካከል የሚገኘውን አስፓልት በግሬደር ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታል።
የሕወሐት ጁንታው እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪ ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋል።
ምንጭ: የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ
የማይካድራው ጭፍጨፋ የዓይን እማኝ
******************
(ኢ ፐ ድ)
መላ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፤ ከንፈሩ ደርቋል። ለሁለት ቀናት ምግብ አላገኘም። ድንጋጤ አለቀቀውም። ከማይካድራ ግድያ አምልጦ ሁመራ ከተማ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በር ላይ ያገኘነው ወጣት ዳንኤል ማሚን።
የደቡብ ክልል የቴፒ ተወላጅ ነው፤ አገር ሰላም ብሎ በማይካድራ ልብስ እየነገደ መኖር ከጀመረ 13 ዓመት ሆኖታል። በዚች ከተማ ይህን ያህል ሲኖር የከፋ አይደለም፤ ቀለል ያለ ችግርም አጋጥሞት አያውቅም። በሚኖርባትና ህይወቱን ለማሻሻል በሚደክምባት ከተማ ቤትና ንብረትም አፍርቷል።
ከሰባት ቀናት በፊት ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በማይካድራ ከተማ በአማራና በሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ያልታሰበ፣ አስደንጋጭና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በዓይኑ ተመልክቷል ፤ እሱም ከዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አምልጦ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ወደ ዋለችው ሁመራ ከተማ መምጣቱን ይናገራል።
የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻዎች በአማራና በሌሎች ብሄሮች የፈጸሙት ግፍና ግድያ በጣም የሚያስደነግጥ ያልታሰበ ነበር የሚለው ወጣቱ፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ በምንኖር ንጹሐን ሰዎች ላይ በትግራይ ሚሊሻዎችና ልዩ ኃይሎች ዘግናኝ ጥቃት ይደርስብናል ብለን አስበንም አልመንም አናውቅም። ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ በከተማዋ በሚኖሩ አማራን ጨምሮ በሌሎች ብሄሮች ዘግናኝ ድርጊት ፈጸሙ ይላል።
“መጀመሪያ ላይ ጥቃቱን የጀመሩት በወልቃይት አማራዎች ላይ መሆኑን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ንጹሐን ሰዎችን በየመንገዱ እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ። ሰው ሮጦ እንዳያመልጥ እንኳን መንገዱ በሚሊሻ ተከቧል። ሩጠው ለማምለጥ የሚሞክሩትን በጭካኔ በጥይት እየመቱ ገድሏቸዋል” ብሏል ።
በአይኔ ሰው ሲገደል አይቻላሁ። እኔም የዳንኤል ቤት የትኛው ነው እያሉ ሲጠይቁ ሰምቼ ሩጬ ማምለጥ ችያለሁ የሚለው ወጣቱ፤ በዚህ ቀውጢ ስዓት እሱም ሆነ ብዙ በርካታ ሰዎች እየሮጡ ጫካ ባይገቡና ባያመልጡ ኖሮ በማይካድራ ከተማ በግፍ እንደተገደሉት ንጹሐን ሰዎች ሁሉ የእሱም ዕጣ ፋንታ በህወሓት አሸባሪ ቡድን ይገደል እንደነበር ነግሮናል።
ሰዎች ሲገደሉ በዓይኑ ማየቱን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ሁለቱ ከድብደባው ለማምለጥ ሲሮጡ በጥይት ሁለቱ ደግሞ በሳንጃ አንገታቸውን ተወገተው አስፓልት ላይ ሲወድቁ እግሬ አውጪኝ ብሎ ከአካባቢው ተሰውሮ ጫካ መግባቱን ንግሮናል። ሰው በጭካኔ እየተገደለ ባየሁበት ከተማ ለመኖር አልጓጓም ያለው ወጣቱ ከሁመራ ወደ ጎንደር ከዚያም ወደ ትውልድ አገሩ ቴፒ ለመሄድ መወሰኑን ገልጾልናል።
ወጣት ዳንኤል፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ የህወሓት ጸንፈኛ ቡድንን ያልደገፈ የሚደርስበት ጫና እንግልት ከፍተኛ መሆኑን ይናገራል። ለትግራይ ልማት የሚሆን ገንዘብ አዋጣ ሲሉኝ 100.00 ብር አዋጣሁ። ሁለተኛ ዙርም ለውጊያ አዋጣ አሉኝ ። እኔም ውጊያውን ስለማላምንበት ብር የለኝም አልኳቸው። ለካስ ያላዋጣነው ሰዎች የቀበሌው የህወሓት ተላላኪዎች የስም ዝርዝራችንን ይዘው ኑሯል፤ጊዜ ጠብቀው የበቀል ጭካኔያቸውን አወረዱብን።
በየመኖሪያ ቤታችን እየዞሩ እስከ ወዲያኛው ሊያስናብቱን እየገሰገሱ መጡ። እግዜአብሄር አትርፎኝ ይኸው ሁመራ ከተማ አግኝተኸኛል” ሲል የጭካኔያቸው ጥግና የበቀል ዕርምጃቸው ከባድ መሆኑን ገልጾታል።
ማይካድራ ከተማ ውስጥ የሚኖር ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከትግራይ ቴሌቪዥንና ከወያኔ ድምፅ ቴሌቪዥን በስተቀር ሌሎች የቴሌዥን ጣቢያዎችን ማየት ወንጀል ነው የሚለው ወጣቱ፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ ዋልታ፣ ፋና ቴሌቪዥንና ሌሎች ህወሓት የሚጠላቸውን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ማየት ፈጽሞ የተከለከለና የሚያስቀጣ ነው። ሲያይ የተገኘም ካለ በህይወቱ የፈረደ ሰው ብቻ ነው ይላል።
ማይካድራ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል ማይካድራ ለምን አትምለስም የሚል ጥያቄ አቅርበንለት የወጣቱ ምልሽ ሌላ አካባቢ ሊስትሮም ቢሆን ሠርቼ መኖርን እመርጣሉሁ እንጂ ሁለተኛ ትግራይ ክልል አልኖርም። ምክንያቱም ያየሁት የጭካኔ አገዳዳል ለሌት በህልሜ ይመጣብኛል። ዘግናኝ ነው። ይህን እያስብኩ እዚያ ከተማ መኖር አልፈልግም። ህይወቴ ተመሰቃቅሏል ሲልም ያየው የጭካን ተግባር የቱን ያህል እንደጎዳው፣ ከቃላቶቹ በላይ ሁኔታውን ሲያስታውስ የሚሰማው ስሜት ይናገራል።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም
******************
(ኢ ፐ ድ)
መላ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፤ ከንፈሩ ደርቋል። ለሁለት ቀናት ምግብ አላገኘም። ድንጋጤ አለቀቀውም። ከማይካድራ ግድያ አምልጦ ሁመራ ከተማ መከላከያ ሠራዊት ካምፕ በር ላይ ያገኘነው ወጣት ዳንኤል ማሚን።
የደቡብ ክልል የቴፒ ተወላጅ ነው፤ አገር ሰላም ብሎ በማይካድራ ልብስ እየነገደ መኖር ከጀመረ 13 ዓመት ሆኖታል። በዚች ከተማ ይህን ያህል ሲኖር የከፋ አይደለም፤ ቀለል ያለ ችግርም አጋጥሞት አያውቅም። በሚኖርባትና ህይወቱን ለማሻሻል በሚደክምባት ከተማ ቤትና ንብረትም አፍርቷል።
ከሰባት ቀናት በፊት ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በማይካድራ ከተማ በአማራና በሌሎች ብሄሮች ተወላጆች ላይ ያልታሰበ፣ አስደንጋጭና ዘግናኝ ግድያ ሲፈጸም በዓይኑ ተመልክቷል ፤ እሱም ከዚህ ዘግናኝ ጭፍጨፋ አምልጦ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ወደ ዋለችው ሁመራ ከተማ መምጣቱን ይናገራል።
የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻዎች በአማራና በሌሎች ብሄሮች የፈጸሙት ግፍና ግድያ በጣም የሚያስደነግጥ ያልታሰበ ነበር የሚለው ወጣቱ፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ በምንኖር ንጹሐን ሰዎች ላይ በትግራይ ሚሊሻዎችና ልዩ ኃይሎች ዘግናኝ ጥቃት ይደርስብናል ብለን አስበንም አልመንም አናውቅም። ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ በከተማዋ በሚኖሩ አማራን ጨምሮ በሌሎች ብሄሮች ዘግናኝ ድርጊት ፈጸሙ ይላል።
“መጀመሪያ ላይ ጥቃቱን የጀመሩት በወልቃይት አማራዎች ላይ መሆኑን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ንጹሐን ሰዎችን በየመንገዱ እየደበደቡ፤ በሳንጃ አንገታቸውን እየቀሉ ሲገሏቸው ተመልክቻለሁ። ሰው ሮጦ እንዳያመልጥ እንኳን መንገዱ በሚሊሻ ተከቧል። ሩጠው ለማምለጥ የሚሞክሩትን በጭካኔ በጥይት እየመቱ ገድሏቸዋል” ብሏል ።
በአይኔ ሰው ሲገደል አይቻላሁ። እኔም የዳንኤል ቤት የትኛው ነው እያሉ ሲጠይቁ ሰምቼ ሩጬ ማምለጥ ችያለሁ የሚለው ወጣቱ፤ በዚህ ቀውጢ ስዓት እሱም ሆነ ብዙ በርካታ ሰዎች እየሮጡ ጫካ ባይገቡና ባያመልጡ ኖሮ በማይካድራ ከተማ በግፍ እንደተገደሉት ንጹሐን ሰዎች ሁሉ የእሱም ዕጣ ፋንታ በህወሓት አሸባሪ ቡድን ይገደል እንደነበር ነግሮናል።
ሰዎች ሲገደሉ በዓይኑ ማየቱን የሚገልጸው ወጣት ዳንኤል ሁለቱ ከድብደባው ለማምለጥ ሲሮጡ በጥይት ሁለቱ ደግሞ በሳንጃ አንገታቸውን ተወገተው አስፓልት ላይ ሲወድቁ እግሬ አውጪኝ ብሎ ከአካባቢው ተሰውሮ ጫካ መግባቱን ንግሮናል። ሰው በጭካኔ እየተገደለ ባየሁበት ከተማ ለመኖር አልጓጓም ያለው ወጣቱ ከሁመራ ወደ ጎንደር ከዚያም ወደ ትውልድ አገሩ ቴፒ ለመሄድ መወሰኑን ገልጾልናል።
ወጣት ዳንኤል፤ በትግራይ ክልል ማይካድራ ከተማ የህወሓት ጸንፈኛ ቡድንን ያልደገፈ የሚደርስበት ጫና እንግልት ከፍተኛ መሆኑን ይናገራል። ለትግራይ ልማት የሚሆን ገንዘብ አዋጣ ሲሉኝ 100.00 ብር አዋጣሁ። ሁለተኛ ዙርም ለውጊያ አዋጣ አሉኝ ። እኔም ውጊያውን ስለማላምንበት ብር የለኝም አልኳቸው። ለካስ ያላዋጣነው ሰዎች የቀበሌው የህወሓት ተላላኪዎች የስም ዝርዝራችንን ይዘው ኑሯል፤ጊዜ ጠብቀው የበቀል ጭካኔያቸውን አወረዱብን።
በየመኖሪያ ቤታችን እየዞሩ እስከ ወዲያኛው ሊያስናብቱን እየገሰገሱ መጡ። እግዜአብሄር አትርፎኝ ይኸው ሁመራ ከተማ አግኝተኸኛል” ሲል የጭካኔያቸው ጥግና የበቀል ዕርምጃቸው ከባድ መሆኑን ገልጾታል።
ማይካድራ ከተማ ውስጥ የሚኖር ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከትግራይ ቴሌቪዥንና ከወያኔ ድምፅ ቴሌቪዥን በስተቀር ሌሎች የቴሌዥን ጣቢያዎችን ማየት ወንጀል ነው የሚለው ወጣቱ፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ ዋልታ፣ ፋና ቴሌቪዥንና ሌሎች ህወሓት የሚጠላቸውን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ማየት ፈጽሞ የተከለከለና የሚያስቀጣ ነው። ሲያይ የተገኘም ካለ በህይወቱ የፈረደ ሰው ብቻ ነው ይላል።
ማይካድራ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል ማይካድራ ለምን አትምለስም የሚል ጥያቄ አቅርበንለት የወጣቱ ምልሽ ሌላ አካባቢ ሊስትሮም ቢሆን ሠርቼ መኖርን እመርጣሉሁ እንጂ ሁለተኛ ትግራይ ክልል አልኖርም። ምክንያቱም ያየሁት የጭካኔ አገዳዳል ለሌት በህልሜ ይመጣብኛል። ዘግናኝ ነው። ይህን እያስብኩ እዚያ ከተማ መኖር አልፈልግም። ህይወቴ ተመሰቃቅሏል ሲልም ያየው የጭካን ተግባር የቱን ያህል እንደጎዳው፣ ከቃላቶቹ በላይ ሁኔታውን ሲያስታውስ የሚሰማው ስሜት ይናገራል።
በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ህዳር 8 ቀን 2013 ዓ.ም
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታምዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ ከፍተኛ የሆነ ሽንፈት ስለደረሰበት እና አብዛኛውን ግዛቱን እየተነጠቀ ስለሆነ ወደ ጥፋት ተልዕኮ እየገባ ነው።
እንደ ጠቅላይ ኢታምዦር ሹሙ ገለጻ፤ የጁንታው ታጣቂዎች ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሱ ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቶቹንና ተተኳሾቹን ቤተክርስቲያን ላይ አድርጓል።
የመከላከያ ሰራዊቱም ይሄንን በመገንዘብ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘራፊው ጁንታ በግሬደርና በዶዘር ታግዞ በከፍተኛ ሃብት የተሰራውን የአስፓልት መንገድ እየቆረጠ እና ድልድይ እያፈረሰ የሰራዊቱን እንቅስቃሴ ለመግታት ሙከራ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ለአብነት ያህልም በጨርጨር ግንባር ሶስት ድልድዮችን ማፍረሱን አስታውቀዋል።
በወንድወሰን ሽመልስ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሀዲው ጁንታ ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሰ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታምዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ከሀዲው የህወሓት ጁንታ ከፍተኛ የሆነ ሽንፈት ስለደረሰበት እና አብዛኛውን ግዛቱን እየተነጠቀ ስለሆነ ወደ ጥፋት ተልዕኮ እየገባ ነው።
እንደ ጠቅላይ ኢታምዦር ሹሙ ገለጻ፤ የጁንታው ታጣቂዎች ቤተ ክርስቲያኖች ውስጥ በመጠለል ከቤተ ክርስቲያን ወደ መከላከያ ሰራዊቱ እየተኮሱ ነው፡፡ ኮማንድ ፖስቶቹንና ተተኳሾቹን ቤተክርስቲያን ላይ አድርጓል።
የመከላከያ ሰራዊቱም ይሄንን በመገንዘብ ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዘራፊው ጁንታ በግሬደርና በዶዘር ታግዞ በከፍተኛ ሃብት የተሰራውን የአስፓልት መንገድ እየቆረጠ እና ድልድይ እያፈረሰ የሰራዊቱን እንቅስቃሴ ለመግታት ሙከራ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ብርሃኑ፤ ለአብነት ያህልም በጨርጨር ግንባር ሶስት ድልድዮችን ማፍረሱን አስታውቀዋል።
በወንድወሰን ሽመልስ
በምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት፤ በምዕራብ ወለጋ በጉሊሶ ዞን በአርሶ አደሩ ላይ ከተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ ወዲህ የኦሮሚያ ፖሊስ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ ቀጥለዋል።
በቅርቡም 142 በሚሆኑ የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገለጸው፤ 48 አባላት እጅ የሰጡ ሲሆን 64 የሚሆኑት ደግሞ ከህብረተሰቡ ውስጥ ቢቀላቀሉም እየተያዙ እንዳለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ ከሁለት ሳምንት ወዲህ በቅንጅት በተሰራው ስራ ይህንን ቡድን ከኦሮሚያ ለማፅዳት ጫካ ላለው ኦነግ ሸኔ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ 1 ሺህ 341 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለውል። ከነዚህ ውስጥ 104 የሚሆኑት የከሀዲው ህወሓት አባላት ናቸው፡፡
ቦንብን ጨምሮ 57 የጦር መሳሪያዎች ከ681 ጥይቶች ጋር መያዛቸውንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
አሁን ባለው ተጨባች ሁኔታ ኦነግ ሸኔ እና ከሃዲው የህወሓት ቡድን ለአንድ አላማ የሚሰሩ የጥፋት ሀይሎች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ኮሚሽነር መርዳሳ ማናገራቸውን የኦሮሚያ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡
በሀይማኖት ከበደ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በተሰራ ስራ 142 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት፤ በምዕራብ ወለጋ በጉሊሶ ዞን በአርሶ አደሩ ላይ ከተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ ወዲህ የኦሮሚያ ፖሊስ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ ቀጥለዋል።
በቅርቡም 142 በሚሆኑ የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገለጸው፤ 48 አባላት እጅ የሰጡ ሲሆን 64 የሚሆኑት ደግሞ ከህብረተሰቡ ውስጥ ቢቀላቀሉም እየተያዙ እንዳለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ ከሁለት ሳምንት ወዲህ በቅንጅት በተሰራው ስራ ይህንን ቡድን ከኦሮሚያ ለማፅዳት ጫካ ላለው ኦነግ ሸኔ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ 1 ሺህ 341 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለውል። ከነዚህ ውስጥ 104 የሚሆኑት የከሀዲው ህወሓት አባላት ናቸው፡፡
ቦንብን ጨምሮ 57 የጦር መሳሪያዎች ከ681 ጥይቶች ጋር መያዛቸውንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡
አሁን ባለው ተጨባች ሁኔታ ኦነግ ሸኔ እና ከሃዲው የህወሓት ቡድን ለአንድ አላማ የሚሰሩ የጥፋት ሀይሎች መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ኮሚሽነር መርዳሳ ማናገራቸውን የኦሮሚያ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡
በሀይማኖት ከበደ
ገቢዎች ሚኒስቴር በአራት ወራት ውስጥ ከ107 ነጥብ 8 ቢለዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት ለመሰብሰብ ካደቀው 104 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ 107 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አቶ ላቀ አያሌው አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ17.3 ቢሊየን ብር እድገት ማሳየቱን ጠቅሰው የህግ ተገዢነት ደረጃ መሻሻል፣ የተቋሙ ሰራተኛና አመራሮች ቁርጠኝነት መጨመር እና የገቢው መሰረትን ለማስፋት የተደረጉ ጥረቶች ገቢው እንዲጨምር ከሚጠቀሱ ምክንያቶች መካከል ናቸው።
እንደ አቶ ላቀ ገለጻ፤ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶችም በአራት ወራት መጠናከራቸውን ለገቢ አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡
ህግን ለማስከበር ከተከናወኑ ተግብራት መካከል የኮንትሮባንድ ክትትል አንዱ ሲሆን በወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የተገኘ መሆኑን አስታውቀዋል።
የፌደራል እና የክልል የጸጥታ አካላት፣ የጉምሩክ ኮምሽን ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች አጋር አካላት ሚና የላቀ በመሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት ለመሰብሰብ ካደቀው 104 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ 107 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አቶ ላቀ አያሌው አስታወቁ፡፡
ሚኒስትሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ17.3 ቢሊየን ብር እድገት ማሳየቱን ጠቅሰው የህግ ተገዢነት ደረጃ መሻሻል፣ የተቋሙ ሰራተኛና አመራሮች ቁርጠኝነት መጨመር እና የገቢው መሰረትን ለማስፋት የተደረጉ ጥረቶች ገቢው እንዲጨምር ከሚጠቀሱ ምክንያቶች መካከል ናቸው።
እንደ አቶ ላቀ ገለጻ፤ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶችም በአራት ወራት መጠናከራቸውን ለገቢ አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡
ህግን ለማስከበር ከተከናወኑ ተግብራት መካከል የኮንትሮባንድ ክትትል አንዱ ሲሆን በወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የተገኘ መሆኑን አስታውቀዋል።
የፌደራል እና የክልል የጸጥታ አካላት፣ የጉምሩክ ኮምሽን ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች አጋር አካላት ሚና የላቀ በመሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአዲስ አበባ ባለቤት ያልተገኘላቸው ህንጻዎች 100 መድረሳቸውን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የከተማዋ ወጣቶች ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በከተማዋ የሚገኙ ህንጻዎች፣ ታጥረው የሚገኙ መሬቶች እና የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ እየተደረገ ባለው ዳሰሳ እስካሁን 100 ህንጻዎች ባለቤት አልተገኘላቸውም።
እንደ ኢቢሲ.ዘገባ፤ ከዚህም በተጨማሪ ታጥሮ የተቀመጠ ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ባለቤት ሳይገኝለት ቀርቷል።
በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ ቤቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ወጣቶች በትግራይ ክልል እየተደረገ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውን ገልጸዋል።
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የከተማዋ ወጣቶች ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በከተማዋ የሚገኙ ህንጻዎች፣ ታጥረው የሚገኙ መሬቶች እና የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ እየተደረገ ባለው ዳሰሳ እስካሁን 100 ህንጻዎች ባለቤት አልተገኘላቸውም።
እንደ ኢቢሲ.ዘገባ፤ ከዚህም በተጨማሪ ታጥሮ የተቀመጠ ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ባለቤት ሳይገኝለት ቀርቷል።
በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ ቤቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ወጣቶች በትግራይ ክልል እየተደረገ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውን ገልጸዋል።