በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም ስምምነት ተፈረመ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለው ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ተቋሙ በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የሚቋቋም ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት መሆኑን ገልጸዋል።
በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የሚስተዋለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን የሚቀርፍ መሆኑን ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብና በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት የተቀመጠውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #የቤት_መግዣ_ብድር #ብሔራዊ_ባንክ #IFC #የፋይናንስ_ዘርፍ #የቤት_ልማት #ኢትዮጵያ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለው ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ተቋሙ በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የሚቋቋም ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት መሆኑን ገልጸዋል።
በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የሚስተዋለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን የሚቀርፍ መሆኑን ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ እንደሚሆን ገልጸዋል።
ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብና በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት የተቀመጠውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #የቤት_መግዣ_ብድር #ብሔራዊ_ባንክ #IFC #የፋይናንስ_ዘርፍ #የቤት_ልማት #ኢትዮጵያ
❤6👍3
ኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን ለማቀላጠፍ በ83 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 መርከቦችን ልትገዛ ነው
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ አሁን ካሏት 10 መርከቦች በተጨማሪ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 16 መርከቦችን ለመግዛት አቅዳ የስድስት መርከቦች ግዥ በሂደት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዋና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ኃይለማርያም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ለወጪና ገቢ ምርቶች ከምትጠቀምባቸው 10 መርከቦች በተጨማሪ 16 መርከቦችን ለመግዛት አቅዳለች፡፡
መርከቦቹን በቀጣይ አምስት ዓመታት ለመግዛት የታቀደ ሲሆን፤ ለዚህም 83 ነጥብ1 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ገልፀው መርከቦችን በግዥ የኢትዮጵያ የማድረግ ሥራ የተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅዶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ስድስት መርከቦች ሕጋዊ የግዥ ሥርዓት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ የሚገኙ መርከቦች ጠቅላላ የመሸከም አቅም ከ25ሺ እስከ 28ሺ ሲሆን፤ የአዳዲሶቹ መጫን አቅም ከቀድሞቹ አንጻር ሲታይ ግዙፍና ከ50ሺ እስከ 63ሺ የመጫን አቅም ያላቸው ናቸው ብለዋል፡፡
የመርከቦቹ ግዥ በሀገሪቱ ስትራቴጂክ የሆኑ ግብዓቶችን ጨምሮ በርካታ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንዲሁም ወደ ውጭ የሚላከውን በቅልጥፍናና በወቅቱ በመላክ የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴን ውጤታማነት ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በድርጅቱ መርከቦች፣ በስሎትና በኪራይ መርከቦች ብትን ዕቃን ጨምሮ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን ገቢ ዕቃ ለማጓጓዝ ታቅዶ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ቶን አጓጉዟል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት የመሆን ሕልሟን ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ጥረት እያደረገች መሆኗን የገለጹት አቶ ስንታየሁ፤ ይህን ውጥን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በክፍለዮሐንስ አንበርብር
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት#ጋዜጣፕላስ #መርከብ ግዥ#ገቢና ወጭ ምርቶች#ንግድ #ኢኮኖሚ#ኢትዮጵያ
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ አሁን ካሏት 10 መርከቦች በተጨማሪ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 16 መርከቦችን ለመግዛት አቅዳ የስድስት መርከቦች ግዥ በሂደት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዋና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ኃይለማርያም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ለወጪና ገቢ ምርቶች ከምትጠቀምባቸው 10 መርከቦች በተጨማሪ 16 መርከቦችን ለመግዛት አቅዳለች፡፡
መርከቦቹን በቀጣይ አምስት ዓመታት ለመግዛት የታቀደ ሲሆን፤ ለዚህም 83 ነጥብ1 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ገልፀው መርከቦችን በግዥ የኢትዮጵያ የማድረግ ሥራ የተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅዶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ስድስት መርከቦች ሕጋዊ የግዥ ሥርዓት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ የሚገኙ መርከቦች ጠቅላላ የመሸከም አቅም ከ25ሺ እስከ 28ሺ ሲሆን፤ የአዳዲሶቹ መጫን አቅም ከቀድሞቹ አንጻር ሲታይ ግዙፍና ከ50ሺ እስከ 63ሺ የመጫን አቅም ያላቸው ናቸው ብለዋል፡፡
የመርከቦቹ ግዥ በሀገሪቱ ስትራቴጂክ የሆኑ ግብዓቶችን ጨምሮ በርካታ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እንዲሁም ወደ ውጭ የሚላከውን በቅልጥፍናና በወቅቱ በመላክ የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴን ውጤታማነት ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በድርጅቱ መርከቦች፣ በስሎትና በኪራይ መርከቦች ብትን ዕቃን ጨምሮ 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን ገቢ ዕቃ ለማጓጓዝ ታቅዶ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ቶን አጓጉዟል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት የመሆን ሕልሟን ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ጥረት እያደረገች መሆኗን የገለጹት አቶ ስንታየሁ፤ ይህን ውጥን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በክፍለዮሐንስ አንበርብር
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት#ጋዜጣፕላስ #መርከብ ግዥ#ገቢና ወጭ ምርቶች#ንግድ #ኢኮኖሚ#ኢትዮጵያ
❤6😁1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የማንሠራራት ቀንን (ጳጉሜ 2ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት
++++++++++++
ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!
ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል።
ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።
#EthiopiaDelivers
++++++++++++
ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!
ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል።
ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።
#EthiopiaDelivers
👍6❤4
"ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ጉዞ፤ በተግባር የታነጸበት ስራ" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
+++++++++++++
ዛሬ በሞጆ ተገኝተን ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት ትልቅ ሚና የሚጫወተውንና በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፍያ የመጀመሪያ ምዕራፍ አስመርቀናል።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት እስከ አንድ ሚሊዮን ባለ 20 ጫማ ኮንቴነሮች የማስተናገድ አቅም ያላቸው ጣቢያዎችና ዘመናዊ መጋዘኖች ያሉት ሲሆን፣ የደረቅ ብትን ጭነቶችን በሀገር ውስጥ እንድናሽግ ማስቻሉ፣ የውጭ ምንዛሬን ከመቆጠብ ባለፈ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
የማዕከሉን የአሰራር ፍጥነት ለማሳደግ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተተከለው የባቡር ላይ ክሬን ከባቡር መስመር የሚደረገውን የኮንቴነር ዝውውር በከፍተኛ ፍጥነት ያከናውናል።
ሙሉ አሰራሩ በዘመናዊ ዲጂታል መሰረተ ልማት የተሳሰረ በመሆኑ፣ ለተገልጋዮች ፈጣን እና አስተማማኝ አገልግሎትን ያሳልጣል። ይህ ማዕከል ከኢትዮ-ጅቡቲ መስመር ባሻገር ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን የሚያስተሳስረው የ‘ደሱ’ ኮሪደር አካል ሲሆን፤ ይህም ሀገራችን በዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ደረጃ ላይ ያላትን ስፍራ የሚያሻሽልና የቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስራችንን ወደ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ትልቅ ድል ነው።
#EthiopiaDelivers
+++++++++++++
ዛሬ በሞጆ ተገኝተን ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት ትልቅ ሚና የሚጫወተውንና በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፍያ የመጀመሪያ ምዕራፍ አስመርቀናል።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት እስከ አንድ ሚሊዮን ባለ 20 ጫማ ኮንቴነሮች የማስተናገድ አቅም ያላቸው ጣቢያዎችና ዘመናዊ መጋዘኖች ያሉት ሲሆን፣ የደረቅ ብትን ጭነቶችን በሀገር ውስጥ እንድናሽግ ማስቻሉ፣ የውጭ ምንዛሬን ከመቆጠብ ባለፈ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
የማዕከሉን የአሰራር ፍጥነት ለማሳደግ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተተከለው የባቡር ላይ ክሬን ከባቡር መስመር የሚደረገውን የኮንቴነር ዝውውር በከፍተኛ ፍጥነት ያከናውናል።
ሙሉ አሰራሩ በዘመናዊ ዲጂታል መሰረተ ልማት የተሳሰረ በመሆኑ፣ ለተገልጋዮች ፈጣን እና አስተማማኝ አገልግሎትን ያሳልጣል። ይህ ማዕከል ከኢትዮ-ጅቡቲ መስመር ባሻገር ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን የሚያስተሳስረው የ‘ደሱ’ ኮሪደር አካል ሲሆን፤ ይህም ሀገራችን በዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ደረጃ ላይ ያላትን ስፍራ የሚያሻሽልና የቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስራችንን ወደ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ትልቅ ድል ነው።
#EthiopiaDelivers
❤2