የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን ዛሬ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮው ማየት ይቻላል
- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
+++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽበት አድራሻ ይፋ ማድረጉን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል።
#Ethiopia #ExaminationResult #12Class #ExamResult #education #EthiopiaProgress
- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
+++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽበት አድራሻ ይፋ ማድረጉን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል።
#Ethiopia #ExaminationResult #12Class #ExamResult #education #EthiopiaProgress
❤1
ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ ችሏል።
ተማሪ ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል።
በከተማ አስተዳደሩም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል ብለዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ መሆኗንም ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራትና ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል።
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ ችሏል።
ተማሪ ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል።
በከተማ አስተዳደሩም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል ብለዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ መሆኗንም ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራትና ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል።
❤7
ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው።
በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል።
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ።
ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq
#PMOEthiopia
በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል።
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ።
ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq
#PMOEthiopia
❤8😁1
የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - የጎቤ እና የሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት የወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ገለጹ።
የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የጎቤ እና የሺኖዬ ጨዋታ በኦሮሞ ባህልና እሴት መሠረት ሊከበር የሚገባውና የዘመን መለወጫ ማብሰሪያ ባህላዊ ጨዋታ ነው።
ባህላዊ ጨዋታው ጥንታዊ የኦሮሞ ባህልና እሴቶችን የተከተለ መሆን እንዳለበት የጠቀሱት አባ ገዳ ጌቱ፤ ጎቤ እና ሺኖዬን ከባህላዊ እሴቱ ውጭ ለገቢ ማስገኛነት መጠቀም እንደማይቻል ተናግረዋል።
የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ያሉ ልጃገረዶችና ወጣቶች ተሰባስበው የሚጫወቱት ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የገለጹት አባ ገዳው፤ በዓሉ ከጭጋጋማው የክረምት ወራት ወደ ፀደይ ብርሃን የመሸጋገሪያ ብስራት የሚበሰርበት መሆኑንም አብራርተዋል።
የዘንድሮው የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ከነሐሴ 16 ቀን ጀምሮ እየተከበረ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ ጌታቸው በበኩላቸው፤ ጎቤ እና ሺኖዬ በመንገዶች ላይና ቤት ለቤት በመሄድ የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት፣ እንዲሁም አንድነትና ፍቅር በአደባባይ የሚታይበት በዓል መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት በዓሉን ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ የሚረዳ መሆኑንም ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ አክለው ተናግረዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ጎቤና_ሺኖዬ #የኦሮሞ_ባህል #የገዳ_ሥርዓት #ኦሮሚያ #ኢፕድ #ኢትዮጵያ
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - የጎቤ እና የሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት የወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ገለጹ።
የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የጎቤ እና የሺኖዬ ጨዋታ በኦሮሞ ባህልና እሴት መሠረት ሊከበር የሚገባውና የዘመን መለወጫ ማብሰሪያ ባህላዊ ጨዋታ ነው።
ባህላዊ ጨዋታው ጥንታዊ የኦሮሞ ባህልና እሴቶችን የተከተለ መሆን እንዳለበት የጠቀሱት አባ ገዳ ጌቱ፤ ጎቤ እና ሺኖዬን ከባህላዊ እሴቱ ውጭ ለገቢ ማስገኛነት መጠቀም እንደማይቻል ተናግረዋል።
የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ያሉ ልጃገረዶችና ወጣቶች ተሰባስበው የሚጫወቱት ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የገለጹት አባ ገዳው፤ በዓሉ ከጭጋጋማው የክረምት ወራት ወደ ፀደይ ብርሃን የመሸጋገሪያ ብስራት የሚበሰርበት መሆኑንም አብራርተዋል።
የዘንድሮው የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ከነሐሴ 16 ቀን ጀምሮ እየተከበረ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ ጌታቸው በበኩላቸው፤ ጎቤ እና ሺኖዬ በመንገዶች ላይና ቤት ለቤት በመሄድ የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት፣ እንዲሁም አንድነትና ፍቅር በአደባባይ የሚታይበት በዓል መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት በዓሉን ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ የሚረዳ መሆኑንም ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ አክለው ተናግረዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ጎቤና_ሺኖዬ #የኦሮሞ_ባህል #የገዳ_ሥርዓት #ኦሮሚያ #ኢፕድ #ኢትዮጵያ
❤1
የሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ኃይል የማመንጭት አቅም ያለው የኮይሻ ግድብ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ ደርሷል
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተገነባ የሚገኘውና የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል ተብሎ የሚጠበቀው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሽብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለመገናኛ ብዙኃን ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ግድቡን በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በሦስት ቢሊዮን ዩሮ ወጪ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል።
የኮይሻ ግድብን በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በከፊል ሥራ ለማስጀመር ግብ ተይዞ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ያህል ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ይህ ግድብ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት በማሳደግ ረገድ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
የኮይሻ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት ከመቀየር ባለፈ ለዘላቂ ልማት ትልቅ ምሰሶ እንደሚሆን ይጠበቃል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኮይሻ_ግድብ #ኢትዮጵያ_ኤሌክትሪክ_ኃይል #የውኃ_ኃይል_ማመንጫ #የሕዳሴ_ግድብ #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ኢትዮጵያ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተገነባ የሚገኘውና የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል ተብሎ የሚጠበቀው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሽብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለመገናኛ ብዙኃን ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ግድቡን በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በሦስት ቢሊዮን ዩሮ ወጪ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል።
የኮይሻ ግድብን በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በከፊል ሥራ ለማስጀመር ግብ ተይዞ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ያህል ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ይህ ግድብ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት በማሳደግ ረገድ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
የኮይሻ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት ከመቀየር ባለፈ ለዘላቂ ልማት ትልቅ ምሰሶ እንደሚሆን ይጠበቃል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኮይሻ_ግድብ #ኢትዮጵያ_ኤሌክትሪክ_ኃይል #የውኃ_ኃይል_ማመንጫ #የሕዳሴ_ግድብ #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ኢትዮጵያ
❤8
የህዳሴ ግድብ በሀብታችን የመጠቀም ጅማሮ እንጂ መጨረሻ አይደለም ሲሉ የውሃ ምህንድስና ተመራማሪው ገለጹ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ፡ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የገነባችው ግድብ ጅማሮ መሆኑንና ገና በርካታ ሥራዎች ሊከናወኑ እንደሚችሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውኃ ምሕንድስና መምህሩ ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ገለጹ።
የውኃ ምሕንድስና መምህሩ ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከዓባይ ወንዝ ገና መጠቀም ጀመረች እንጂ የማንንም ጥቅም አልነካችም። ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ተጠቅማ የሕዳሴ ግድብን በመገንባቷ ምንም ዓይነት ቅሬታ የሚያስነሳባት ጉዳይ እንደሌለም ተናግረዋል።
የዓባይ ወንዝ 45 ሺህ ጊጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችል አቅም እንዳለው የጠቆሙት ፕሮፌሰር ይልማ፤ ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ላይ የምታከናውናቸው ሥራዎች የተደበቁ ሳይሆኑ በግልጽ ለሁሉም በሚታይ መልኩ የሰፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የዓባይ ወንዝ ከኢትዮያ የሚነሳ ሀብቷ ቢሆንም የታችኛውም ሆነ የላይኛው ተፋሰስ ሀገራትን በሚጠቅምና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ያስቀመጠችው እውነታ እንደሆነም አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን ሕግ የተላለፈችበት ጊዜ እንደሌለ የገለጹት ፕሮፌሰር ይልማ፤ አሁንም ቢሆን ፍትሐዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ወንዙን ለሌሎች አገልግሎቶች የመጠቀም ሙሉ መብት እንዳላት አስረድተዋል።
የግብፅ ጩኸት የውኃ መጠን ቀንሶባት ሳይሆን ቀደም ሲል በበላይነት የመጠቀም አሠራሯ እንዳያበቃ ከመስጋት የመነጨ መሆኑንም ፕሮፌሰሩ አክለው ገልጸዋል።
የህዳሴ ግድብ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱና ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣፕላስ #ዓባይወንዝ #የሕዳሴግድብ #የውኃምሕንድስና #ኢፕድ #ኢትዮጵያ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ፡ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የገነባችው ግድብ ጅማሮ መሆኑንና ገና በርካታ ሥራዎች ሊከናወኑ እንደሚችሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውኃ ምሕንድስና መምህሩ ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ገለጹ።
የውኃ ምሕንድስና መምህሩ ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከዓባይ ወንዝ ገና መጠቀም ጀመረች እንጂ የማንንም ጥቅም አልነካችም። ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብት ተጠቅማ የሕዳሴ ግድብን በመገንባቷ ምንም ዓይነት ቅሬታ የሚያስነሳባት ጉዳይ እንደሌለም ተናግረዋል።
የዓባይ ወንዝ 45 ሺህ ጊጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችል አቅም እንዳለው የጠቆሙት ፕሮፌሰር ይልማ፤ ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ላይ የምታከናውናቸው ሥራዎች የተደበቁ ሳይሆኑ በግልጽ ለሁሉም በሚታይ መልኩ የሰፈሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የዓባይ ወንዝ ከኢትዮያ የሚነሳ ሀብቷ ቢሆንም የታችኛውም ሆነ የላይኛው ተፋሰስ ሀገራትን በሚጠቅምና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ያስቀመጠችው እውነታ እንደሆነም አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን ሕግ የተላለፈችበት ጊዜ እንደሌለ የገለጹት ፕሮፌሰር ይልማ፤ አሁንም ቢሆን ፍትሐዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ወንዙን ለሌሎች አገልግሎቶች የመጠቀም ሙሉ መብት እንዳላት አስረድተዋል።
የግብፅ ጩኸት የውኃ መጠን ቀንሶባት ሳይሆን ቀደም ሲል በበላይነት የመጠቀም አሠራሯ እንዳያበቃ ከመስጋት የመነጨ መሆኑንም ፕሮፌሰሩ አክለው ገልጸዋል።
የህዳሴ ግድብ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱና ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣፕላስ #ዓባይወንዝ #የሕዳሴግድብ #የውኃምሕንድስና #ኢፕድ #ኢትዮጵያ
❤5👍1