ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል።
«አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል።
«አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።
❤11👍2👏2
አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሪከርድን ሰበረ
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቦነስ አይረስ በተካሄደው ውድድር የግማሽ ማራቶን ሪከርድ ሰብሯል። አትሌቱ ርቀቱን በ56 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በማጠናቀቅ አዲስ የዓለም ሪከርድ አስመዝግቧል።
በዚህም አትሌት ዮሚፍ ዩጋንዳዊው ጃኮብ ኪፕሊሞ ከዚህ በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 57 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ የዓለም ሪከርድ በ29 ሴከንዶች በማሻሻል የርቀቱ የዓለም ፈጣን አትሌት መሆኑን አረጋግጧል።
#WorldAthletics #TrackAndField #Athletics #TrackNation #DiamondLeague #World #Championships #DistanceRunning #TrackField #RoadToVictory
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቦነስ አይረስ በተካሄደው ውድድር የግማሽ ማራቶን ሪከርድ ሰብሯል። አትሌቱ ርቀቱን በ56 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በማጠናቀቅ አዲስ የዓለም ሪከርድ አስመዝግቧል።
በዚህም አትሌት ዮሚፍ ዩጋንዳዊው ጃኮብ ኪፕሊሞ ከዚህ በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 57 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ የዓለም ሪከርድ በ29 ሴከንዶች በማሻሻል የርቀቱ የዓለም ፈጣን አትሌት መሆኑን አረጋግጧል።
#WorldAthletics #TrackAndField #Athletics #TrackNation #DiamondLeague #World #Championships #DistanceRunning #TrackField #RoadToVictory
❤14👍3🔥1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
++++++++++++++++++
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።
የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡
ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡
ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡
ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡
የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡ በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
++++++++++++++++++
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።
የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡
ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡
ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡
ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡
የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡ በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
❤10😁3
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን ዛሬ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮው ማየት ይቻላል
- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
+++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽበት አድራሻ ይፋ ማድረጉን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል።
#Ethiopia #ExaminationResult #12Class #ExamResult #education #EthiopiaProgress
- የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
+++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽበት አድራሻ ይፋ ማድረጉን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል።
#Ethiopia #ExaminationResult #12Class #ExamResult #education #EthiopiaProgress
❤1
ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ ችሏል።
ተማሪ ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል።
በከተማ አስተዳደሩም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል ብለዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ መሆኗንም ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራትና ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል።
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ ችሏል።
ተማሪ ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል።
በከተማ አስተዳደሩም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል ብለዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ መሆኗንም ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራትና ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል።
❤6
ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው።
በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል።
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ።
ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq
#PMOEthiopia
በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል።
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ።
ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq
#PMOEthiopia
❤4😁1