Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ የጎበኙት የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ በፎቶ‼️
#EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia
4😁1
ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
+++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ│በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል።

በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት ተችሏል።

ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።

በታደሠ ብናልፈው

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #የወጪ #ገቢ #ንግድ #ንግድናቀጠናዊትስስር #ኢትዮጵያ
1😁1
በአዲስ አበባ 543 ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏበከተማው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ መቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ወስኗል።

የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናውን ከወሰዱት ከ97 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል። 543 ትምህርት ቤቶችም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል።

የማለፊያ ነጥብ ለመደበኛ ተማሪዎች 50 በመቶ እንዲሁም 45 በመቶ ለአካል ጉዳተኞች መወሰኑን ተናግረዋል።

በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በቀንና በማታ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ85 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸው፤ በዘንድሮው ፈተና ሁለት ተማሪዎች 98 አማካይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመዋል።

459 ተማሪዎች 95 እና ከዚያ በላይ አማካይ ማስመዝገባቸውን ጠቅሰው፤አምስት ሺህ 559 የሚሆኑት ከ90 በላይ አማካይ ያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል።

አጠቃላይ ውጤቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በሁለት ነጥብ አራት በመቶ እድገት ማሳየቱንም ገልጸው፣ ከዛሬ ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በኦላይን መመልከት የሚችሉ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #AddisAbaba #AddisAbabaEducation #Grade6Exam
👍3
ኢትዮጵያ 33 ሚሊየን ቶን ስንዴ በዓመት እያመረተች ትገኛለች
+++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ - "በአፍሪካ ትልቋ የስንዴ አምራች ሀገር ግብጽ ነበረች፤ በአመት 9.7 ሚሊዮን ቶን ታመርት ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ በጣም ያነሰ ነበር የምታመርተው። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች።

ይህም ቀዳሚ አምራች የነበረችውን ግብጽን በ3 እጥፍ መብለጥ ያስቻለን ትልቅ ድል ነው ብለዋል።

በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት ማሳያ ነው።

#Ethiopia #Wheat #AfricaNo1 #WheatProduction #AgriculturalTransformation #Rising
6😁6
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዚዳንት ጋር ያደረጉት ውይይት‼️
#COP32 #COP32Ethiopia #PMOEthiopia #gazette_plus #Ethiopiadelivers
2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ኢትዮጵያ እየመከረች ነው" – 5ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ
++++++++++++++

"ኢትዮጵያ እየመከረች ነው" በሚል ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓም የሚካሄድ አምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዘጋጅቷል።

በዚህ ታሪካዊ ስፖርታዊ መርሐግብር ላይ ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሩጫው ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ ዜጎች ሁሉ እንድትሳተፉ ኮሚሽኑ ጥሪውን አቅርቧል።

#ሀገራዊ_ምክክር #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው #የጎዳና_ላይ_ሩጫ #ሐምሌ_5 #ሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን #የምክክር_ሩጫ #EthiopianNationalDialogue #Ethiopia
2👍2
በመደመር መንግሥት የኢኮኖሚ ስትራቴጂ የታገዘው የግብርናው ዘርፍ፣ ፈጣን ዕድገትን በማረጋገጥ የሀገራችንን ራስን የመቻል ርዕይ እውን እያደረገ ይገኛል።

‎የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እና የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ዘርፉ ለሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማይናወጥ መሠረት ሆኗል። ይኸው ወሳኝ እመርታ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አማካኝነት በሀገር በቀል መፍትሔዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት መለወጥና የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል በተግባር እያሳየን ነው።

‎በጋራ እናልማ፣ እናምርት፣ እንበልጽግ!

#EthiopiaDelivers
#PMOEthiopia
3👎2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ስራ አሰጀመሩ
++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ የደብረ ማርቆስና የአካባቢው ሕዝብ ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውና ለ30 ዓመታት ያህል ተቋርጦ የነበረው ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የአውሮፕላን ማረፊያ፤ በዘመናዊ መልክ ተሻሽሎና ደረጃው ከፍ ብሎ ተገንብቶ ዛሬ መመረቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።

በ2,400 ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ላይ የተገነባው እንደ Q400 እና B737 ያሉ ግዙፍ የሕዝብና የጭነት አውሮፕላኖችን ማሳረፍ የሚያስችል ከፍተኛ ዐቅምም ፈጥሯል።

ይህ አውሮፕላን ማረፊያ ሥራ መጀመሩ የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ለአካባቢው እና ለመላው ሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል።

ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር፤ የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስና የጀመርናቸውን ሜጋ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለምርቃት ለማብቃት ያለንን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየን እንቀጥላለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

#NationalDialogue #ሀገራዊምክክር #ኤርፖርት #airport Ethiopian Airlines
4