Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ የጎበኙት የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ በፎቶ‼️
#EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia
4😁1
ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
+++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ│በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል።

በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት ተችሏል።

ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።

በታደሠ ብናልፈው

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #የወጪ #ገቢ #ንግድ #ንግድናቀጠናዊትስስር #ኢትዮጵያ
1😁1
በአዲስ አበባ 543 ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏበከተማው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ መቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ወስኗል።

የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናውን ከወሰዱት ከ97 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል። 543 ትምህርት ቤቶችም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል።

የማለፊያ ነጥብ ለመደበኛ ተማሪዎች 50 በመቶ እንዲሁም 45 በመቶ ለአካል ጉዳተኞች መወሰኑን ተናግረዋል።

በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በቀንና በማታ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ85 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸው፤ በዘንድሮው ፈተና ሁለት ተማሪዎች 98 አማካይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመዋል።

459 ተማሪዎች 95 እና ከዚያ በላይ አማካይ ማስመዝገባቸውን ጠቅሰው፤አምስት ሺህ 559 የሚሆኑት ከ90 በላይ አማካይ ያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል።

አጠቃላይ ውጤቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በሁለት ነጥብ አራት በመቶ እድገት ማሳየቱንም ገልጸው፣ ከዛሬ ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በኦላይን መመልከት የሚችሉ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #AddisAbaba #AddisAbabaEducation #Grade6Exam
👍3
ኢትዮጵያ 33 ሚሊየን ቶን ስንዴ በዓመት እያመረተች ትገኛለች
+++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ - "በአፍሪካ ትልቋ የስንዴ አምራች ሀገር ግብጽ ነበረች፤ በአመት 9.7 ሚሊዮን ቶን ታመርት ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ በጣም ያነሰ ነበር የምታመርተው። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች።

ይህም ቀዳሚ አምራች የነበረችውን ግብጽን በ3 እጥፍ መብለጥ ያስቻለን ትልቅ ድል ነው ብለዋል።

በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት ማሳያ ነው።

#Ethiopia #Wheat #AfricaNo1 #WheatProduction #AgriculturalTransformation #Rising
6😁6
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዚዳንት ጋር ያደረጉት ውይይት‼️
#COP32 #COP32Ethiopia #PMOEthiopia #gazette_plus #Ethiopiadelivers
2