የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‼️
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባችንን ተከትሎ፣ እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጎብኝተናል።
በዚህ ሳይት ሦስት የላቁ የግንባታ ዘዴዎች በጥምረት ጥቅም ላይ ውለዋል፤ የ3ዲ ህትመት፣ የቅድመ-ዝግጅት ቀላል የአረብ ብረት ግንባታና የኮንቴይነር መኖሪያ ቤቶች ናቸው።
እያንዳንዳቸው ግንባታዎች ትክክለኛውን ቴክኖሎጂ ስንጠቀም ጥራታቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን ከወራትና ከዓመታት ይልቅ በጥቂት ቀናትና ሳምንታት ውስጥ ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት ህያው ምስክር ናቸው።
ይህ አይነቱ የላቀ ፈጠራ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በቀላሉ ሊተገበር፣ ሊደገምና ሊስፋፋ የሚችል በመሆኑ የሀገራችንን የቤት ልማት ፕሮግራም አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ የመቀየር ኃይል አለው።
ቴክኖሎጂን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር አጣምረናል፤ መሰል በተግባር የተገለጡ ስራዎቻችን ደግሞ ለሀገር የሚገባውን ፈጣን ዕድገት እውን ለማድረግ በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ በቁርጠኝነት እየተጓዝን መሆናችንን በተግባር አሳይቷል።
#ኢትዮጵያ #ታዳሽኃይል Office of the Prime Minister-Ethiopia #technology #TechHouse
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባችንን ተከትሎ፣ እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጎብኝተናል።
በዚህ ሳይት ሦስት የላቁ የግንባታ ዘዴዎች በጥምረት ጥቅም ላይ ውለዋል፤ የ3ዲ ህትመት፣ የቅድመ-ዝግጅት ቀላል የአረብ ብረት ግንባታና የኮንቴይነር መኖሪያ ቤቶች ናቸው።
እያንዳንዳቸው ግንባታዎች ትክክለኛውን ቴክኖሎጂ ስንጠቀም ጥራታቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን ከወራትና ከዓመታት ይልቅ በጥቂት ቀናትና ሳምንታት ውስጥ ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት ህያው ምስክር ናቸው።
ይህ አይነቱ የላቀ ፈጠራ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በቀላሉ ሊተገበር፣ ሊደገምና ሊስፋፋ የሚችል በመሆኑ የሀገራችንን የቤት ልማት ፕሮግራም አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ የመቀየር ኃይል አለው።
ቴክኖሎጂን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር አጣምረናል፤ መሰል በተግባር የተገለጡ ስራዎቻችን ደግሞ ለሀገር የሚገባውን ፈጣን ዕድገት እውን ለማድረግ በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ በቁርጠኝነት እየተጓዝን መሆናችንን በተግባር አሳይቷል።
#ኢትዮጵያ #ታዳሽኃይል Office of the Prime Minister-Ethiopia #technology #TechHouse
❤12
"በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮችን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ መታቀዱንም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። ለዚህም ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች” ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከተጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማትና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሠልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ሥልጠናውን አጠናቀዋል ብለዋል።
ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ እንደሆነም ጠቁመዋል።
እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጊዜያቸውን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥበው በመመዝገብ እና በመማር ወደ ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው የዲጂታል መሪዎች እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፣ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ- ethiocoders.et/
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮችን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ መታቀዱንም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። ለዚህም ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች” ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከተጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማትና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሠልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ሥልጠናውን አጠናቀዋል ብለዋል።
ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ እንደሆነም ጠቁመዋል።
እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጊዜያቸውን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥበው በመመዝገብ እና በመማር ወደ ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው የዲጂታል መሪዎች እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፣ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ- ethiocoders.et/
❤10
አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል። በመጨረሻው የማስተር ፕላን አቅሙ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ለማስተናገድ የተወጠነ ሲሆን፣ ይህም አሁን ካለው የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የማስተናገድ አቅም ጋር ሲነጻጸር በ4.4 እጥፍ ብልጫ ይኖረዋል።
ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት፣ ሀገራችንን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ፣ በደረሰበት ሁሉ ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርጎ የሚያሳይና የአኅጉራችን ኩራት በሆነው በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት በአፍሪካና ከዚያም ባሻገር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል!
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት፣ ሀገራችንን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ፣ በደረሰበት ሁሉ ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርጎ የሚያሳይና የአኅጉራችን ኩራት በሆነው በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት በአፍሪካና ከዚያም ባሻገር ያለውን ትስስር ለማጠናከር ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል!
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
👏4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መረሐግብር የችግኝ ተከላ በቢሾፍቱ ሲያስጀምሩ
#GreenLegacy #ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #AfricaRising #አረንጓዴዐሻራ #water
#GreenLegacy #ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #AfricaRising #አረንጓዴዐሻራ #water
"የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ግንባታ አትችሉም ለሚሉን እንደምንችል የምናሳይበት ፕሮጀክት ነው"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማሪፊያ ፕሮጀክት አትችሉም ለሚሉን እንደምንችል፣ የአፍሪካን አቅም ለዓለም የምናሳይበት ፕሮጀክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ፕሮጀክቱ ሲታሰብ ጀምሮ በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬ እንደነበርም ጠቅሰዋል።
በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ከ8ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ግንባታን በጎበኙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ የቢሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የማሰብ፣ የማቀድና የመስራት አቅም ለአለም የሚያሳይ ግዙፍ ስራ ነው ብለዋል።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም እንደነበሩትና በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚዘገዩት ፕሮጀክቶች ሳይሆን በከፍተኛ ክትትል የሚመራ፤ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ የሚጠናቀቅ እንደሆነም ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ ጅማሮ ላይ ብዙዎች አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ስራውን መምራት አይሆንላችሁም፣ ለምን ታስባላችሁ የሚል የተስፋ ማስቆረጥ ምልከታ እንደነበራቸው አስታውሰው፤ እኛ ግን እንችላለን፣ ይገባናል የሚመጥነን ፕሮጀክት ነው ብለን በተግባር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
የኤርፖርቱ ግንባታ በትልቅነቱ፣ በሚመደብለት ሃብትና በአጠቃላይ በሚያንቀሳቅሰው ማሽነሪ በአፍሪካ ደረጃ ትልቁ ፕሮጀክት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በግንባታው ሂደት የሚገጥሙ በርካታ ፈተናዎችን በመፍታት ፕሮጀክቱን ማሳካት እንደሚቻል በተግባር እየታየ ይገኛል ብለዋል።
በልማቱ ምክንያት የተነሱ የአካባቢው አርሶ አደሮች የቤት ግንባታና የቢዝነስ ተቋማት መደራጀታቸውንና በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚጎዳ አርሶ አደር እንደማይኖርና ሙሉ በሙሉ ህይወታቸው እንደሚሻሻል አረጋግጠዋል።
በፕሮጀክቱ ከ8 ሺህ በላይ ሠራተኞች እንደሚገኙና እስከ 4 ሺህ የሚጠጉ ማሽነሪዎችና መኪናዎች እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው፣ ለማሽኖቹና ለመኪናዎች አገልግሎት በቀን ከ650 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ጥቅም ላይ ይውላል ብለዋል።
በብዙ ሀገራት ብሎም በኢትዮጵያ የሥራ ሐሳብና ሀብት ቢኖርም፤ የፕሮጀክት አመራር ችግር ስላለ ፕሮጀክቶች መቼ ተጀምረው መቼ እንደሚጠናቀቁና እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው በቂ ግንዛቤ አለመኖሩን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ በረከት ነው፤ ለልጆቻችንም ትልቅ መሰረት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያን ድህነት ለመስበር፣ የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን በጋራ ለማየት በጋራ እንዲቆምና እንዲተባባር ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በአማን ረሺድ እና በሀብታሙ በውቀት
#ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #ሜጋ_ፕሮጀክት #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #አፍሪካ #BishoftuAirport #AfricanExcellence #Infrastructure #AfricaRising
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማሪፊያ ፕሮጀክት አትችሉም ለሚሉን እንደምንችል፣ የአፍሪካን አቅም ለዓለም የምናሳይበት ፕሮጀክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ፕሮጀክቱ ሲታሰብ ጀምሮ በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬ እንደነበርም ጠቅሰዋል።
በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ከ8ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ግንባታን በጎበኙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ የቢሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የማሰብ፣ የማቀድና የመስራት አቅም ለአለም የሚያሳይ ግዙፍ ስራ ነው ብለዋል።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም እንደነበሩትና በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚዘገዩት ፕሮጀክቶች ሳይሆን በከፍተኛ ክትትል የሚመራ፤ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ የሚጠናቀቅ እንደሆነም ገልጸዋል።
በፕሮጀክቱ ጅማሮ ላይ ብዙዎች አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ስራውን መምራት አይሆንላችሁም፣ ለምን ታስባላችሁ የሚል የተስፋ ማስቆረጥ ምልከታ እንደነበራቸው አስታውሰው፤ እኛ ግን እንችላለን፣ ይገባናል የሚመጥነን ፕሮጀክት ነው ብለን በተግባር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
የኤርፖርቱ ግንባታ በትልቅነቱ፣ በሚመደብለት ሃብትና በአጠቃላይ በሚያንቀሳቅሰው ማሽነሪ በአፍሪካ ደረጃ ትልቁ ፕሮጀክት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በግንባታው ሂደት የሚገጥሙ በርካታ ፈተናዎችን በመፍታት ፕሮጀክቱን ማሳካት እንደሚቻል በተግባር እየታየ ይገኛል ብለዋል።
በልማቱ ምክንያት የተነሱ የአካባቢው አርሶ አደሮች የቤት ግንባታና የቢዝነስ ተቋማት መደራጀታቸውንና በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚጎዳ አርሶ አደር እንደማይኖርና ሙሉ በሙሉ ህይወታቸው እንደሚሻሻል አረጋግጠዋል።
በፕሮጀክቱ ከ8 ሺህ በላይ ሠራተኞች እንደሚገኙና እስከ 4 ሺህ የሚጠጉ ማሽነሪዎችና መኪናዎች እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው፣ ለማሽኖቹና ለመኪናዎች አገልግሎት በቀን ከ650 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ጥቅም ላይ ይውላል ብለዋል።
በብዙ ሀገራት ብሎም በኢትዮጵያ የሥራ ሐሳብና ሀብት ቢኖርም፤ የፕሮጀክት አመራር ችግር ስላለ ፕሮጀክቶች መቼ ተጀምረው መቼ እንደሚጠናቀቁና እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው በቂ ግንዛቤ አለመኖሩን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ በረከት ነው፤ ለልጆቻችንም ትልቅ መሰረት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያን ድህነት ለመስበር፣ የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን በጋራ ለማየት በጋራ እንዲቆምና እንዲተባባር ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በአማን ረሺድ እና በሀብታሙ በውቀት
#ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #ሜጋ_ፕሮጀክት #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #አፍሪካ #BishoftuAirport #AfricanExcellence #Infrastructure #AfricaRising
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን።
ዜጎች ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል።
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን።
ዜጎች ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል።
❤9👏1😁1🏆1