Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ መደበኛ ስራ እንደማይኖር ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
+++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።

በዚህም መሠረት፤

✍️ ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣

✍️ ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤

✍️ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

✍️ የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችንና ዕቅዶችን እንዳይይዙና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

#ምርጫ #ኢትዮጵያ Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ #gazette_plus
😁2
"ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን"
-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

++++++++++++++++

#ጋዜጣ-ፕላስ | ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በበሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል። ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል"

በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት@ጋዜጣ-ፕላስ#በምርጫብቻ#ዲሞክራሲ#ምርጫ2018#ኢትዮጵያ#አርባምንጭ #EthiopianElection 2026#ዐቢይ አሕመድ
7👍2🥱2
የኢዜማ ፓርቲ መሪ አቶ ኢዮብ መሳፍንት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ድምፃቸውን ሰጡ

++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በባሕርዳር ምርጫ ክልል ህዳሴ ምርጫ ጣቢያ(02-1) በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በመካሄድ ላይ ሲሆን የባሕርዳር ከተማ ነዋሪዎችም በ164 የምርጫ ጣቢያዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

በአማን ረሺድ
8
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቋል
+++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ ትናንት የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ የድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ በስኬት ተጠናቅቋል ። በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅት እና የድኅረ ምርጫ ሥራዎች በአግባቡ ተከናውነዋል።

የመራጮች ምዝገባ፣ የእጩዎች ምዝገባ፣ ምርጫ ለሚታዘቡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የመመዝገብ እንዲሁም ለሌሎችም አካላት ፈቃድ የመስጠት የቅድመ ምርጫ ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ የተጠናቀቁ ሲሆን፤ በትናንትናው ዕለት በተካሄደው የድምጽ አሰጣጥ ሒደት በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን አስረድተዋል።

እንደ እሳቸው ገለጻ፣ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ማለዳ 12:00 ክፍት ተደርገው ድምጽ ተሰጥቶባቸዋል። የሲቪክ ማኅበራትም በየምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ታዝበዋል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) ታዛቢዎች ከማለዳው 12:00 ጀምሮ ሲታዘቡ ውለዋል።

በብዙ አካባቢዎች የድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ ከተጠናቀቀበት ሰዓት ጀምሮ ድምጾች የተቆጠሩ ሲሆን፤ የድምጽ አሰጣጡ ዘግይቶ በተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ ቆጠራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቆጠራው እንደተጠናቀቀ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ በሚቀጥሉት ቀናት ይፋ ይደረጋል። ከድምጽ አሰጣጥና ከቆጠራ ጋር በተገናኘ የሚመጡ ጥቆማዎችን በማጣራት ቦርዱ በሕግ አግባብ እርምጃ እንደሚወስድም ገልጸዋል።

በአብዱረዛቅ መሐመድ

#Ethiopianelection2026 #GeneralElection #EthiopiaVotes #NEBE #AfricanUnion #IGAD
6
በብስክሌት “ሜትር ታክሲ”
+++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- የታክሲ ሰልፉ ረዥም ነው። ስንት ሰዓት ነው ወረፋ የሚደርሰኝ? ታክሲ ባገኝ ደግሞ መንገዱ ይዘጋጋል። በሰዓቴ ሥራ ቦታ መገኘት ይኖርብኛል። ታዲያ ምን ይሻለኛል? ብሎ ለሚጨነቅ ሰው ጭንቀቱን የሚጋራና የሚያቃልል ችግር ፈቺ ስታርትአፕ ተፈጥሯል። ከወጪ አንፃር ገንዘብ ቆጣቢ ጤናም ለመጠበቅ የሚያስችል፤ እንግልትን የሚቀንስ ብስክሌትን በመጠቀም አዲስ ሥራ ይዘን መጥተናል ያሉ ወጣቶች ዘመን ኢኮኖሚ አነጋግራቸዋለች። ወጣቶቹ ስለ ፈጠራ ሥራቸው ያብራራሉ ።

እንደ ሜትር ታክሲ አገልግሎት ብስክሌትን በማጋራት ትራንስፖርትን ማቀላጠፍ ይቻላል ብለው የተነሱ ወጣቶች ዳይናሚክ የተሰኘ አክሲዮን ማኅበር መሠረቱ። ድርጅታቸው መሥራት ካሰባቸው ሥራዎች አንዱ የትራንስፖርት ዘርፍ ነውና አንድ ለውጥ የሚያመጣ ሥራ መሥራት አለብን በሚል ሐሳብ “ፔዳል ፍላይ” የሚል ስያሜ አውጥተው ወደ ትራንስፖርት ዘርፍ ተቀላቀሉ።https://press.et/
7👍3