የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ - በባህልና ስፖርት ዘርፍ - የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት የባህልበ ስፖርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ፤ ከለውጡ በፊት ዘርፉ ከነበሩበት ክፍተቶች መካከል፤ ለአደባባይ ክብረ በዓላት ትኩረት ማነስ፣ ባህላዊ የፍትህና ዳኝነት ስርዓትን ያለመጠቀም፣ የአካታችነት ችግር እንዲሁም የባህል እሴቶችን ለአንድነት ያለመጠቀም ከብዙ ጥቂቶች ናቸው።
የለውጡ መንግሥት ለነዚህ ክፍተቶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ዘርፉ ወሳኝ ለውጦች እንዲያስመዘግብ መደላድል ፈጥሯል። ከስኬቶቹም፤ ለ83 ክብረ በዓላት እውቅና መስጠትና መከበር፣ 36 አዲስ ባህል ማዕከላት መገንባት፣ ዲጂታል የቅርስ መረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋት፣ የባህልና የብዝኃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራ፣ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙ የማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች፣ በርካታ ቤተ-መጻሃፍት ግንባታና የንባብ አገልግሎት መበራከት፣ ብዝሃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራና የሙያ ማህበራት መደራጀት እንዲሁም ዘርፉን ለዲፕሎማሲ ስኬት ከመጠቀም ባለፈ አደይ አበባን ጨምሮ 17,636 አዳዲስ ስታዲየሞች ግንባታ የዘርፉ ትልቅ እመርታዎች ናችው። #PMOEthiopia
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት የባህልበ ስፖርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ፤ ከለውጡ በፊት ዘርፉ ከነበሩበት ክፍተቶች መካከል፤ ለአደባባይ ክብረ በዓላት ትኩረት ማነስ፣ ባህላዊ የፍትህና ዳኝነት ስርዓትን ያለመጠቀም፣ የአካታችነት ችግር እንዲሁም የባህል እሴቶችን ለአንድነት ያለመጠቀም ከብዙ ጥቂቶች ናቸው።
የለውጡ መንግሥት ለነዚህ ክፍተቶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ዘርፉ ወሳኝ ለውጦች እንዲያስመዘግብ መደላድል ፈጥሯል። ከስኬቶቹም፤ ለ83 ክብረ በዓላት እውቅና መስጠትና መከበር፣ 36 አዲስ ባህል ማዕከላት መገንባት፣ ዲጂታል የቅርስ መረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋት፣ የባህልና የብዝኃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራ፣ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙ የማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች፣ በርካታ ቤተ-መጻሃፍት ግንባታና የንባብ አገልግሎት መበራከት፣ ብዝሃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራና የሙያ ማህበራት መደራጀት እንዲሁም ዘርፉን ለዲፕሎማሲ ስኬት ከመጠቀም ባለፈ አደይ አበባን ጨምሮ 17,636 አዳዲስ ስታዲየሞች ግንባታ የዘርፉ ትልቅ እመርታዎች ናችው። #PMOEthiopia
❤2
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ - በትምህርት ዘርፍ - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፤ ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት ዕጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች ነበሩ።
በዚህም በጥናት በተደገፈ መልኩ፤ የትምህርት ዘርፉን ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች በመለየት ከተመዘገቡ ዋና ዋና ለውጦች መካከል፤ የሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ፣ የመፅሃፍት ህትመት ስርጭትና ተደራሽነት፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻል፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ዲጂታል ትምህርት መስፋፋት፣ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር መሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማደግ ዋነኞቹ በለውጡ ተግባራዊ የሆኑና ውጤት ያስገኙ ሆነው ተመዝግበዋል።
#PMOEthiopia
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፤ ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት ዕጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች ነበሩ።
በዚህም በጥናት በተደገፈ መልኩ፤ የትምህርት ዘርፉን ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች በመለየት ከተመዘገቡ ዋና ዋና ለውጦች መካከል፤ የሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ፣ የመፅሃፍት ህትመት ስርጭትና ተደራሽነት፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻል፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ዲጂታል ትምህርት መስፋፋት፣ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር መሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማደግ ዋነኞቹ በለውጡ ተግባራዊ የሆኑና ውጤት ያስገኙ ሆነው ተመዝግበዋል።
#PMOEthiopia
❤1
ከ800 በላይ የቱሪስት መስህቦች ተለይተዋል
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን ለመለየትና ለመመዝገብ በተከናወኑ ስራዎች እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎች በሦስት ደረጃዎች ተለይተው መመዝገባቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡
ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙና እስካሁን ያልታወቁ የቱሪስት መስህቦችን የመለየትና የመመዝገብ ሥራ በበጀት ዓመቱ በስፋት ሲከናወን ቆይቷል።
በዚህም እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎችን በመለየት በሦስት ደረጃዎች መድቦ ማስቀመጥ መቻሉን ጠቁመው፤ እነዚህ ደረጃዎች የተለዩት የመስህቦቹ የመልማት አቅም፣ ከየአካባቢው ያላቸው ተደራሽነትና ሊሠራባቸው በሚችሉ ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት መሆኑን አስረድተዋል።
የተለዩ ሀብቶች በትንሽ የኢንቨስትመንት ድጋፍ መልማት የሚችሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የመስህቦቹን መገኛና ዝርዝር ሁኔታ ማወቅ ለዘርፉ ልማት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አመላክተዋል።
ለዚህ የልማት ተግባር ስኬታማነት ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት እንዲሁም ከሕዝቡ የሚጠበቀውን ድርሻ የማስተባበር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሀገሪቱ ያሉ የቱሪስት መስህቦች 800 ብቻ እንዳልሆኑ የገለጹት ሰላማዊት ካሳ፤ አሁን የተከናወነው የመለየት ሥራ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እነዚህን ሀብቶች በማልማትና ለቱሪዝም ክፍት በማድረግ ረገድ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን ለመለየትና ለመመዝገብ በተከናወኑ ስራዎች እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎች በሦስት ደረጃዎች ተለይተው መመዝገባቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡
ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙና እስካሁን ያልታወቁ የቱሪስት መስህቦችን የመለየትና የመመዝገብ ሥራ በበጀት ዓመቱ በስፋት ሲከናወን ቆይቷል።
በዚህም እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎችን በመለየት በሦስት ደረጃዎች መድቦ ማስቀመጥ መቻሉን ጠቁመው፤ እነዚህ ደረጃዎች የተለዩት የመስህቦቹ የመልማት አቅም፣ ከየአካባቢው ያላቸው ተደራሽነትና ሊሠራባቸው በሚችሉ ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት መሆኑን አስረድተዋል።
የተለዩ ሀብቶች በትንሽ የኢንቨስትመንት ድጋፍ መልማት የሚችሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የመስህቦቹን መገኛና ዝርዝር ሁኔታ ማወቅ ለዘርፉ ልማት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አመላክተዋል።
ለዚህ የልማት ተግባር ስኬታማነት ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት እንዲሁም ከሕዝቡ የሚጠበቀውን ድርሻ የማስተባበር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሀገሪቱ ያሉ የቱሪስት መስህቦች 800 ብቻ እንዳልሆኑ የገለጹት ሰላማዊት ካሳ፤ አሁን የተከናወነው የመለየት ሥራ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እነዚህን ሀብቶች በማልማትና ለቱሪዝም ክፍት በማድረግ ረገድ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።
❤8😁2👍1
"የአራዳ ፓርክ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ስራችን ነው"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
የአራዳ ፓርክ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ስራችን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት አዲሱን የአራዳ ፓርክ መርቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ቀደም ሲል ተዘንግቶና ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው የአራዳ አካባቢ፣ ዛሬ ተመልሶ ተገንብቶ አስደናቂ የከተማ አካል መሆን መቻሉን ገልጸዋል።
"ኢትዮጵያ ለእኛ በምናብ የምትሳል ህልም ብቻ ሳትሆን በተግባር የምትገነባ እውነታ ናት" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ጤናማ፣ ጽኑ፣ ለመጭው ትውልድ ተስፋን ከተጨባጭ ሀብት ጋር የምትሰጥ፣ በአፍሪካ መሪ፣ በዓለም መድረክ ደግሞ ተወዳዳሪ የሆነች ሀገር እየተገነባች መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት በየቀኑ ይህንን ተስፋ ወደ እውነታ የመለወጥ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #አራዳፓርክ #EthiopiaDelivers
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
የአራዳ ፓርክ አዲስ አበባን ለመለወጥ ያለንን ርዕይ በተግባር ያሳየንበት አንዱ ስራችን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት አዲሱን የአራዳ ፓርክ መርቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ቀደም ሲል ተዘንግቶና ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው የአራዳ አካባቢ፣ ዛሬ ተመልሶ ተገንብቶ አስደናቂ የከተማ አካል መሆን መቻሉን ገልጸዋል።
"ኢትዮጵያ ለእኛ በምናብ የምትሳል ህልም ብቻ ሳትሆን በተግባር የምትገነባ እውነታ ናት" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ጤናማ፣ ጽኑ፣ ለመጭው ትውልድ ተስፋን ከተጨባጭ ሀብት ጋር የምትሰጥ፣ በአፍሪካ መሪ፣ በዓለም መድረክ ደግሞ ተወዳዳሪ የሆነች ሀገር እየተገነባች መሆኑን አስታውቀዋል።
መንግሥት በየቀኑ ይህንን ተስፋ ወደ እውነታ የመለወጥ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
#ጋዜጣ_ፕላስ #አራዳፓርክ #EthiopiaDelivers
👍4❤3😁1
ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻን ጎብኝቻለው።
ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊየን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው።
በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻ ዘመናዊ ማሽኖች እና በቴክኖሎጂ የተዋቀረ ነው። ማምረቻው ለበርካታ ዜጎች የስራ እድልም ፈጥሯል።
በመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ጌጋዋት ዓመታዊ የማምረት አቅም ያለው ፋብሪካው የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ኃይል ለማድረግ ለተጀመረው ሃገራዊ ርዕይ እውን ለማድረግ ተደማሪ አቅም ፈጥሯል።
በኢንደስትሪ ፓርኩ ውስጥ የሚገኘውን የጫማ ማምረቻ እና ንዑስ የኤሌክትሪክ ጣቢያን ተመልክቻለው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊየን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው።
በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው "ጎበዝ ሶላር ሴል" ማምረቻ ዘመናዊ ማሽኖች እና በቴክኖሎጂ የተዋቀረ ነው። ማምረቻው ለበርካታ ዜጎች የስራ እድልም ፈጥሯል።
በመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ጌጋዋት ዓመታዊ የማምረት አቅም ያለው ፋብሪካው የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከታዳሽ ኃይል ለማድረግ ለተጀመረው ሃገራዊ ርዕይ እውን ለማድረግ ተደማሪ አቅም ፈጥሯል።
በኢንደስትሪ ፓርኩ ውስጥ የሚገኘውን የጫማ ማምረቻ እና ንዑስ የኤሌክትሪክ ጣቢያን ተመልክቻለው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
❤10🔥5
በአፍሪካ የመጀመሪያው የከተሞች ማውንቴን ባይክ ዓለም አቀፍ ውድድር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
❤2