ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን ጋር ቀጣናችንን መልክ በሚያሲዙና የጋራ መፃኢ የልማት ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል።
የሁለቱን ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥነ ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብርና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የሁለቱን ሀገሮች በላቀ እድገትና ተጠቃሚነት ዙሪያ መረጃ የተለዋወጥነ ሲሆን፤ የኢኮኖሚ ትስስርን በጠንካራ ትብብርና በኢንቨስትመንት በመደገፍ እድሎችን የምናሰፋባቸውን የቀጣይ ስራዎች የተመለከተ ፍሬያማ ምክክር አድርገናል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
❤3👍1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡ ግዙፍ ፋብሪካዎችን መረቁ
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂንና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል።
በዛሬው ዕለት የተመረቁ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅንና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርቧሉ።
የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ዘላቂና የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
#EthiopiaDelivers #PMOEthiopia #solarenergy #greenenergy #ታዳሽኃይል
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተገነቡትን የቶዮ ሶላር ኢነርጂ ምዕራፍ ሁለት፣ የኦሪጂንና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎችን እንዲሁም የኤች.ዜድ ጋዝ ማምረቻ ፋብሪካን በይፋ መርቀዋል።
በዛሬው ዕለት የተመረቁ የሶላር ፋብሪካዎች በጋራ በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹሕ ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፣ የኤች.ዜድ ጋዝ ፋብሪካ ደግሞ በዓመት 900 ቶን ኦክስጅን፣ 40,000 ቶን ናይትሮጅንና 7 ቶን ሃይድሮጅን ለገበያ ያቀርቧሉ።
የኢትዮጵያን የታዳሽ ኃይል ልማት ለማፋጠን፣ የኢነርጂ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ዘላቂና የማይበገር ሁለንተናዊ እድገት ዕውን ለማድረግ የተነደፈውን ስትራቴጂ ለማሳካት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
#EthiopiaDelivers #PMOEthiopia #solarenergy #greenenergy #ታዳሽኃይል
👍3❤1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሞዛምቢኩ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ ደማቅ አቀባበል አደረጉ
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሞዛምቢክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖን በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የክብር አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የፕሬዝደንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ስራዎችን ቅድሚያ የሰጠ መሆኑም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። #PMOEthiopia #Mozambique #diplomacy #ዲፕሎማሲ #redsea #Tradein
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሞዛምቢክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖን በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የክብር አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የፕሬዝደንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ስራዎችን ቅድሚያ የሰጠ መሆኑም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። #PMOEthiopia #Mozambique #diplomacy #ዲፕሎማሲ #redsea #Tradein
👍7❤1
ሚኒስቴሩ ለቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውሉ 92 የኤሌክትሪክ ገልባጭ መኪኖችን ስራ አስጀመረ
+++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ 92 የኤሌክትሪክ ገልባጭ መኪኖችን ስራ አስጀምሯል፡፡
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ መኪኖች የመተካት ስራ በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነች ነው፡፡
ይህም ሀገሪቱ ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለዘላቂ ልማትና ለታዳሽ ኃይል የሰጠችውን የላቀ ትኩረት የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስና የዜጎችን የትራንስፖርት ወጪ ለመቆጠብ ጭምር እየሰራች እንደሆነም አመልክተዋል፡፡
አዲስ የገቡት የኤሌክትሪክ ገልባጭ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ እንደሚውሉ ገልጸዋል፡፡
መኪኖቹ ከቀረጥ ነጻ የገቡ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው÷ ሲሲሲሲ የተሰኘ የቻይና ካምፓኒ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቱን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
+++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ 92 የኤሌክትሪክ ገልባጭ መኪኖችን ስራ አስጀምሯል፡፡
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን እንዳሉት፣ ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ መኪኖች የመተካት ስራ በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነች ነው፡፡
ይህም ሀገሪቱ ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለዘላቂ ልማትና ለታዳሽ ኃይል የሰጠችውን የላቀ ትኩረት የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስና የዜጎችን የትራንስፖርት ወጪ ለመቆጠብ ጭምር እየሰራች እንደሆነም አመልክተዋል፡፡
አዲስ የገቡት የኤሌክትሪክ ገልባጭ ተሽከርካሪዎች ሙሉ በሙሉ ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ እንደሚውሉ ገልጸዋል፡፡
መኪኖቹ ከቀረጥ ነጻ የገቡ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው÷ ሲሲሲሲ የተሰኘ የቻይና ካምፓኒ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቱን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
❤5
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ - በባህልና ስፖርት ዘርፍ - የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት የባህልበ ስፖርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ፤ ከለውጡ በፊት ዘርፉ ከነበሩበት ክፍተቶች መካከል፤ ለአደባባይ ክብረ በዓላት ትኩረት ማነስ፣ ባህላዊ የፍትህና ዳኝነት ስርዓትን ያለመጠቀም፣ የአካታችነት ችግር እንዲሁም የባህል እሴቶችን ለአንድነት ያለመጠቀም ከብዙ ጥቂቶች ናቸው።
የለውጡ መንግሥት ለነዚህ ክፍተቶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ዘርፉ ወሳኝ ለውጦች እንዲያስመዘግብ መደላድል ፈጥሯል። ከስኬቶቹም፤ ለ83 ክብረ በዓላት እውቅና መስጠትና መከበር፣ 36 አዲስ ባህል ማዕከላት መገንባት፣ ዲጂታል የቅርስ መረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋት፣ የባህልና የብዝኃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራ፣ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙ የማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች፣ በርካታ ቤተ-መጻሃፍት ግንባታና የንባብ አገልግሎት መበራከት፣ ብዝሃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራና የሙያ ማህበራት መደራጀት እንዲሁም ዘርፉን ለዲፕሎማሲ ስኬት ከመጠቀም ባለፈ አደይ አበባን ጨምሮ 17,636 አዳዲስ ስታዲየሞች ግንባታ የዘርፉ ትልቅ እመርታዎች ናችው። #PMOEthiopia
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት የባህልበ ስፖርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ፤ ከለውጡ በፊት ዘርፉ ከነበሩበት ክፍተቶች መካከል፤ ለአደባባይ ክብረ በዓላት ትኩረት ማነስ፣ ባህላዊ የፍትህና ዳኝነት ስርዓትን ያለመጠቀም፣ የአካታችነት ችግር እንዲሁም የባህል እሴቶችን ለአንድነት ያለመጠቀም ከብዙ ጥቂቶች ናቸው።
የለውጡ መንግሥት ለነዚህ ክፍተቶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ዘርፉ ወሳኝ ለውጦች እንዲያስመዘግብ መደላድል ፈጥሯል። ከስኬቶቹም፤ ለ83 ክብረ በዓላት እውቅና መስጠትና መከበር፣ 36 አዲስ ባህል ማዕከላት መገንባት፣ ዲጂታል የቅርስ መረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋት፣ የባህልና የብዝኃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራ፣ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙ የማይዳሰሱ የባህል ቅርሶች፣ በርካታ ቤተ-መጻሃፍት ግንባታና የንባብ አገልግሎት መበራከት፣ ብዝሃ ልሳን ፖሊሲ ትግበራና የሙያ ማህበራት መደራጀት እንዲሁም ዘርፉን ለዲፕሎማሲ ስኬት ከመጠቀም ባለፈ አደይ አበባን ጨምሮ 17,636 አዳዲስ ስታዲየሞች ግንባታ የዘርፉ ትልቅ እመርታዎች ናችው። #PMOEthiopia
❤2
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ - በትምህርት ዘርፍ - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፤ ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት ዕጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች ነበሩ።
በዚህም በጥናት በተደገፈ መልኩ፤ የትምህርት ዘርፉን ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች በመለየት ከተመዘገቡ ዋና ዋና ለውጦች መካከል፤ የሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ፣ የመፅሃፍት ህትመት ስርጭትና ተደራሽነት፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻል፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ዲጂታል ትምህርት መስፋፋት፣ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር መሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማደግ ዋነኞቹ በለውጡ ተግባራዊ የሆኑና ውጤት ያስገኙ ሆነው ተመዝግበዋል።
#PMOEthiopia
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶች ቀርበዋል።
የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፤ ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት ዕጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች ነበሩ።
በዚህም በጥናት በተደገፈ መልኩ፤ የትምህርት ዘርፉን ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች በመለየት ከተመዘገቡ ዋና ዋና ለውጦች መካከል፤ የሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ፣ የመፅሃፍት ህትመት ስርጭትና ተደራሽነት፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻል፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ዲጂታል ትምህርት መስፋፋት፣ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር መሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማደግ ዋነኞቹ በለውጡ ተግባራዊ የሆኑና ውጤት ያስገኙ ሆነው ተመዝግበዋል።
#PMOEthiopia
❤1
ከ800 በላይ የቱሪስት መስህቦች ተለይተዋል
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን ለመለየትና ለመመዝገብ በተከናወኑ ስራዎች እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎች በሦስት ደረጃዎች ተለይተው መመዝገባቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡
ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙና እስካሁን ያልታወቁ የቱሪስት መስህቦችን የመለየትና የመመዝገብ ሥራ በበጀት ዓመቱ በስፋት ሲከናወን ቆይቷል።
በዚህም እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎችን በመለየት በሦስት ደረጃዎች መድቦ ማስቀመጥ መቻሉን ጠቁመው፤ እነዚህ ደረጃዎች የተለዩት የመስህቦቹ የመልማት አቅም፣ ከየአካባቢው ያላቸው ተደራሽነትና ሊሠራባቸው በሚችሉ ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት መሆኑን አስረድተዋል።
የተለዩ ሀብቶች በትንሽ የኢንቨስትመንት ድጋፍ መልማት የሚችሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የመስህቦቹን መገኛና ዝርዝር ሁኔታ ማወቅ ለዘርፉ ልማት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አመላክተዋል።
ለዚህ የልማት ተግባር ስኬታማነት ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት እንዲሁም ከሕዝቡ የሚጠበቀውን ድርሻ የማስተባበር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሀገሪቱ ያሉ የቱሪስት መስህቦች 800 ብቻ እንዳልሆኑ የገለጹት ሰላማዊት ካሳ፤ አሁን የተከናወነው የመለየት ሥራ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እነዚህን ሀብቶች በማልማትና ለቱሪዝም ክፍት በማድረግ ረገድ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን ለመለየትና ለመመዝገብ በተከናወኑ ስራዎች እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎች በሦስት ደረጃዎች ተለይተው መመዝገባቸውን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡
ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ፣ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙና እስካሁን ያልታወቁ የቱሪስት መስህቦችን የመለየትና የመመዝገብ ሥራ በበጀት ዓመቱ በስፋት ሲከናወን ቆይቷል።
በዚህም እስካሁን ከ800 በላይ የመስህብ ቦታዎችን በመለየት በሦስት ደረጃዎች መድቦ ማስቀመጥ መቻሉን ጠቁመው፤ እነዚህ ደረጃዎች የተለዩት የመስህቦቹ የመልማት አቅም፣ ከየአካባቢው ያላቸው ተደራሽነትና ሊሠራባቸው በሚችሉ ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት መሆኑን አስረድተዋል።
የተለዩ ሀብቶች በትንሽ የኢንቨስትመንት ድጋፍ መልማት የሚችሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የመስህቦቹን መገኛና ዝርዝር ሁኔታ ማወቅ ለዘርፉ ልማት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑንም አመላክተዋል።
ለዚህ የልማት ተግባር ስኬታማነት ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት እንዲሁም ከሕዝቡ የሚጠበቀውን ድርሻ የማስተባበር ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሀገሪቱ ያሉ የቱሪስት መስህቦች 800 ብቻ እንዳልሆኑ የገለጹት ሰላማዊት ካሳ፤ አሁን የተከናወነው የመለየት ሥራ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እነዚህን ሀብቶች በማልማትና ለቱሪዝም ክፍት በማድረግ ረገድ በቀጣይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።
❤8😁2👍1