Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.1K subscribers
41K photos
337 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
እንደ ሀገር ትኩረት ሰጥተን እየሰራንባቸው ከሚገኙት ምርቶች አንዱ የሆነው የበቆሎ መስኖ ስራችን ከፍ ባለ ስኬት ላይ ይገኛል።

የተገኘው ጅምር ውጤት፤ ኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ ከመቀበል ወጥታ ራሷን መመገብ የምትችል ሀገር የማድረግ ታላቁ ህልማችን እውን የሚሆንበት መንገድ ላይ ስለመሆኑ አመላካች ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍62👎1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለትውልድ መርሃግብር አካል የሆነውን የሀሮ ደንዲ ሎጅን ዛሬ በይፋ መርቀዋል። የደንዲ ሐይቅን ቁልቁል የሚመለከተው የሥነ-ምህዳር ቱሪዝም ልማት፣ ኢትዮጵያ ለከፍተኛ እና ዘላቂ የቱሪዝም ዘርፍ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
‎ይህ ስኬት ኢትዮጵያ ያለመችውን ዳር እንደምታደርስ ህያው ምስክር ነው!

‎ሀገራችን ተፈጥሯዊ ውበቷን ካልተቆጠበ ጥረት ጋር በማቀናጀት፣ የራሷን መጻኢ ዕድል በራሷ የመገንባት ዐቅም እንዳላት በድጋሚ በተግባር ያረጋገጠችበት ስኬት ነው።

#VisitEthiopia #EthiopiaDelivers #PMOEthiopia
13👎2
ዛሬ ጠዋት የአውሮፓ ኅብረት የአለምአቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጆሴፍ ሲከላን አግኝቼ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ስላለን የረጅም ጊዜ ትብብር ተወያይተናል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
3
የልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ ኢንሼቲቮችን በመለየት መተግበር.......

‎ከ100 ቀናት ሪፖርት እና ከ9 ወራት የሥራ አፈፃፀም የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ሥር የተቀረጹት ስድስት ታላላቅ ውጥኖች በመላ ሀገሪቱ የሚታይ ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።

✍️ አረንጓዴ ዐሻራ፦ የሀገሪቱ የደን ሽፋን 23.6 በመቶ ደርሷል። በዚህም የአርሶ አደሮች ገቢ እያደገ፣ አረንጓዴ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ፣ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ሥራዎች እየተከናወኑ እንዲሁም ሥነ-ምህዳሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጤናማ እየሆነ መጥቷል።

✍️ ሀገራዊ የስንዴ ልማት፦ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና ሉዓላዊነትን እያረጋገጠች ትገኛለች። አዳዲስ የግብርና ዕውቀቶች እየተስፋፉ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ግብዓቶችን እያገኙ፣ ውድ የሆኑ የውጭ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የሥራ ዕድሎች እየሰፉና የአርሶ አደሮች ገቢ እየጨመረ ይገኛል።

✍️ የሌማት ትሩፋት፦ የግብርና ግብዓቶች አቅርቦት እና ምርታማነት እየጨመረ ነው። የተመጣጠነ ምግብ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገኝ ከማድረግ ባለፈ፣ አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡና አካባቢው ይበልጥ እንዲጠበቅ እያደረገ ይገኛል።

✍️ ዲጂታል ኢትዮጵያ፦ የሕግ፣ የፋይናንስ እና የማንነት መታወቂያ (ID) ሥርዓቶች ወደ ዲጂታል እየተቀየሩ ነው። የኢንተርኔት ተደራሽነትና የኦንላይን አገልግሎቶች እየተስፋፉ፣ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ ንግድ የዜጎችን ጊዜና ገንዘብ እያተረፈ ነው።

✍️ የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት፦ የከተሞች መሠረተ ልማት በአረንጓዴ ትራንስፖርት እየዘመነ ነው። ይህም የዜጎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻለ፣ የአካባቢ ንግድን እያነቃቃ እንዲሁም በከተማና በገጠር መካከል ያለውን ትስስር እያጠናከረ ይገኛል።

✍️ ‎ኢትዮጵያ ታምርት፦ የማምረት አቅምና የምርቶች እሴት የመጨመር ሂደት እየተሻሻለ ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተተኩ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝት እያደገ፣ የግብዓት አቅርቦት እየተጠናከረና አዳዲስ የሥራ ዕድሎች እየተፈጠሩ ነው። እያንዳንዱ ምሰሶ ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር፣ ጠንካራና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው።
#PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #ጋዜጣ_ፕሳስ #ኢትዮጵያታምርት #EthiopiaDelivers
9