Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.1K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ
++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ። በታላቅ የለውጥ ጉዞ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሚኖርዎት ጉብኝትና ቆይታ ስኬታማ እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።

#ጋዜጣ_ፕላስ #PMOEthiopia #diplomacy #bilateral #Burundi #ETH
4👏4
የቡሩንዲው ፕሬዝደንት ክቡር ኤቫሪስቴ ንድያይሽሚዬ በኢትዮጵያ የሚያደርጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝታቸው አካል በሆነው በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ሙዚየም ጉብኝት አድርገዋል። በታላቁ ቤተ-መንግስት ጣሪያ ስር የተገናኙት ሁለቱ ወንድማማች ሀገራት፤ በአፍሪካውያን የተጻፈውን ታላቅ ታሪካዊ ቅርስ በጋራ ዘክረዋል! #PMOEthiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንድያይሺሚዬ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተለያዩ የመግባቢያ ስምምነቶች ልውውጥ ላይ ታድመዋል። በመከላከያ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በውሃና ኢነርጂ፣ በግብርና ፣ በንግድ ፣ በዲጂታል መታወቅያ እና በቱሪዝም ዘርፎች የተፈረሙት እነዚህ ሁሉን አቀፍ ስምምነቶች ለቀጣናዊ ዘላቂ ልማት ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት በይፋ የሚያረጋግጡ ናቸው። እነዚህ የመግባቢያ ስምምነቶች የሁለቱን ሀገራት ሰፊ አቅም በመደመር ወደ ብልጽግና ለምናደርገው የጋራ ጉዞ መሠረት የሚጥሉ ናቸው።

#PMOEthiopia
👍1👎1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቡሩንዲ ፕሬዝደንት ኢቫሪስት ንዲያሺሚዬን ከሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝታቸው በኋላ በቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ሸኝተዋቸዋል።
#PMOEthiopia
1
“የትግራይ ወጣት ከአሁን በኋላ በጦርነት ማለቅ የለበትም”

- ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም
++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የትግራይ ወጣት ከአሁን በኋላ በጦርነት ሕይወቱን ማጣት እንደሌለበትና ማንኛውም የሕዝቡ ጥያቄ በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለበት የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም (ወ/ሮ) አሳሰቡ።

የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም ከጋዜጣ ፕላስ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳብራሩት፤ “አንድም የትግራይ ወጣት ደም መፍሰስ የለበትም፤ አሁን ጦርነት አያስፈልገንም።”

ወጣቱ ከአሁን በኋላ ደም መክፈል እንደሌለበት የገለጹት ዋና አፈ ጉባኤዋ፤ የትግራይ ሕዝብ ጥያቄዎች በጦርነት ሳይሆን በውይይት መፈታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የትግራይ ወጣት “ከአሁን በኋላ ጦርነት በቃን፤ መኖር እንፈልጋለን፤ ጥያቄ ካለም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንወያይበታለን” የሚል ግልጽ መልዕክት እያስተላለፈ መሆኑን ጠቁመዋል።

አሁን የሚያስፈልገው ቁጭ ብሎ በጠረጴዛ ዙሪያ ችግሮችን መፍታት መሆኑንም አክለዋል። ወጣቱ የትግራይ ሕዝብ ጥያቄ በመመካከርና በመወያየት እንደሚፈታ ጽኑ አመለካከት እንዳለውም ተናግረዋል።

ወጣቱን እንፈልገዋለን ብለው በወጣቶች ዙሪያ የሚሠሩ አካላት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ኬሪያ፤ የትግራይ ሕዝብ ፍትሕ እንደሚያስፈልገውና ፍትሕም መረጋገጥ እንዳለበት አሳስበዋል።

ሕዝቡ ከፍተኛ የሰላም ጥማት እንዳለበት በመግለጽ፣ ሰላምን ማረጋገጥ አለብን የሚሉ ተቋማት በሰላም ግንባታ ዙሪያ በስፋት ሊሠሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

በማርቆስ በላይ
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #ትግራይ #ሰላም #ወጣቶች #ፍትሕ #ውይይት #ኢትዮጵያ #ኬሪያ_ኢብራሂም
10😁1