"በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በአዲስ ስፖርት ፓርክ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#የጀግኖቻችን_ታሪክ #OlympicLegacy #የኢትዮጵያ_ጀግኖች #ChampionsPark #አዲስ_ስፖርት_ፓርክ
#NextGenerationAthletes
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#የጀግኖቻችን_ታሪክ #OlympicLegacy #የኢትዮጵያ_ጀግኖች #ChampionsPark #አዲስ_ስፖርት_ፓርክ
#NextGenerationAthletes
❤9
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በአዲስ አበባ እምብርት የተጀመረው ታላቅ ርዕይ፣ ዛሬ መላው ሀገርን አቅፎ፣ በተግባር እየተገለጠ፣ አዲስ ትውልድን ለከፍታ እያነቃቃ ይገኛል!
የለውጥ እና የልማት ጉዟችን አሁንም እንደቀጠለ ነው። ቀጣዩ የታሪክ ምዕራፍ የት ይሆን?
#ገበታለሸገር #ገበታለሀገር #ገበታለትውልድ #PMOEthiopia
የለውጥ እና የልማት ጉዟችን አሁንም እንደቀጠለ ነው። ቀጣዩ የታሪክ ምዕራፍ የት ይሆን?
#ገበታለሸገር #ገበታለሀገር #ገበታለትውልድ #PMOEthiopia
❤4
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
Photo
ኢትዮጵያ በተመድ የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንትነቷን በብቃት ተወጥታለች
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ -ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንትነቷን በብቃት መወጣቷን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በ61ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፥ ኢትዮጵያ 47 አባል ሀገራት ያሉት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባል በመሆን ለሦስተኛ ጊዜ ተመርጣ በንቃት እየሠራች ትገኛለች።
በዚህ የአባልነት ዘመኗም፣ ከፌብሩዋሪ 23- ማርች 31/2026 በጄኔቫ ሲካሄድ በቆየው በ61ኛው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን የመጀመሪያውን የአመራር ኃላፊነት በብቃት ተወጥታለች።
በስብሰባው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን በሚመለከት በአባል ሀገራት የቀረቡ 38 ውሳኔዎች የተላለፉበት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ሰባቱ ሀገር ተኮር ውሳኔዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ከሀገር ተኮር (Country Specific) ውሳኔዎች መካከል ከዩክሬን እና ሩሲያ ግጭት፣ ቤላሩስ፣ የሶሪያና ጎላን አካባቢ ባሉ ጉዳዮች፣ በፍልስጤም እና ከደቡብ ሱዳን ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ይገኙበታል ብለዋል።
በእነዚህ ሀገር ተኮር ጉዳዮች ላይ አባል ሀገራቱ ከራሳቸው ብሔራዊ ጥቅም በመነሳት፥ የመደገፍና የመቃወም ውሳኔ ማሳለፋቸውን ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያም እንደ አባል ሀገር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አቋሟን ማንጸባረቋን ጠቅሰው፥ ሀገራችን በመርህ ደረጃ ሀገር ተኮር ውሳኔን እንደማትደግፍ ገልጸዋል።
እንደዚህ ያሉ ውሳኔዎች ከዚህ ቀደም እንደነበሩና ኢትዮጵያ እንደምትቃወምም አንስተዋል።
ለአብነትም ኢትዮጵያ ችግር ላይ በነበረች ጊዜ ሀገራችን ባልተስማማችበት ጉዳይ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያዎች ኮሚሽን ተቋቁሞ እንደነበር አስታውሰው፥ ኢትዮጵያና ሌሎች ሀገራት በጋራ እንዲቀለበስ ማድረጋቸውን አስረድተዋል።
እንደዚህ ያሉ ሀገር ተኮር ጉዳዮች የሚመለከታቸው ሀገራት ሳይስማሙባቸው የሚቋቋሙ፣ የዓለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት ሥልጣንና ሚና የሚያጣቅሱ፣ እንዲሁም የምርመራና የዓለም አቀፍ ዳኝነት ይዘት ያላቸው ናቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደዚህ ያሉ የሀገርን ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥሉ ሀገር ተኮር ውሳኔዎችን በመርህ ደረጃ እንደማትደግፍ በማንሳት፥ በጉባኤው ያሳለፈችው ውሳኔም ይህንኑ እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ፍልስጤም እና የእስራኤልን በተመለከተ በተመድ መድረክ ስታራምድ የቆየችውን አቋም አሁንም ማስቀጠሏን ገልጸዋል።
የእስራኤልና ፍልስጤም የሁለት ሀገርነት መርህን እንደምትደግፍና ከሁለቱም ጋር መልካም ግንኙነት እንዳላት አንስተዋል።
ኢትዮጵያ የፍልስጤምን ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እንደምትደግፍ ጠቅሰው፥ ይህንንም በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጉባኤ የተላለፈውን የፍልስጤም የራስ ገዝነት ውሳኔ (HRC/61/L.37) ደግፋ ድምፅ መስጠቷን ተናግረዋል።
የሁለት ሀገርነት መፍትሔውም በዘላቂነት በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤዎችና በጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎች መሰረት እንዲተገበር ጥሪ ማቅረቧንም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በጉባኤው በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ከየአር ትራንስፖርት፣ ከመርከቦች እንቅስቃሴ፣ በቀጥታ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያሳድረውን ጫናና ስጋት ለጉባኤው መግልጿን ጠቅሰዋል።
አፋጣኝ ተኩስ አቁም እንዲደረግና መፍትሔ እንዲፈለግ ጥሪ ማቅርቧንም ተናግረዋል።
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ -ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንትነቷን በብቃት መወጣቷን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በ61ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ፥ ኢትዮጵያ 47 አባል ሀገራት ያሉት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባል በመሆን ለሦስተኛ ጊዜ ተመርጣ በንቃት እየሠራች ትገኛለች።
በዚህ የአባልነት ዘመኗም፣ ከፌብሩዋሪ 23- ማርች 31/2026 በጄኔቫ ሲካሄድ በቆየው በ61ኛው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን የመጀመሪያውን የአመራር ኃላፊነት በብቃት ተወጥታለች።
በስብሰባው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን በሚመለከት በአባል ሀገራት የቀረቡ 38 ውሳኔዎች የተላለፉበት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ሰባቱ ሀገር ተኮር ውሳኔዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ከሀገር ተኮር (Country Specific) ውሳኔዎች መካከል ከዩክሬን እና ሩሲያ ግጭት፣ ቤላሩስ፣ የሶሪያና ጎላን አካባቢ ባሉ ጉዳዮች፣ በፍልስጤም እና ከደቡብ ሱዳን ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ይገኙበታል ብለዋል።
በእነዚህ ሀገር ተኮር ጉዳዮች ላይ አባል ሀገራቱ ከራሳቸው ብሔራዊ ጥቅም በመነሳት፥ የመደገፍና የመቃወም ውሳኔ ማሳለፋቸውን ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያም እንደ አባል ሀገር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አቋሟን ማንጸባረቋን ጠቅሰው፥ ሀገራችን በመርህ ደረጃ ሀገር ተኮር ውሳኔን እንደማትደግፍ ገልጸዋል።
እንደዚህ ያሉ ውሳኔዎች ከዚህ ቀደም እንደነበሩና ኢትዮጵያ እንደምትቃወምም አንስተዋል።
ለአብነትም ኢትዮጵያ ችግር ላይ በነበረች ጊዜ ሀገራችን ባልተስማማችበት ጉዳይ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያዎች ኮሚሽን ተቋቁሞ እንደነበር አስታውሰው፥ ኢትዮጵያና ሌሎች ሀገራት በጋራ እንዲቀለበስ ማድረጋቸውን አስረድተዋል።
እንደዚህ ያሉ ሀገር ተኮር ጉዳዮች የሚመለከታቸው ሀገራት ሳይስማሙባቸው የሚቋቋሙ፣ የዓለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት ሥልጣንና ሚና የሚያጣቅሱ፣ እንዲሁም የምርመራና የዓለም አቀፍ ዳኝነት ይዘት ያላቸው ናቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደዚህ ያሉ የሀገርን ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥሉ ሀገር ተኮር ውሳኔዎችን በመርህ ደረጃ እንደማትደግፍ በማንሳት፥ በጉባኤው ያሳለፈችው ውሳኔም ይህንኑ እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ፍልስጤም እና የእስራኤልን በተመለከተ በተመድ መድረክ ስታራምድ የቆየችውን አቋም አሁንም ማስቀጠሏን ገልጸዋል።
የእስራኤልና ፍልስጤም የሁለት ሀገርነት መርህን እንደምትደግፍና ከሁለቱም ጋር መልካም ግንኙነት እንዳላት አንስተዋል።
ኢትዮጵያ የፍልስጤምን ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እንደምትደግፍ ጠቅሰው፥ ይህንንም በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጉባኤ የተላለፈውን የፍልስጤም የራስ ገዝነት ውሳኔ (HRC/61/L.37) ደግፋ ድምፅ መስጠቷን ተናግረዋል።
የሁለት ሀገርነት መፍትሔውም በዘላቂነት በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤዎችና በጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎች መሰረት እንዲተገበር ጥሪ ማቅረቧንም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በጉባኤው በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ከየአር ትራንስፖርት፣ ከመርከቦች እንቅስቃሴ፣ በቀጥታ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያሳድረውን ጫናና ስጋት ለጉባኤው መግልጿን ጠቅሰዋል።
አፋጣኝ ተኩስ አቁም እንዲደረግና መፍትሔ እንዲፈለግ ጥሪ ማቅርቧንም ተናግረዋል።
❤3👎2👍1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ አመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማና ውይይት ተደርጓል። #PMOEthiopia
🤔2
አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር፤ በአፍሪካ ህብረትና በተባባሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን መሠራታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011ዓ.ም ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይም ልዩ አማካሪም ነበሩ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአምባሳደር ቆንጂት ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች መጽናናትን ይመኛል።
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር፤ በአፍሪካ ህብረትና በተባባሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን መሠራታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011ዓ.ም ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይም ልዩ አማካሪም ነበሩ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአምባሳደር ቆንጂት ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች መጽናናትን ይመኛል።
❤2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅርበዋል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ
++++++++++++++++
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ።
አምባሳደር ቆንጂት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ኢትዮጵያን በዲፕሎማትነት በማገልገል፣ ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛዋ ሴት የኢትዮጵያ አምባሳደር ናቸው። ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን። ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለመላ ኢትዮጵያውያን መጽናናት እመኛለሁ ብለዋል ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ።
++++++++++++++++
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ።
አምባሳደር ቆንጂት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ኢትዮጵያን በዲፕሎማትነት በማገልገል፣ ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛዋ ሴት የኢትዮጵያ አምባሳደር ናቸው። ለሕግ፣ ለአሠራር፣ ለፕሮቶኮል እና ለኢትዮጵያ ጥቅሞች በነበራቸው የጸና አቋም እናስታውሳቸዋለን። ከእርሳቸው በኋላ አያሌ ሴት ዲፕሎማቶች በመስኩ እንዲሠማሩ መንገዱን አስፍተዋል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለመላ ኢትዮጵያውያን መጽናናት እመኛለሁ ብለዋል ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ።
❤4👏1
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 62(9)እና በዐዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀፅ 2(ለ) መሠረት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደርን በርዕሰ መስተዳደርነት እንዲመሩ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር አስመልክቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 479/2013 አንቀጽ 4(2) እና የዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ባቀረቡት መሠረት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሌፍተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደን ለአንድ ዓመት ሹመታቸውን አራዝመዋል፡፡ #PMOEthiopia
❤7🤔2
ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ
++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ። በታላቅ የለውጥ ጉዞ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሚኖርዎት ጉብኝትና ቆይታ ስኬታማ እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።
#ጋዜጣ_ፕላስ #PMOEthiopia #diplomacy #bilateral #Burundi #ETH
++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስት ንዴሺሚዬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ። በታላቅ የለውጥ ጉዞ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሚኖርዎት ጉብኝትና ቆይታ ስኬታማ እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።
#ጋዜጣ_ፕላስ #PMOEthiopia #diplomacy #bilateral #Burundi #ETH
❤4👏4