ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል።
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት ሕገ መንግሥታዊነትን ለማረጋገጥ፣ የመብቶችን ጥበቃ ለማስፋትና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሚያስችሉ ሰፋፊ የሕግና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተደረጉ ሲሆን በዚህ ሒደት ከተለዩት ቁልፍ ሕጎች መካከል አንዱ የወንጀል ሥነ ሥርዓት የሕግ መድብሉ ነው።
የ1954 የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው።
#EthiopiaDelivers #PMOEthiopia
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት ሕገ መንግሥታዊነትን ለማረጋገጥ፣ የመብቶችን ጥበቃ ለማስፋትና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሚያስችሉ ሰፋፊ የሕግና ተቋማዊ ማሻሻያዎች የተደረጉ ሲሆን በዚህ ሒደት ከተለዩት ቁልፍ ሕጎች መካከል አንዱ የወንጀል ሥነ ሥርዓት የሕግ መድብሉ ነው።
የ1954 የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት እና ከወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ብዙ ምክክር ተደርጎበት የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን የሚያስተዋውቅ፤ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው።
#EthiopiaDelivers #PMOEthiopia
የአማራ ክልል ምክር ቤት 1ሺህ 224 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ ወሰነ
++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛው ዙር 5ኛ ዓመት 9ኛው መደበኛ ጉባኤ ለ1 ሺህ 224 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታውቋል።
የክልሉ ፍትህ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) የይቅርታ አሰጣጡን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት፤ የይቅርታ ቦርዱ ካቀረባቸው 1 ሺህ 463 ታራሚዎች መካከል መስፈርቱን ሙሉ በሙሉ አሟልተው የተገኙ 1 ሺህ 224 ታራሚዎች ከእስር እንዲፈቱ ምክር ቤቱ ወስኗል።
ታራሚዎቹ ይቅርታ የተደረገላቸው በእስር ቆይታቸው የታረሙ በመሆናቸው በመረጋገጡ፣ ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንደሚችሉ በመታመኑ እና አንድ ሶስተኛ ወይም ሁለት ሶስተኛ የሚሆነውን የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተልጧል።
በሴቶችና በሕፃናት ላይ የመድፈር ወንጀል የፈጸሙ፣ የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው፤ እርቅ ያልፈጸሙና ካሳ ያልከፈሉ ታራሚዎች በይቅርታው አለመካተታቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፊርማ አማካኝነት አስፈላጊው ደብዳቤ ተጽፎላቸው በቅርቡ ከእስር እንደሚለቀቁ ተገልጿል።
በሙሉጌታ ምህረት
++++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት# ጋዜጣ-ፕላስ# አማራ ክልል# ፍትህ# ታራሚዎች#ይቅርታ#
++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው 6ኛው ዙር 5ኛ ዓመት 9ኛው መደበኛ ጉባኤ ለ1 ሺህ 224 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታውቋል።
የክልሉ ፍትህ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) የይቅርታ አሰጣጡን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት፤ የይቅርታ ቦርዱ ካቀረባቸው 1 ሺህ 463 ታራሚዎች መካከል መስፈርቱን ሙሉ በሙሉ አሟልተው የተገኙ 1 ሺህ 224 ታራሚዎች ከእስር እንዲፈቱ ምክር ቤቱ ወስኗል።
ታራሚዎቹ ይቅርታ የተደረገላቸው በእስር ቆይታቸው የታረሙ በመሆናቸው በመረጋገጡ፣ ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንደሚችሉ በመታመኑ እና አንድ ሶስተኛ ወይም ሁለት ሶስተኛ የሚሆነውን የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተልጧል።
በሴቶችና በሕፃናት ላይ የመድፈር ወንጀል የፈጸሙ፣ የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው፤ እርቅ ያልፈጸሙና ካሳ ያልከፈሉ ታራሚዎች በይቅርታው አለመካተታቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።
ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፊርማ አማካኝነት አስፈላጊው ደብዳቤ ተጽፎላቸው በቅርቡ ከእስር እንደሚለቀቁ ተገልጿል።
በሙሉጌታ ምህረት
++++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት# ጋዜጣ-ፕላስ# አማራ ክልል# ፍትህ# ታራሚዎች#ይቅርታ#
❤2👍1
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
❤4👍1
በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደረግ ይገባል
+++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ ዝናብ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው፤ የሚያዝያ ወር ከሌሎቹ የበልግ ወራት አንጻር የዝናብ መጠኑም ሆነ ስርጭቱ የሚሰፋበት ወቅት ሲሆን፤ በርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
ከሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል።
በሌላ በኩል የተሻለ እርጥበት መኖሩ የበልግ አብቃይ አካባቢዎች ለሚያከናውኑት የግብርና እንቅስቃሴ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የተመላከተ ሲሆን፤ አርሶ አደሮች፤ አርብቶ አደሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ለግብርና ስራ ሊጠቀሙበት ይገባል፡፡
በሄለን ወንድምነው
+++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት#ጋዜጣ_ፕላስ #ሜቲዎሮሎጂ #ኢትዮጵያ #የአየር_ትንበያ #ጥንቃቄ
+++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ ዝናብ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው፤ የሚያዝያ ወር ከሌሎቹ የበልግ ወራት አንጻር የዝናብ መጠኑም ሆነ ስርጭቱ የሚሰፋበት ወቅት ሲሆን፤ በርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
ከሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል።
በሌላ በኩል የተሻለ እርጥበት መኖሩ የበልግ አብቃይ አካባቢዎች ለሚያከናውኑት የግብርና እንቅስቃሴ አመቺ ሁኔታን እንደሚፈጥር የተመላከተ ሲሆን፤ አርሶ አደሮች፤ አርብቶ አደሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ለግብርና ስራ ሊጠቀሙበት ይገባል፡፡
በሄለን ወንድምነው
+++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት#ጋዜጣ_ፕላስ #ሜቲዎሮሎጂ #ኢትዮጵያ #የአየር_ትንበያ #ጥንቃቄ
በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሳይንስ ሥነ-ምሕዳር ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ዘመናዊ የምርምር ማዕከል ዛሬ መርቀን ከፍተናል። በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባው ይህ ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው።
የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካትቷል። በተጨማሪም ተቋሙ ለድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድ እንደ ማገር ሆኖ ያገለግላል።
ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
የምርምር ማዕከሉ 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) ቦታዎችን፣ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካትቷል። በተጨማሪም ተቋሙ ለድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት አቅምን በመገንባት ረገድ እንደ ማገር ሆኖ ያገለግላል።
ምርምርን ወደ ፖሊሲ፣ ፈጠራን ደግሞ ወደ ተግባራዊ መፍትሔ በመቀየር፤ ይህ ማዕከል በመድኃኒት ምርት ራሳችንን ለመቻል፣ ዘላቂ የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥና ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ትልቅ እርምጃ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍2
"ታላቋን ኢትዮጵያ ማለም ብቻ ሳይሆን በተግባር እንገነባታለን" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
+++++++++++++
የከተማችንን እድሳት ለማፋጠንና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል።
በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋል።
የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል።
የእውነተኛ ልማት ማዕከል ማህበረሰቡ ላይ መሆን አለበት! ይህ ፕሮጀክት ከላቀ የስፖርት አገልግሎት ባለፈ፣ በልማቱ ምክንያት ለተነሱ የህብረተሰብ ክፍሎች የኢኮኖሚ አቅም የሚሆኑ 105 አዳዲስ የንግድ ሱቆችን እንዲሁም 3 ሺህ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሰፊ ፕላዛ ይዟል።
በአንዴ 300 መኪናዎችን የሚይዝ ባለ ሁለት ወለል የምድር ቤት መኪና ማቆሚያ ያለውና ከወንዝ ዳርቻ ልማት ጋር የተሳሰረው ይህ ፓርክ፤ ንፁህና ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ የጀመርነውን ቁርጠኝነት ጉልህ ማሳያ ነው።
ታላቋን ኢትዮጵያ ማለም ብቻ ሳይሆን በተግባር እንገነባታለን!
#አዲስ_ስፖርት_ፓርክ #ታላቋ_ኢትዮጵያ #የጀግኖች_ታሪክ #የከተማ_እድሳት #በተግባር
+++++++++++++
የከተማችንን እድሳት ለማፋጠንና የዜጎቻችንን ክብር ለመመለስ የገባነውን ቃል አንዱ ማረጋገጫ የሆነውን የአዲስ ስፖርት ፓርክን በይፋ መርቀን ከፍተናል።
በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ፕሮጀክት፤ በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ 15 አትሌቶችን የሚዘክሩ የክብር ሐውልቶችን በፓርኩ መሃል በማቆም፣ የጀግኖቻችን ታሪክ ለተተኪ ትውልድ ስፖርተኞች ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋል።
የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስና የሜዳ ቴኒስ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም የ800 ሜትር የሩጫ ትራክን ጨምሮ፤ እያንዳንዱ የዚህ ማዕከል ክፍል የዓለም አቀፍ መስፈርቶችን እንዲያሟላ ተደርጎ ተገንብቷል።
የእውነተኛ ልማት ማዕከል ማህበረሰቡ ላይ መሆን አለበት! ይህ ፕሮጀክት ከላቀ የስፖርት አገልግሎት ባለፈ፣ በልማቱ ምክንያት ለተነሱ የህብረተሰብ ክፍሎች የኢኮኖሚ አቅም የሚሆኑ 105 አዳዲስ የንግድ ሱቆችን እንዲሁም 3 ሺህ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሰፊ ፕላዛ ይዟል።
በአንዴ 300 መኪናዎችን የሚይዝ ባለ ሁለት ወለል የምድር ቤት መኪና ማቆሚያ ያለውና ከወንዝ ዳርቻ ልማት ጋር የተሳሰረው ይህ ፓርክ፤ ንፁህና ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ የጀመርነውን ቁርጠኝነት ጉልህ ማሳያ ነው።
ታላቋን ኢትዮጵያ ማለም ብቻ ሳይሆን በተግባር እንገነባታለን!
#አዲስ_ስፖርት_ፓርክ #ታላቋ_ኢትዮጵያ #የጀግኖች_ታሪክ #የከተማ_እድሳት #በተግባር
❤2😁1