በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚተላለፉ ይዘቶች 25 በመቶ ያህሉ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃዎች ናቸው
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በናሙና ከመረመራቸው የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶች መካከል 25 በመቶ ያህሉ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃዎች መሆናቸውን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ እንደገለጹት፤ ከየካቲት 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2018 ዓ.ም ድረስ ከፍተኛ ተከታይ ባላቸው እና ከፍተኛ ይዘቶች በሚሰራጭባቸው የፌስቡክ፣ የቲክቶክ፣ የቴሌግራም፣ የኤክስ እና የዩቲዩብ ገጾች ላይ ክትትል ተደርጓል።
በናሙናነት ከተመረመሩ 32 ሺህ ይዘቶች ውስጥ ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ይዘት ያላቸው እንደሆኑ ማረጋገጡን ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
ከማህበራዊ ሚዲያ ፕላትፎርሞች የተሰበሰቡ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ይዘቶችን በሳይንሳዊ መንገድ የመተንተን እና የመተርጎም ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ባለሥልጣኑ የክትትል ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሯ አመልክተዋል።
በሄለን ወንድምነው
++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት@ጋዜጣ-ፕላስ#መገናኛ_ብዙኃን_ባለሥልጣን#የጥላቻ_ንግግር#ሐሰተኛ_መረጃ #ኢትዮጵያ#
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በናሙና ከመረመራቸው የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶች መካከል 25 በመቶ ያህሉ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃዎች መሆናቸውን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ እንደገለጹት፤ ከየካቲት 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2018 ዓ.ም ድረስ ከፍተኛ ተከታይ ባላቸው እና ከፍተኛ ይዘቶች በሚሰራጭባቸው የፌስቡክ፣ የቲክቶክ፣ የቴሌግራም፣ የኤክስ እና የዩቲዩብ ገጾች ላይ ክትትል ተደርጓል።
በናሙናነት ከተመረመሩ 32 ሺህ ይዘቶች ውስጥ ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ይዘት ያላቸው እንደሆኑ ማረጋገጡን ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
ከማህበራዊ ሚዲያ ፕላትፎርሞች የተሰበሰቡ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ይዘቶችን በሳይንሳዊ መንገድ የመተንተን እና የመተርጎም ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ባለሥልጣኑ የክትትል ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሯ አመልክተዋል።
በሄለን ወንድምነው
++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት@ጋዜጣ-ፕላስ#መገናኛ_ብዙኃን_ባለሥልጣን#የጥላቻ_ንግግር#ሐሰተኛ_መረጃ #ኢትዮጵያ#
❤3
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
❤5
መንግሥት በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቋቋም የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ይፋ አደረገ
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ መንግሥት በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቋቋም የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመካካለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን አቅጣጫዎች በተመለከተ ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን የሚከታተል፣ እርምጃ የሚወስድና የነዳጅ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ዘርፍች የሚለይ ልዩ ክፍል መቋቋሙንም ይፋ አድርገዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ተናግረዋል።
በጦርነቱ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጦርነቱ በፊት የአንድ በርሜል ነጭ ናፍጣ ዋጋ 80 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 230 ዶላር መድረሱን ቤንዚንም ከ70 ወደ 150 ዶላር ማሻቀቡን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጋር የነበራት የረጅም ጊዜ የነዳጅ ግብይት ውል በጦርነቱ ምክንያት መስተጓጎሉንና አቅራቢ ሀገራቱ ምርቱን ማቅረብ እንደማይችሉ ማሳወቃቸውን አስታውሰዋል።
በዚህም ምክንያት በግዥ ሂደት ላይ የነበረ ከ180 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ነዳጅ አለመቅረቡን ጠቅሰዋል።
በጦርነቱና አለመረጋጋቱ ምክንያትም በነጭ ናፍጣ ላይ የነበረው የቀን አቅርቦት ከ9 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4 ነጥብብ 5 ሚሊዮን ሊትር ዝቅ ማለቱን ጠቁመዋል።
የተለያዩ ሀገራት ያጋጠማቸውን የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ተከትሎ የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቀባዎችን እያደረጉ መሆኑን ገልጸው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚከተለው መርህ ግን ከህዝቡ ጋር በመተባበር ችግሩን በጋራ ለመሻገር መሆኑን ጠቅሰዋል።
መንግሥት የተፈጠረውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዳይገቱ ነዳጅን ከተጓዳኝ ገበያ ስለሚገዛና የዓለም የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት በሦስት እጥፍ ዋጋ እየገዛ ለማቅረብ መገደዱን ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
ምንም እንኳን የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቢጨምርም፣ መንግሥት የዜጎችን ኑሮ ለመታደግ በአሁኑ ወቅት በነጭ ናፍጣ ላይ በአንድ ሊትር 95 ብር፣ በቤንዚን ላይ ደግሞ 42 ብር ድጎማ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
እስካሁን 262 ቢሊዮን ብር ገደማ ድጎማ ማድረጉን በማንሳት የተደረገ ሲሆን፣ በየወሩም ከ15 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለድጎማ እየተመደበ መሆኑ ጠቅሰዋል።
ያጋጠመው የነዳጅ አቅርቦት እጥረት በሀገርና በዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና እንዳያሳድርና በፍትሐዊነት ለመምራት መንግሥት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የቅድሚያ አሰጣጥ ውሳኔ ማሳለፉን ሚኒስትሩ ይፋ አድርገዋል።
በዚህም መሠረት
1. ነዳጅ የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች በማደያ የቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው
2. ከፍተኛ አምራችና የኤክስፖርት ድርጅቶች በቀጥታ ፣
3. ልዩ ትኩረት የሚሹ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች በቀጥታ፣
4. የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች
5. ግብርናን የሚያዘምኑ ትራክተሮች፣
6. የከተማና ሀገር አቀፍ የብዙሃን ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች
7. እንዲሁም በናፍጣ የሚሰሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ነዳጅን በቅድሚያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የቅድሚያ የነዳጅ አጠቃቀም አሠራር የሚተገበር መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ውጭ የሚደረግ የነዳጅ ስርጭት ተገቢ ባለመሆኑ እርምጃ ይወሰዳል ያሉት ሚኒስትር፥ ይህንን ውሳኔ በአግባቡ ለማስፈጸም በቅንጅት እንደሚሠራም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል መንግሥት የፌደራልና የክልል ተቋማትን ያካተተና ስርጭቱን 24/7 የሚከታተል የሁኔታዎች ልዩ የመከታተያ ክፍል ማቋቋሙን ይፋ አድርገዋል።
ልዩ የመከታተያ ክፍሉ በማዕከል የሚመራ ሲሆን የነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭትና አጠቃቀምን የሚከታተል፣ ውሳኔዎችን የሚየቀርብና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የሚለይ መሆኑን ተናግረዋል።
በነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ዙሪያ ሕገ-ወጥ ድርጊት የፈጸሙ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ 658 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ከ720 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተይዞ ለመንግሥት ገቢ ሆኗል ብለዋል።
ከህብረተሰቡ የሚከጠበቁ ተግባራትን ይፋ ያደረጉ ሲሆን በዚህም መሠረት፦
1) ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም፣
2) የታዳሽ ኃይል አማራጮችን የመጠቀም ስልትን መከተል፣
3) የእግር ጉዞ ባህልን ማጎልበት
4) አላስፈላጊ የጉዞ ፕሮግራሞችን መሰረዝና ማቆም
5) የሕዝብ ትራንስፖርትን መጠቀም
6) በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ረገድ ከመንግሥት ጋር ተባብሮ እንዲሠራ ጥሪ አቅርበዋል።
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ መንግሥት በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቋቋም የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመካካለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን አቅጣጫዎች በተመለከተ ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን የሚከታተል፣ እርምጃ የሚወስድና የነዳጅ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ዘርፍች የሚለይ ልዩ ክፍል መቋቋሙንም ይፋ አድርገዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ተናግረዋል።
በጦርነቱ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጦርነቱ በፊት የአንድ በርሜል ነጭ ናፍጣ ዋጋ 80 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 230 ዶላር መድረሱን ቤንዚንም ከ70 ወደ 150 ዶላር ማሻቀቡን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጋር የነበራት የረጅም ጊዜ የነዳጅ ግብይት ውል በጦርነቱ ምክንያት መስተጓጎሉንና አቅራቢ ሀገራቱ ምርቱን ማቅረብ እንደማይችሉ ማሳወቃቸውን አስታውሰዋል።
በዚህም ምክንያት በግዥ ሂደት ላይ የነበረ ከ180 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ነዳጅ አለመቅረቡን ጠቅሰዋል።
በጦርነቱና አለመረጋጋቱ ምክንያትም በነጭ ናፍጣ ላይ የነበረው የቀን አቅርቦት ከ9 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4 ነጥብብ 5 ሚሊዮን ሊትር ዝቅ ማለቱን ጠቁመዋል።
የተለያዩ ሀገራት ያጋጠማቸውን የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ተከትሎ የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቀባዎችን እያደረጉ መሆኑን ገልጸው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚከተለው መርህ ግን ከህዝቡ ጋር በመተባበር ችግሩን በጋራ ለመሻገር መሆኑን ጠቅሰዋል።
መንግሥት የተፈጠረውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዳይገቱ ነዳጅን ከተጓዳኝ ገበያ ስለሚገዛና የዓለም የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት በሦስት እጥፍ ዋጋ እየገዛ ለማቅረብ መገደዱን ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
ምንም እንኳን የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቢጨምርም፣ መንግሥት የዜጎችን ኑሮ ለመታደግ በአሁኑ ወቅት በነጭ ናፍጣ ላይ በአንድ ሊትር 95 ብር፣ በቤንዚን ላይ ደግሞ 42 ብር ድጎማ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
እስካሁን 262 ቢሊዮን ብር ገደማ ድጎማ ማድረጉን በማንሳት የተደረገ ሲሆን፣ በየወሩም ከ15 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለድጎማ እየተመደበ መሆኑ ጠቅሰዋል።
ያጋጠመው የነዳጅ አቅርቦት እጥረት በሀገርና በዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና እንዳያሳድርና በፍትሐዊነት ለመምራት መንግሥት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የቅድሚያ አሰጣጥ ውሳኔ ማሳለፉን ሚኒስትሩ ይፋ አድርገዋል።
በዚህም መሠረት
1. ነዳጅ የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች በማደያ የቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው
2. ከፍተኛ አምራችና የኤክስፖርት ድርጅቶች በቀጥታ ፣
3. ልዩ ትኩረት የሚሹ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች በቀጥታ፣
4. የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች
5. ግብርናን የሚያዘምኑ ትራክተሮች፣
6. የከተማና ሀገር አቀፍ የብዙሃን ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች
7. እንዲሁም በናፍጣ የሚሰሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ነዳጅን በቅድሚያ እንዲያገኙ የሚያደርግ የቅድሚያ የነዳጅ አጠቃቀም አሠራር የሚተገበር መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ውጭ የሚደረግ የነዳጅ ስርጭት ተገቢ ባለመሆኑ እርምጃ ይወሰዳል ያሉት ሚኒስትር፥ ይህንን ውሳኔ በአግባቡ ለማስፈጸም በቅንጅት እንደሚሠራም ገልጸዋል።
በሌላ በኩል መንግሥት የፌደራልና የክልል ተቋማትን ያካተተና ስርጭቱን 24/7 የሚከታተል የሁኔታዎች ልዩ የመከታተያ ክፍል ማቋቋሙን ይፋ አድርገዋል።
ልዩ የመከታተያ ክፍሉ በማዕከል የሚመራ ሲሆን የነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭትና አጠቃቀምን የሚከታተል፣ ውሳኔዎችን የሚየቀርብና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የሚለይ መሆኑን ተናግረዋል።
በነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ዙሪያ ሕገ-ወጥ ድርጊት የፈጸሙ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ 658 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ከ720 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተይዞ ለመንግሥት ገቢ ሆኗል ብለዋል።
ከህብረተሰቡ የሚከጠበቁ ተግባራትን ይፋ ያደረጉ ሲሆን በዚህም መሠረት፦
1) ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም፣
2) የታዳሽ ኃይል አማራጮችን የመጠቀም ስልትን መከተል፣
3) የእግር ጉዞ ባህልን ማጎልበት
4) አላስፈላጊ የጉዞ ፕሮግራሞችን መሰረዝና ማቆም
5) የሕዝብ ትራንስፖርትን መጠቀም
6) በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ረገድ ከመንግሥት ጋር ተባብሮ እንዲሠራ ጥሪ አቅርበዋል።
❤3
የኢትዮጵያ መንግሥት በInvest in Ethiopia 2026 ፎረም፤ ከቻይና፣ ፖላንድ፣ ህንድ፣ ሲንጋፖር እና ኬንያ ከመጡ አጋሮች ጋር የ13.1 ቢሊዮን ዶላር ታሪካዊ የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራርሟል።
በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው። የውጭ ምንዛሬ ተመን ሊበራላይዜሽንና የባንክና ቴሌኮም ዘርፎችን ለንግድ ማህበረሰቡ ክፍት ማድረግ የመሳሰሉ ቆራጥ እርምጃዎች ግልጽና ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠራቸውን በተጨባጭ ያረጋግጣል። ይህም በዘመናዊ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አማካኝነት ለዓለም አቀፍ ገበያ ምቹ መዳረሻን ፈጥሯል።
ይህ ዕድገት በሁሉም ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በግልጽ እየታየ የሚገኝ ሲሆን፤ በታላቁ የህዳሴ ግድብ የተንተራሰው የሀገራችንን የታዳሽ ኃይል ሀብትን በመጠቀም በሶላር ምርትና በሃይድሮጅን ፕሮጀክቶች ላይ የተገኘው እመርታ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የማዕድን ዘርፍ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራበት ይገኛል።
የኢንዱስትሪ ዕድገታችን አዲስ በሚገነቡት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እየተፋጠነ ሲሆን፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፉም በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በልህቀት እየተመራ ይገኛል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስርና በባህላዊ ቅርሶቻችን የታጀበችው ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ሆናለች።
ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን ለላቀ አጋርነት እንጋብዛለን፤ ኢትዮጵያ ከነበረው እጅጉን በተሻለ ለንግድ ዝግጁ ናት!
#InvestInEthiopia #EthiopiaDelivers
#PMOEthiopia
በታዳሽ ኃይል፣ በማዕድንና በአረንጓዴ አሞኒያ ዘርፎች ላይ ያተኮሩት እነዚህ ስምምነቶች የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ጉልህ ማሳያ ናቸው። የውጭ ምንዛሬ ተመን ሊበራላይዜሽንና የባንክና ቴሌኮም ዘርፎችን ለንግድ ማህበረሰቡ ክፍት ማድረግ የመሳሰሉ ቆራጥ እርምጃዎች ግልጽና ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠራቸውን በተጨባጭ ያረጋግጣል። ይህም በዘመናዊ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አማካኝነት ለዓለም አቀፍ ገበያ ምቹ መዳረሻን ፈጥሯል።
ይህ ዕድገት በሁሉም ስትራቴጂካዊ ዘርፎች በግልጽ እየታየ የሚገኝ ሲሆን፤ በታላቁ የህዳሴ ግድብ የተንተራሰው የሀገራችንን የታዳሽ ኃይል ሀብትን በመጠቀም በሶላር ምርትና በሃይድሮጅን ፕሮጀክቶች ላይ የተገኘው እመርታ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የማዕድን ዘርፍ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራበት ይገኛል።
የኢንዱስትሪ ዕድገታችን አዲስ በሚገነቡት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እየተፋጠነ ሲሆን፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፉም በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በልህቀት እየተመራ ይገኛል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ ትስስርና በባህላዊ ቅርሶቻችን የታጀበችው ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ሆናለች።
ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን ለላቀ አጋርነት እንጋብዛለን፤ ኢትዮጵያ ከነበረው እጅጉን በተሻለ ለንግድ ዝግጁ ናት!
#InvestInEthiopia #EthiopiaDelivers
#PMOEthiopia
❤5
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ ከትግራይ ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳ ለማሰባሰብ በተዘጋጀው የመጀመሪያ ዙር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች
❤2👎2👏1
❤3🔥1😢1