በፍራፍሬና በደን ዛፎች የተከበበው የ ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ’ ጉብኝት። ለአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ያለው ቅርበ የጎብኝዎችን ምቾት ከመጨመሩም በላይ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሰፊ የስራ ዕድልን የፈጠረ ነው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ገበታ_ለትውልድ #PMOEthiopia #VisitEthiopia #EthiopiaDelivers
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ገበታ_ለትውልድ #PMOEthiopia #VisitEthiopia #EthiopiaDelivers
❤1👍1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከቃና ቲቪ ጋር በኢትዮጵያ ከተሞች የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ያደረጉትን ልዩ ቆይታ ይከታተሉ! በውይይቱ የከተማ ፕላን፣ የዘላቂ ልማት እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አዲስ አበባንና ሌሎች ከተሞችን እንዴት እየቀየሩ እንደሆነ፤ እንዲሁም የመሠረተ ልማትን፣ የንግድና የኢኮኖሚ ዕድሎችን በመላው ሀገሪቱ ለማሳደግ ያላቸው ፋይዳ በጥልቀት ይዳሰሳል!
መጋቢት 15 ከምሽቱ 2:30 ላይ!
Join Prime Minister Abiy Ahmed Ali for an exclusive discussion with Kana TV on the future of Ethiopian cities! Explore how urban planning, sustainable development, and corridor projects are transforming Addis Ababa and beyond; boosting infrastructure, trade, and economic opportunities across the country.
March 24th at 8:30pm!
#PMOEthiopia
መጋቢት 15 ከምሽቱ 2:30 ላይ!
Join Prime Minister Abiy Ahmed Ali for an exclusive discussion with Kana TV on the future of Ethiopian cities! Explore how urban planning, sustainable development, and corridor projects are transforming Addis Ababa and beyond; boosting infrastructure, trade, and economic opportunities across the country.
March 24th at 8:30pm!
#PMOEthiopia
❤7👍3
ኢትዮጵያ አምስት የባሕር በሮች እንዲኖሯት እንደሚሠራ ነእፓ አስታወቀ
+++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ሀገሪቱ ያሏትን ሀብቶች በሰጥቶ መቀበል መርህ በመጠቀም ኢትዮጵያ አምስት የባሕር በሮች እንዲኖሯት ስትራቴጂ ነድፎ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ።
ፓርቲው ይህን ያለው 7ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ባከበረበትና ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያዘጋጀውን የቃል ኪዳን ሰነድ (ማኒፌስቶ) ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው።
የፓርቲው የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ ሰነዱ በቀረበበት ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ሀብቶች ያሏት በመሆኑ፣ እነዚህን መሠረት በማድረግና በሰጥቶ መቀበል መርህ አምስት የባሕር በሮች እንዲኖሯት ለማድረግ ፓርቲው በትኩረት ይሠራል።
ኃላፊዋ አክለውም፤ ከባሕር በር በተጨማሪ ሀገሪቱ ያሏትን የውኃ ሀብቶች በአግባቡ መጠቀም እንድትችል ፓርቲው ስትራቴጂ መንደፉን አስረድተዋል።
የፓርቲው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረው ግንኙነት ሰላማዊ፣ ሚዛናዊና ባለብዙ ወገን እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑንም አመላክተዋል።
ነእፓ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም መሠረት ያደረጉ ተግባራት ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ ያነሱት ነቢሃ፤ በተጨማሪም በቀጣናው ያሉ ጂኦ-ፖለቲካዊ ችግሮችን በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት እንደሚሠራ አብራርተዋል።
ይፋ የተደረገው የፓርቲው የቃል ኪዳን ሰነድ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፤ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ ጉዳዮችንና የውጭ ግንኙነትን በዝርዝር የያዘ መሆኑ ተገልጿል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ነእፓ #ምርጫ #የባሕር_በር #ፖለቲካ #ማኒፌስቶ
+++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ሀገሪቱ ያሏትን ሀብቶች በሰጥቶ መቀበል መርህ በመጠቀም ኢትዮጵያ አምስት የባሕር በሮች እንዲኖሯት ስትራቴጂ ነድፎ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ።
ፓርቲው ይህን ያለው 7ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ባከበረበትና ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያዘጋጀውን የቃል ኪዳን ሰነድ (ማኒፌስቶ) ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው።
የፓርቲው የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ ሰነዱ በቀረበበት ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በርካታ ሀብቶች ያሏት በመሆኑ፣ እነዚህን መሠረት በማድረግና በሰጥቶ መቀበል መርህ አምስት የባሕር በሮች እንዲኖሯት ለማድረግ ፓርቲው በትኩረት ይሠራል።
ኃላፊዋ አክለውም፤ ከባሕር በር በተጨማሪ ሀገሪቱ ያሏትን የውኃ ሀብቶች በአግባቡ መጠቀም እንድትችል ፓርቲው ስትራቴጂ መንደፉን አስረድተዋል።
የፓርቲው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረው ግንኙነት ሰላማዊ፣ ሚዛናዊና ባለብዙ ወገን እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑንም አመላክተዋል።
ነእፓ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም መሠረት ያደረጉ ተግባራት ላይ ትኩረት እንደሚሰጥ ያነሱት ነቢሃ፤ በተጨማሪም በቀጣናው ያሉ ጂኦ-ፖለቲካዊ ችግሮችን በመፍታት ለጋራ ተጠቃሚነት እንደሚሠራ አብራርተዋል።
ይፋ የተደረገው የፓርቲው የቃል ኪዳን ሰነድ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፤ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ ጉዳዮችንና የውጭ ግንኙነትን በዝርዝር የያዘ መሆኑ ተገልጿል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ነእፓ #ምርጫ #የባሕር_በር #ፖለቲካ #ማኒፌስቶ
👍7🤣4❤2🤔2
“ከተሞች የሀገር መኳያ እና የአብሮነት ቤተሙከራዎች ናቸው”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ከተሞች የሀገር መኳያ፣ የስልጣኔ መስታወት እና የአብሮነት ቤተ-ሙከራዎች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተሞች በአዲስ ምናብ በሚል ርዕሰ ጉዳይ የኢትዮጵያ የከተማ ልማት የለውጥ ሥራዎችን በተመለከተ ከቃና ቴሌቭዥን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቆይታ እንዳሉት፣ ቀደም ሲል ከተሞችን እንደ ስጋትና ነዋሪዎቻቸውን እንደ ወላዋይ የመመልከት የተሳሳተ ዝንባሌ ተቀይሮ፣ አሁን ላይ ከተሞች የሀገር ዕድገት መለኪያና የስልጣኔ መስታወት ተደርገው በትኩረት እየተሠራባቸው ነው፡፡
ከተሞች የሀገር "እጅና አእምሮ" የሆኑና ግማሹ የሀገር ኢኮኖሚ የሚንቀሳቀስባቸው በመሆኑ፣ ከተማን ያገለለ የብልጽግና ጉዞ ሊሳካ እንደማይችል አስረድተዋል።
ከተሞች ለዘመናዊ ፈጠራ፣ ለውጥና ቀልጣፋ አሠራር መገኛ ከመሆናቸው ባለፈ፣ የአንድ ሀገር ስልጣኔና ዕድገት የሚለካው በከተሞቿ ውበትና ስልጣኔ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ከተማ ከተለያየ አካባቢ የመጡ ዜጎች በቋንቋ፣ በባህልና በሃይማኖት ሳይገደቡ በጋራ የሚኖሩባትና አብሮነት በተግባር የሚታይባት ስፍራ በመሆኗ፣ ሀገርን ለመገንባት እንደ ትልቅ መነሻ እንደምትወሰድም አክለዋል።
የከተማ ነዋሪ ለለውጥ ዝግጁ፣ ጥሮ ግሮ ለመለወጥ የሚተጋና ችግር ፈቺ በመሆኑ፣ መንግሥት የከተማውን ነዋሪ እንደ ዋና ማኅበራዊ መሠረት በመውሰድ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡
ከተሞች የሀገር መኳያ መገለጫ በመሆናቸው፣ እንደ አዲስ አበባ ያሉ ከተሞችን ውብ በማድረግ የሀገርን ክብርና ውበት ከፍ ለማድረግ የተሰራው ስራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ከተሞች የሀገር መኳያ፣ የስልጣኔ መስታወት እና የአብሮነት ቤተ-ሙከራዎች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተሞች በአዲስ ምናብ በሚል ርዕሰ ጉዳይ የኢትዮጵያ የከተማ ልማት የለውጥ ሥራዎችን በተመለከተ ከቃና ቴሌቭዥን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቆይታ እንዳሉት፣ ቀደም ሲል ከተሞችን እንደ ስጋትና ነዋሪዎቻቸውን እንደ ወላዋይ የመመልከት የተሳሳተ ዝንባሌ ተቀይሮ፣ አሁን ላይ ከተሞች የሀገር ዕድገት መለኪያና የስልጣኔ መስታወት ተደርገው በትኩረት እየተሠራባቸው ነው፡፡
ከተሞች የሀገር "እጅና አእምሮ" የሆኑና ግማሹ የሀገር ኢኮኖሚ የሚንቀሳቀስባቸው በመሆኑ፣ ከተማን ያገለለ የብልጽግና ጉዞ ሊሳካ እንደማይችል አስረድተዋል።
ከተሞች ለዘመናዊ ፈጠራ፣ ለውጥና ቀልጣፋ አሠራር መገኛ ከመሆናቸው ባለፈ፣ የአንድ ሀገር ስልጣኔና ዕድገት የሚለካው በከተሞቿ ውበትና ስልጣኔ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ከተማ ከተለያየ አካባቢ የመጡ ዜጎች በቋንቋ፣ በባህልና በሃይማኖት ሳይገደቡ በጋራ የሚኖሩባትና አብሮነት በተግባር የሚታይባት ስፍራ በመሆኗ፣ ሀገርን ለመገንባት እንደ ትልቅ መነሻ እንደምትወሰድም አክለዋል።
የከተማ ነዋሪ ለለውጥ ዝግጁ፣ ጥሮ ግሮ ለመለወጥ የሚተጋና ችግር ፈቺ በመሆኑ፣ መንግሥት የከተማውን ነዋሪ እንደ ዋና ማኅበራዊ መሠረት በመውሰድ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡
ከተሞች የሀገር መኳያ መገለጫ በመሆናቸው፣ እንደ አዲስ አበባ ያሉ ከተሞችን ውብ በማድረግ የሀገርን ክብርና ውበት ከፍ ለማድረግ የተሰራው ስራ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡
❤4
"የኮሪደር ልማት በርካታ በሥራ የተፈተኑ ኢንጂነሮችን ፈጥሯል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ባሻገር በሥራ የተፈተኑ በርካታ ወጣት ኢንጂነሮችን በተግባር ማፍራት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የኮሪደር ልማቱ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ግቦችን የያዘ መሆኑን ያነሱት ዐቢይ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ ወጣቶች ዩኒቨርሲቲ ገብተው ከሚያገኙት በላይ የተግባር እውቀት እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልጸዋል።
ወጣቶቹ የአዲስ አበባን ኮሪደር ከሠሩ በኋላ፣ በክልል ከተሞች ላይ መቶ በመቶ የራሳቸውን ዲዛይን በማውጣት ሠርተው ለማጠናቀቅ የሚያስችል አቅም እንደፈጠረላቸውም አብራርተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከገቢ ምንጭነት በተጨማሪ፣ የዕውቀትና የክህሎት ማዳበሪያ እንዲሁም የኢኖቬሽንና ፈጠራ ማጎልበቻ መሆኑን አክለው አስረድተዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ኮሪደር_ልማት #ኢንጂነሪንግ #አዲስ_አበባ #ወጣቶች #gazetteplus
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ባሻገር በሥራ የተፈተኑ በርካታ ወጣት ኢንጂነሮችን በተግባር ማፍራት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የኮሪደር ልማቱ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ግቦችን የያዘ መሆኑን ያነሱት ዐቢይ (ዶ/ር)፤ ፕሮጀክቱ ወጣቶች ዩኒቨርሲቲ ገብተው ከሚያገኙት በላይ የተግባር እውቀት እንዲያገኙ ማስቻሉን ገልጸዋል።
ወጣቶቹ የአዲስ አበባን ኮሪደር ከሠሩ በኋላ፣ በክልል ከተሞች ላይ መቶ በመቶ የራሳቸውን ዲዛይን በማውጣት ሠርተው ለማጠናቀቅ የሚያስችል አቅም እንደፈጠረላቸውም አብራርተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከገቢ ምንጭነት በተጨማሪ፣ የዕውቀትና የክህሎት ማዳበሪያ እንዲሁም የኢኖቬሽንና ፈጠራ ማጎልበቻ መሆኑን አክለው አስረድተዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ኮሪደር_ልማት #ኢንጂነሪንግ #አዲስ_አበባ #ወጣቶች #gazetteplus
❤5
ከውበት አንጻር ሲታይ፣ ከተማ የሥነ-ውበት ተምሳሌት ናት። ከተሞች የአንድን ሀገር ገጽታ ይገልጻሉ። ውብ የሆነችውን አዲስ አበባን የተመለከተ ሰው፣ ስለ ኢትዮጵያ ሲያስብ ሁልጊዜ ያ ምስል በአዕምሮው ውስጥ ታትሞ ይቀራል።#PMOEthiopia
❤4👍2🔥2