Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.2K subscribers
40.8K photos
333 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
“የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም” - የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ
+++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም ሲሉ በለንደን የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ ሀማድ ቤይግ ገለጹ፡፡

ሀማድ ቤይግ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ኢኮኖሚያዊ አስፈላጊነትና የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋ መልስ እንዲገኝ በሕግና በድርድር የተደገፈ መፍትሄዎችን እንደምትከተል የገለጹት ሀማድ፤ የባሕር በር በኃይል አማራጭ ልታገኝ ነው የሚለው ኢ-ምክንያታዊ ነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ባነሳች ማግስት ጸብ አጫሪ አድርገው ሊመለከቷት የፈለጉ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ እና በሕጋዊ ድርድር የባሕር በር ለማግኘት ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

ኢትዮጵያ ታሪክን፣ መልክዓ ምድርንና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይን መሰረት በማድረግ የባሕር በር ጥያቄ የማንሳት መብት አላት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጎችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በየትኛውም መመዘኛ ፍትሃዊነት ያለው ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ይፋዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ወደ ግጭት የመግባት ፍላጎትም ዝግጅትም እንደሌላት ማረጋገጧን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ለመሆን እያነሳች የምትገኘው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት እና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የሀገራትን ድጋፍ ለማግኘት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

በኢማኑኤል ጆርጌ
#ባህር_በር #ኢትዮጵያ #gazette_plus
9👍3
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።

🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።

ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።

📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
6👍1
"የጸና ወዳጅነት፣ በመተማመን ላይ የተመሠረተ ትብብር"

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናል።

‎ውይይታችን በኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብርና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር።

ለተደረገልኝ አቀባበልና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነው።
6
ቦርዱ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል በሆኑ የምርጫ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ወሰደ
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የምርጫ አስፈጻሚዎች ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ነፃ መሆን ያለባቸው ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል ሆነው በተገኙ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ዛሬ ማምሻውን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ ምርጫው ፍትሐዊና ገለልተኛ እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል። በዚህም መሠረት በተደረገ ማጣራት የፓርቲ አባል መሆናቸው የተረጋገጠባቸው አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ግለሰቦች መካከል ከፓርቲ አባልነት ባለፈ የፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ጭምር እንደሚገኙበት ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል።
ቦርዱ በማጣራት ያገኛቸውን እነዚህን ግለሰቦች ከአስፈጻሚነት ያሰናበተ ሲሆን፤ የማጣራት ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
በሌላ በኩል ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት የሚታዘቡላቸውን ወኪሎች እንዲልኩ ጥሪ ተደርጎ ባጅ የተዘጋጀ ቢሆንም፣ እስካሁን ወኪሎቻቸውን የላኩት ውስን ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
ቦርዱ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ማንኛውንም ችግሮች ለመፍታት ከቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ ያሉ አሠራሮችን እንደሚጠቀም ተናግረዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #ምርጫ_2018 #ምርጫ_ቦርድ #ገለልተኝነት #ኢትዮጵያ #ምርጫ_አስፈጻሚ
👍4
የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱምን አግኝቼ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
‎በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
10👍3
በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት ተቸግረዋል። በመሆኑም ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስክንመለስ ድረስ ነዳጅን በቁጠባና ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት መጠቀም ይኖርብናል።
በመሆኑም የነዳጅ አከፋፋዮች፣ማደያዎችና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ፣ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በሃላፊነት ስሜት እንድንጠቀም ለማሳሰብ እወዳለው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍3😁2
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
Photo
“ወድቆ መቅረት የለም”፤ ከሥልጣን እስከ መቄዶንያ
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ሕይወት እንዲህ ናት፤ ከፍታን በቀኟ ከያዘች በግራዋ ዝቅታን ይዛ እንካችሁ ማለት ልመዷ ነው።
ይህ አባባል የቀድሞው ባለስልጣን አሁን በመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑት የአቶ መላኩ አሰፋ የሕይወት ምስክርነት ሊሰጡበት የሚያስችል ነው።
አቶ መላኩ አሰፋ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ሲወጡ ትልቅ ራዕይ አንግበው ነበር የወጡት።
በኢትዮጵያ ማዕድን ሀብት ልማት ኮርፖሬሽን ውስጥ ለ10 ዓመታት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል። የኢትዮጵያን ሠራተኞች ኮንፌዴሬሽንን በምክትል ፕሬዝዳንትነት መርተዋል፡፡
በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችን ወክለው ከሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትርና ሚኒስትሮች ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ ተደራድረዋል፤ ተወያይተዋል።
የሰው ልጅ ሕይወት ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አይደለምና በኋላ ግን የአቶ መላኩ ሕይወት በዚህ ልትቀጥል አልቻለችም።
አቶ መላኩን ከባድ የአዕምሮ ሕመም ገጠማቸው። ያ ሁሉ ዝና፣ ያ ሁሉ ሥልጣንና እውቀት በሕመሙ ጥላ ሥር ተሸፈነ።
በአንድ ወቅት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችን መብትና ጥቅም ለማስከበር የሚሟገቱት ግለሰብ፣ ሕመም አሸንፏቸው ጎዳና ላይ ለመውደቅ በቁ።
ከውድቀትም በኋላ ትንሳኤ ከሕመምም በኋላ ፈውስ አለና አቶ መላኩ በሕመሙ ተሸንፈው አልቀሩም። ወደመቄሄዶንያ ገቡ፡፡
በመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር ባገኙት ፍቅር፣ እንክብካቤና ሕክምና ዳግም ለመወለድም ታደሉ። አእምሯቸው ተመልሶና ማንነታቸውን መልሰው በማግኘት ዛሬ ለመቄዶንያ ትልቅ ውለታ እየመለሱ ይገኛል።
በአሁኑ ጊዜ አቶ መላኩ በመቄዶንያ ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያና የስክሪፕት ጸሐፊ ናቸው።
በፋና እና በተለያዩ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በሚተላለፉ የመቄዶንያ የአየር ሰዓቶች ላይ ከ70 በላይ ስክሪፕቶችን አዘጋጅተዋል። በተጨማሪም ዶክመንተሪዎችንና ቃለ መጠይቆችን በብቃት ያከናውናሉ።
አቶ መላኩ መቄዶንያ ከበጎ አድራጎት ማኅበርነት አልፎ ወደ "ቻሪቲ ቪሌጅ" (Charity Village) እንዲያድግ የራሳቸውን ሙያዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ያስረዳሉ።
"መቄዶንያ የኢትዮጵያውያን የበጎነት ጥግ የታየበት፣ የሀገርን ሸክም የተሸከመ ተቋም ነው" ሲሉ መቄዶንያን ይገልጹታል።
"እኔ ድኜ ዛሬ እዚህ ሥራ ላይ ብገኝም፣ ነገ ለማንም ምን እንደሚመጣ አይታወቅም። ስለዚህ ሰውን አትናቁ፣ መቄዶንያን ደግሞ ደግፉ" ሲሉም መልእክታቸውን ያስተላልፋሉ።
በክቡር ዶክተር ቢኒያም በለጠ የተመሰረተው መቄዶንያ እንደአቶ መላኩ አይነት በርካታ የሕይወት ውጣ ውረድ ያሳለፉ ግለሰቦችን ያስጠለለ ተቋም ነው፡፡
ተቋሙ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በክልል ከተሞችም ቅርንጫፎችን ከፍቶ ሰውን ከጎዳና እያነሳ እየጦረ ይገኛል፡፡
መቄዶንያ ከመጋቢት 6 ጀምሮ የገበያ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ያዘጋጀ ሲሆን፤ ይህም ተቋሙ ለጀመረው ባለ 15 ወለል ሆስፒታል እና በክልል ከተማ እየተገነቡ ላሉ ቅርንጫፎች ማስጨረሻ የሚሆን ነው፡፡
መላው ኢትዮጵያውያንና ሌሎችም በገቢ ማሳባሰቢያው በመሳተፍ ተቋሙን እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል፡፡
በሄለን ወንድምነው
9👏2🥰1
"ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነትና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የስልክ ውይይት አድርገናል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍153😁3