Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.2K subscribers
40.8K photos
333 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ድሬ የቀደመ የከተሜነት ታሪኳን፣ ዘመናት ያስቆጠረ ድንቅ ባህሏን እንዲሁም በፍቅር የተሞላውን ህዝቧን የሚመጥን ውበት ተላብሳለች! የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን እጅግ ውብ እና ምቹ በማድረግ ታሪካዊነቷን ከዘመናዊ የከተማ መሰረተ ልማት ጋር በማቀናጀት ለመጎብኘት ተመራጭ አድርጓታል፡፡

#VisitEthiopia #PMOEthiopia
2🥰1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ረፋድ ላይ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬቶች ገብተዋል።

#PMOEthiopia
👍16🤣3
“የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም” - የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ
+++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም ሲሉ በለንደን የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ ሀማድ ቤይግ ገለጹ፡፡

ሀማድ ቤይግ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ኢኮኖሚያዊ አስፈላጊነትና የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋ መልስ እንዲገኝ በሕግና በድርድር የተደገፈ መፍትሄዎችን እንደምትከተል የገለጹት ሀማድ፤ የባሕር በር በኃይል አማራጭ ልታገኝ ነው የሚለው ኢ-ምክንያታዊ ነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ባነሳች ማግስት ጸብ አጫሪ አድርገው ሊመለከቷት የፈለጉ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ እና በሕጋዊ ድርድር የባሕር በር ለማግኘት ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

ኢትዮጵያ ታሪክን፣ መልክዓ ምድርንና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይን መሰረት በማድረግ የባሕር በር ጥያቄ የማንሳት መብት አላት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጎችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በየትኛውም መመዘኛ ፍትሃዊነት ያለው ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ይፋዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ወደ ግጭት የመግባት ፍላጎትም ዝግጅትም እንደሌላት ማረጋገጧን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ለመሆን እያነሳች የምትገኘው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት እና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የሀገራትን ድጋፍ ለማግኘት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

በኢማኑኤል ጆርጌ
#ባህር_በር #ኢትዮጵያ #gazette_plus
9👍3
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።

🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።

ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።

📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
6👍1
"የጸና ወዳጅነት፣ በመተማመን ላይ የተመሠረተ ትብብር"

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናል።

‎ውይይታችን በኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብርና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር።

ለተደረገልኝ አቀባበልና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነው።
6
ቦርዱ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል በሆኑ የምርጫ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ወሰደ
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የምርጫ አስፈጻሚዎች ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ነፃ መሆን ያለባቸው ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል ሆነው በተገኙ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ዛሬ ማምሻውን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ ምርጫው ፍትሐዊና ገለልተኛ እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል። በዚህም መሠረት በተደረገ ማጣራት የፓርቲ አባል መሆናቸው የተረጋገጠባቸው አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ግለሰቦች መካከል ከፓርቲ አባልነት ባለፈ የፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ጭምር እንደሚገኙበት ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል።
ቦርዱ በማጣራት ያገኛቸውን እነዚህን ግለሰቦች ከአስፈጻሚነት ያሰናበተ ሲሆን፤ የማጣራት ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
በሌላ በኩል ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት የሚታዘቡላቸውን ወኪሎች እንዲልኩ ጥሪ ተደርጎ ባጅ የተዘጋጀ ቢሆንም፣ እስካሁን ወኪሎቻቸውን የላኩት ውስን ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
ቦርዱ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ማንኛውንም ችግሮች ለመፍታት ከቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ ያሉ አሠራሮችን እንደሚጠቀም ተናግረዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #ምርጫ_2018 #ምርጫ_ቦርድ #ገለልተኝነት #ኢትዮጵያ #ምርጫ_አስፈጻሚ
👍4
የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱምን አግኝቼ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
‎በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
10👍3
በመካከላኛው ምሥራቅ በተፈጠረው ቀውስ የተነሣ ነዳጅ ገዝተው የሚጠቀሙ ሀገሮች እንደልብ ለማግኘት ተቸግረዋል። በመሆኑም ችግሩ ተፈትቶ ወደ መደበኛው የነዳጅ አቅርቦት ሥርዓት እስክንመለስ ድረስ ነዳጅን በቁጠባና ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት መጠቀም ይኖርብናል።
በመሆኑም የነዳጅ አከፋፋዮች፣ማደያዎችና ተጠቃሚዎች ነዳጅን በቁጠባ፣ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት ሁላችንም በሃላፊነት ስሜት እንድንጠቀም ለማሳሰብ እወዳለው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍3😁2