ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመለሱ
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
“የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግስት ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ ሀገራዊ የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ጉዞን የሚዳስስና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚመለከት ኮንፈረስ ተካሂዷል፡፡
የተቋሙ ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤ በኮንፈረንሱ ላይ እንደገለጹት፤ የህዝብ አስተዳደር እንዲሻሻልና የመንግስት ተጠያቂነት ለማሳደግ ይሰራል፡፡
አስተዳደራዊ በደል የደረሰባቸው ግለሰቦች የሚያቀርቧቸውን ቅተሬታዎችና አቤቱታዎች በመከታተል መምርምሮ እልባት እንዲያገኙ እየሰራ ይገኛል፡፡ በቀጣይም የአቤቱታ ምላሽ አሰጣጡን ከ78 በመቶ ወደ 85 በመቶ ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ሥራዎች ወደ ተቋሙ ከሚመጡ አቤቱታዎች መካከል 78 በመቶው እልባት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ ለአስተዳደራዊ በደል ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የቁጥጥር ሥራዎችን በመስራት 87 በመቶ መፍትሔ እንዲያኙ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡
እንደዋና ዕንባ ጠባቂዋ ገለጻ፤ መሬታቸው ያለአግባብ የተወሰደባቸው 828 አቤቱታ አቅራቢዎች ጉዳያቸው ተመርምሮ ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸውና 14 ሚሊየን ብር ካሳ እንዲከፈላቸው ተደርጓል፡፡ ከህግ ውጪ ከሥራቸው ተሰናብተው የነበሩ 942 ሰራተኞች ደግሞ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ መደረጉን አብራርተዋል፡፡
አቤቱታ አቅራቢዎች ከህግ አግባብ ውጪ የተከለከሉትን ልዩ ልዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው፤ ዜጎች መረጃ የማግኘት፤ የመጠየቅ፣ የማዘጋጀት መብታቸው እንዲከበርና የመረጃ ነጻነት ህጉ እንዲተገበር ክትትል እያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡፡
የተጠናከረ የቁጥጥርና የምርመራ ሥርዓትን መዘርጋት፤ የአስተዳደራዊ በደል እንዲቀንስ መስራት የተቋሙ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
የህዝብ አስተዳደር በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ እንዲመራ ለማድረግና ህገ መንግሥታዊነትን ለማስፈን እንደሚሰራ በመግለጽ፤ ተቋማት የሚሰጧቸው ፍትሃዊነት የጎደለው ውሳኔዎችና ትዕዛዞች በወቅቱ ለማረምና ለመከላከል እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazette_plus #ዕንባ_ጠባቂ #መረጃ ነጻነት #አስተዳደራዊ_በደል_ማረም
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
“የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግስት ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ ሀገራዊ የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ጉዞን የሚዳስስና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚመለከት ኮንፈረስ ተካሂዷል፡፡
የተቋሙ ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤ በኮንፈረንሱ ላይ እንደገለጹት፤ የህዝብ አስተዳደር እንዲሻሻልና የመንግስት ተጠያቂነት ለማሳደግ ይሰራል፡፡
አስተዳደራዊ በደል የደረሰባቸው ግለሰቦች የሚያቀርቧቸውን ቅተሬታዎችና አቤቱታዎች በመከታተል መምርምሮ እልባት እንዲያገኙ እየሰራ ይገኛል፡፡ በቀጣይም የአቤቱታ ምላሽ አሰጣጡን ከ78 በመቶ ወደ 85 በመቶ ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ሥራዎች ወደ ተቋሙ ከሚመጡ አቤቱታዎች መካከል 78 በመቶው እልባት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ ለአስተዳደራዊ በደል ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የቁጥጥር ሥራዎችን በመስራት 87 በመቶ መፍትሔ እንዲያኙ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡
እንደዋና ዕንባ ጠባቂዋ ገለጻ፤ መሬታቸው ያለአግባብ የተወሰደባቸው 828 አቤቱታ አቅራቢዎች ጉዳያቸው ተመርምሮ ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸውና 14 ሚሊየን ብር ካሳ እንዲከፈላቸው ተደርጓል፡፡ ከህግ ውጪ ከሥራቸው ተሰናብተው የነበሩ 942 ሰራተኞች ደግሞ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ መደረጉን አብራርተዋል፡፡
አቤቱታ አቅራቢዎች ከህግ አግባብ ውጪ የተከለከሉትን ልዩ ልዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው፤ ዜጎች መረጃ የማግኘት፤ የመጠየቅ፣ የማዘጋጀት መብታቸው እንዲከበርና የመረጃ ነጻነት ህጉ እንዲተገበር ክትትል እያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡፡
የተጠናከረ የቁጥጥርና የምርመራ ሥርዓትን መዘርጋት፤ የአስተዳደራዊ በደል እንዲቀንስ መስራት የተቋሙ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
የህዝብ አስተዳደር በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ እንዲመራ ለማድረግና ህገ መንግሥታዊነትን ለማስፈን እንደሚሰራ በመግለጽ፤ ተቋማት የሚሰጧቸው ፍትሃዊነት የጎደለው ውሳኔዎችና ትዕዛዞች በወቅቱ ለማረምና ለመከላከል እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazette_plus #ዕንባ_ጠባቂ #መረጃ ነጻነት #አስተዳደራዊ_በደል_ማረም
❤10
የሀገር ጉዳይ አይሸጥም ብሎ የሚያምን ህዝብ የባህር በር ጥያቄን እውን የሚያደርግበት ጊዜ ቅርብ ነው
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | “የሀገር ጉዳይ አይሸጥም፤ አይለወጥም” ብሎ የሚያምን ህዝብ ያላት ሀገር የባህር በር ጥያቄን እውን የሚያደርግበት ጊዜ ቅርብ ነው ሲሉ የታሪክ ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ተናገሩ፡፡
ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በዓመት ለወደብ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና እየተዳረገች ነው፡፡
60 ኪሎ ሜትር ብቻ የሚርቅ የባህር በር እያለ፣ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለኪራይ ማውጣት አግባብ አይደለም የሚሉት የታሪክ ተመራማሪው፤ ጥያቄውም የ130 ሚሊዮን ህዝብ ጥያቄ ነው ብለዋል፡፡
የታሪክ ተመራማሪው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ንጉስ ናት፡፡ የህዝቡ ጥያቄ ያለአግባብ ያጣነው የባህር በር ወደ ባለቤቱ ይመለስ የሚል ነው፡፡ ይህም ተቀባይነት ያለው ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በሴራ ያጣነውን የባህር በር መልሶ ለማግኘት በአንድነት መቆም እንደሚገባ በመግለጽ፤ የባህር በር ጥያቄው በሰላማዊና በበሳል የዲፕሎማሲ መንገድ መፈታት እንዳለበት አሳስበዋል።
የባህር በር ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የቀጠናው ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ያሉት ተመራማሪው፤ የቀይ ባህር ሰላም መሆን ለገልፍ ሀገራት ጭምር ወሳኝ በመሆኑ በድርድር መፈታቱ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን በአድዋ ጦርነትና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ያሳዩትን የማይበገር አንድነት፣ አሁንም ለሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማነት ሊደግሙት ይገባል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤት እንድትሆን የሚከለክላት የታሪክም ሆነ የፍትህ ምክንያት የለም እንደለሌለም አመለክተዋል፡፡
በታደሠ ብናልፈው
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | “የሀገር ጉዳይ አይሸጥም፤ አይለወጥም” ብሎ የሚያምን ህዝብ ያላት ሀገር የባህር በር ጥያቄን እውን የሚያደርግበት ጊዜ ቅርብ ነው ሲሉ የታሪክ ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ተናገሩ፡፡
ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በዓመት ለወደብ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ለከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና እየተዳረገች ነው፡፡
60 ኪሎ ሜትር ብቻ የሚርቅ የባህር በር እያለ፣ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለኪራይ ማውጣት አግባብ አይደለም የሚሉት የታሪክ ተመራማሪው፤ ጥያቄውም የ130 ሚሊዮን ህዝብ ጥያቄ ነው ብለዋል፡፡
የታሪክ ተመራማሪው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ንጉስ ናት፡፡ የህዝቡ ጥያቄ ያለአግባብ ያጣነው የባህር በር ወደ ባለቤቱ ይመለስ የሚል ነው፡፡ ይህም ተቀባይነት ያለው ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በሴራ ያጣነውን የባህር በር መልሶ ለማግኘት በአንድነት መቆም እንደሚገባ በመግለጽ፤ የባህር በር ጥያቄው በሰላማዊና በበሳል የዲፕሎማሲ መንገድ መፈታት እንዳለበት አሳስበዋል።
የባህር በር ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የቀጠናው ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ያሉት ተመራማሪው፤ የቀይ ባህር ሰላም መሆን ለገልፍ ሀገራት ጭምር ወሳኝ በመሆኑ በድርድር መፈታቱ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን በአድዋ ጦርነትና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ያሳዩትን የማይበገር አንድነት፣ አሁንም ለሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማነት ሊደግሙት ይገባል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤት እንድትሆን የሚከለክላት የታሪክም ሆነ የፍትህ ምክንያት የለም እንደለሌለም አመለክተዋል፡፡
በታደሠ ብናልፈው
👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ድሬ የቀደመ የከተሜነት ታሪኳን፣ ዘመናት ያስቆጠረ ድንቅ ባህሏን እንዲሁም በፍቅር የተሞላውን ህዝቧን የሚመጥን ውበት ተላብሳለች! የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን እጅግ ውብ እና ምቹ በማድረግ ታሪካዊነቷን ከዘመናዊ የከተማ መሰረተ ልማት ጋር በማቀናጀት ለመጎብኘት ተመራጭ አድርጓታል፡፡
#VisitEthiopia #PMOEthiopia
#VisitEthiopia #PMOEthiopia
❤2🥰1
“የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም” - የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም ሲሉ በለንደን የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ ሀማድ ቤይግ ገለጹ፡፡
ሀማድ ቤይግ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ኢኮኖሚያዊ አስፈላጊነትና የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋ መልስ እንዲገኝ በሕግና በድርድር የተደገፈ መፍትሄዎችን እንደምትከተል የገለጹት ሀማድ፤ የባሕር በር በኃይል አማራጭ ልታገኝ ነው የሚለው ኢ-ምክንያታዊ ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ባነሳች ማግስት ጸብ አጫሪ አድርገው ሊመለከቷት የፈለጉ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ እና በሕጋዊ ድርድር የባሕር በር ለማግኘት ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ መልክዓ ምድርንና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይን መሰረት በማድረግ የባሕር በር ጥያቄ የማንሳት መብት አላት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጎችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በየትኛውም መመዘኛ ፍትሃዊነት ያለው ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ይፋዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ወደ ግጭት የመግባት ፍላጎትም ዝግጅትም እንደሌላት ማረጋገጧን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ለመሆን እያነሳች የምትገኘው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት እና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የሀገራትን ድጋፍ ለማግኘት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
በኢማኑኤል ጆርጌ
#ባህር_በር #ኢትዮጵያ #gazette_plus
+++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም ሲሉ በለንደን የዓለም አቀፍ ንግድ ከፍተኛ ጠበቃና አማካሪ ሀማድ ቤይግ ገለጹ፡፡
ሀማድ ቤይግ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ኢኮኖሚያዊ አስፈላጊነትና የሀገር ሕልውና ጉዳይ እንጂ ጠብ አጫሪነት አይደለም።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋ መልስ እንዲገኝ በሕግና በድርድር የተደገፈ መፍትሄዎችን እንደምትከተል የገለጹት ሀማድ፤ የባሕር በር በኃይል አማራጭ ልታገኝ ነው የሚለው ኢ-ምክንያታዊ ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ባነሳች ማግስት ጸብ አጫሪ አድርገው ሊመለከቷት የፈለጉ ሀገራት መኖራቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ እና በሕጋዊ ድርድር የባሕር በር ለማግኘት ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ መልክዓ ምድርንና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይን መሰረት በማድረግ የባሕር በር ጥያቄ የማንሳት መብት አላት። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጎችን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በየትኛውም መመዘኛ ፍትሃዊነት ያለው ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ይፋዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ወደ ግጭት የመግባት ፍላጎትም ዝግጅትም እንደሌላት ማረጋገጧን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ለመሆን እያነሳች የምትገኘው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት እና ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የሀገራትን ድጋፍ ለማግኘት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡
በኢማኑኤል ጆርጌ
#ባህር_በር #ኢትዮጵያ #gazette_plus
❤9👍3
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።
✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።
📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
❤6👍1
"የጸና ወዳጅነት፣ በመተማመን ላይ የተመሠረተ ትብብር"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናል።
ውይይታችን በኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብርና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር።
ለተደረገልኝ አቀባበልና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በነበረኝ የስራ ጉብኝት ከፕሬዝዳንት ግርማዊ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር ተገናኝቼ ተወያይተናል።
ውይይታችን በኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ለረጅም ዘመናት የቆየውን ወዳጅነት በማጎልበት፤ ትብብርና ቀጣናዊ መረጋጋትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር።
ለተደረገልኝ አቀባበልና በሀገሮቻችን መካከል የፀና ወዳጅነታችንን የበለጠ ለማጠናከር ለተጋራነው የፀና አቋም ምስጋናዬ የላቀ ነው።
❤6
ቦርዱ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል በሆኑ የምርጫ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ወሰደ
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የምርጫ አስፈጻሚዎች ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ነፃ መሆን ያለባቸው ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል ሆነው በተገኙ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ዛሬ ማምሻውን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ ምርጫው ፍትሐዊና ገለልተኛ እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል። በዚህም መሠረት በተደረገ ማጣራት የፓርቲ አባል መሆናቸው የተረጋገጠባቸው አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ግለሰቦች መካከል ከፓርቲ አባልነት ባለፈ የፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ጭምር እንደሚገኙበት ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል።
ቦርዱ በማጣራት ያገኛቸውን እነዚህን ግለሰቦች ከአስፈጻሚነት ያሰናበተ ሲሆን፤ የማጣራት ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
በሌላ በኩል ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት የሚታዘቡላቸውን ወኪሎች እንዲልኩ ጥሪ ተደርጎ ባጅ የተዘጋጀ ቢሆንም፣ እስካሁን ወኪሎቻቸውን የላኩት ውስን ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
ቦርዱ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ማንኛውንም ችግሮች ለመፍታት ከቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ ያሉ አሠራሮችን እንደሚጠቀም ተናግረዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #ምርጫ_2018 #ምርጫ_ቦርድ #ገለልተኝነት #ኢትዮጵያ #ምርጫ_አስፈጻሚ
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የምርጫ አስፈጻሚዎች ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ነፃ መሆን ያለባቸው ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባደረገው ማጣራት የፓርቲ አባል ሆነው በተገኙ አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ዛሬ ማምሻውን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ ምርጫው ፍትሐዊና ገለልተኛ እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል። በዚህም መሠረት በተደረገ ማጣራት የፓርቲ አባል መሆናቸው የተረጋገጠባቸው አስፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
እርምጃ ከተወሰደባቸው ግለሰቦች መካከል ከፓርቲ አባልነት ባለፈ የፓርቲ ዕጩ ሆነው የቀረቡ ጭምር እንደሚገኙበት ሰብሳቢዋ ጠቁመዋል።
ቦርዱ በማጣራት ያገኛቸውን እነዚህን ግለሰቦች ከአስፈጻሚነት ያሰናበተ ሲሆን፤ የማጣራት ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
በሌላ በኩል ፓርቲዎች የምርጫውን ሂደት የሚታዘቡላቸውን ወኪሎች እንዲልኩ ጥሪ ተደርጎ ባጅ የተዘጋጀ ቢሆንም፣ እስካሁን ወኪሎቻቸውን የላኩት ውስን ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
ቦርዱ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ማንኛውንም ችግሮች ለመፍታት ከቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ ያሉ አሠራሮችን እንደሚጠቀም ተናግረዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #ምርጫ_2018 #ምርጫ_ቦርድ #ገለልተኝነት #ኢትዮጵያ #ምርጫ_አስፈጻሚ
👍4
የዱባይ ገዢ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ምክትል ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ግርማዊ ሼኽ ሞሃሙድ ቢን ራሺድ አል መክቱምን አግኝቼ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በሁለቱ ሀገሮቻችን እና ሕዝቦቻችን መካከል ስላለው ጠንካራ የቢዝነስ፣ ትምህርት እና ባህል ትስስር ተነጋግረናል። ከዚህች ጠንካራ፣ ውብ እና ጽኑ ከተማ ጋር ያለን ትስስር በቀጣይ ጉብኝቶችም ይጠናከራል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
❤10👍3