“ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል”
- አቶ ሙስጠፌ መሐመድ
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
+++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል ሲሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በጂግጂጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን “ጉምሩክ ስለኢትዮጵያ” የውይይት መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት፤ ህገ-ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ ህጋዊ ነጋዴዎችን ከገበያ በማውጣት እና የሀገር ኢኮኖሚን በማቀጨጭ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
ኮንትሮባንድ የንግድ ስርዓቱን ከማዛባት ባሻገር የማህበረሰብ ጤና፣ ሰላም እና ደህንነት ላይ እክል የሚፈጥር የሀገር እክል ነው ብለዋል።
የኮንትሮባንድ መረብ ውስብስብ እና በርካታ ተዋናዮች ያሉበት በመሆኑ በፀጥታ አካላት ብቻ በሚደረግ ጥረት እልባት ሊያገኝ አይችልም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይህንን የልማት ጠላት ለመከላከል እና ለማስወገድ ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎች የንግድ ህግን አክብረው እና ለታክስ ህግ ተገዥ ሆነው በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገሪቱ ገቢ እያስገኙ እንደሚገኙ አቶ ሙስጠፌ ገልጸዋል።
አክለውም፣ ክልሉ የሚሰራቸው የልማት ስራዎች ከግብር ከፋዩ በሚገኝ ገቢ የሚሰራ ነው፤ በዚህም ህጋዊ ነጋዴዎቻችን ሊኮሩ ይገባል ብለዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎችን የንግድ ስራዎቻቸውን ለማስፋፋት ምቹ የንግድ ስነ-ምህዳር በመፍጠር እና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የክልሉ መንግስ እንደሚያበረታታቸውም አመልክተዋል።
በዮሐንስ መልካሙ (ጂግጂጋ)
- አቶ ሙስጠፌ መሐመድ
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
+++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል ሲሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በጂግጂጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን “ጉምሩክ ስለኢትዮጵያ” የውይይት መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት፤ ህገ-ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ ህጋዊ ነጋዴዎችን ከገበያ በማውጣት እና የሀገር ኢኮኖሚን በማቀጨጭ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
ኮንትሮባንድ የንግድ ስርዓቱን ከማዛባት ባሻገር የማህበረሰብ ጤና፣ ሰላም እና ደህንነት ላይ እክል የሚፈጥር የሀገር እክል ነው ብለዋል።
የኮንትሮባንድ መረብ ውስብስብ እና በርካታ ተዋናዮች ያሉበት በመሆኑ በፀጥታ አካላት ብቻ በሚደረግ ጥረት እልባት ሊያገኝ አይችልም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይህንን የልማት ጠላት ለመከላከል እና ለማስወገድ ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎች የንግድ ህግን አክብረው እና ለታክስ ህግ ተገዥ ሆነው በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገሪቱ ገቢ እያስገኙ እንደሚገኙ አቶ ሙስጠፌ ገልጸዋል።
አክለውም፣ ክልሉ የሚሰራቸው የልማት ስራዎች ከግብር ከፋዩ በሚገኝ ገቢ የሚሰራ ነው፤ በዚህም ህጋዊ ነጋዴዎቻችን ሊኮሩ ይገባል ብለዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎችን የንግድ ስራዎቻቸውን ለማስፋፋት ምቹ የንግድ ስነ-ምህዳር በመፍጠር እና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የክልሉ መንግስ እንደሚያበረታታቸውም አመልክተዋል።
በዮሐንስ መልካሙ (ጂግጂጋ)
❤8
የእመርታ ቤተ መጻሕፍት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመደመር መጻሕፍት ሽያጭ እና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በተገኘ በጀት የተገነባ ፕሮጀክት ነው።
ቤተ መጻሕፍቱ ከ1ሺ ካሬ ሜትር በላይ የቦታ ስፋት ላይ ያረፈ እና ዘመናዊ መሠረተ ልማት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል። ሶስት የወለል ብዛት የያዘው እመርታ ቤተ መጻሕፍት፤ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ተስማሚ የሆነውን የድሬን አየር እያገኙ እንዲገለገሉም የቴራስ ቦታ ተዘጋጅቶለታል።
ቤተ- መጻሕፍቱ የብሬል ማንበቢያ ቦታ፣ ለልዩ ፍላጎት ተጠቃሚዎች የተዘጋጀ የአይቲ ማዕከል፣ ከክፍል ውጭ የንባብ ቦታ፣ የግል እና የቡድን ማንበቢያ እና የጥናት ክፍሎች፣ እንዲሁም የኮንፈረንስ ክፍልን አካቷል።
በአጠቃላይ እመርታ ቤተ-መጻሕፍት በአንድ ጊዜ ለ1ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንዲችል ሆኖ የተገነባ ሲሆን በመጽሐፍ መደርመሪያው ላይ ብቻ 1ሚሊየን መጻሕፍትን የመያዝ አቅም አለው።
#PMOEthiopia
ቤተ መጻሕፍቱ ከ1ሺ ካሬ ሜትር በላይ የቦታ ስፋት ላይ ያረፈ እና ዘመናዊ መሠረተ ልማት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል። ሶስት የወለል ብዛት የያዘው እመርታ ቤተ መጻሕፍት፤ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ተስማሚ የሆነውን የድሬን አየር እያገኙ እንዲገለገሉም የቴራስ ቦታ ተዘጋጅቶለታል።
ቤተ- መጻሕፍቱ የብሬል ማንበቢያ ቦታ፣ ለልዩ ፍላጎት ተጠቃሚዎች የተዘጋጀ የአይቲ ማዕከል፣ ከክፍል ውጭ የንባብ ቦታ፣ የግል እና የቡድን ማንበቢያ እና የጥናት ክፍሎች፣ እንዲሁም የኮንፈረንስ ክፍልን አካቷል።
በአጠቃላይ እመርታ ቤተ-መጻሕፍት በአንድ ጊዜ ለ1ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንዲችል ሆኖ የተገነባ ሲሆን በመጽሐፍ መደርመሪያው ላይ ብቻ 1ሚሊየን መጻሕፍትን የመያዝ አቅም አለው።
#PMOEthiopia
👍6❤3
በሀረሪ ክልል ሶፊ ወረዳ ቡርቃ ቀበሌ ውስጥ የተሠራው የገጠር ኮሪደር ሥራ በአካባቢው በተገኙ ቁሳቁሶች፤ በኅብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወነ የአነስተኛ መንደር ሞዴል ክንውን ነው። የአካባቢው ነዋሪ በንቃት የተሳተፈበት የገጠር ኮሪደር ሥራ ባሕላዊ የግንባታ ዘዴን፣ የተደራጀ እቅድና ተግባራዊ የአሰራር ውጤት ያሳየ ነው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍8❤4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
"በሀረር ከተማ የተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል አቀናጅቶ የማቅረብ ሀገር አቀፍ መርሃ ግብር አካል ነው።
በሀረር የመሶብ ማዕከል 8 ተቋማት በ24 የአገልግሎት መስኮቶች 67 የተለያዩ የሕዝብ አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ ለተገልጋይ ያቀርባል።
ይኅው ሀገራዊ አፈፃፀም የመንግሥት አገልግሎትን ብቃት፣ ተደራሽነት እና የዜጎች እርካታ በማሻሻል፣ በተቋማት መካከከል የተበታተነ አገልግሎትን በመቀነስ፣ ኅብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት የሚያጠፋውን ጊዜ እና ገንዘብ መቀነስ አስችሏል።
በመላው ሀገራችን የመሶብ ሥነዘዴ፤ መንግሥት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የተቀናጀ የአገልግሎት አሰጣጥ ያለውን ጽኑ አቋም በሚያመላክት መንገድ እየተስፋፋ ይገኛል።
የተቀናጀ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የመንግሥት አገልግሎት አፈፃፀም ቁልፍ የክዋኔ ማመላከቻ እና አጠቃላይ የዜጎች ተጠቃሚነት ማጎልበቻ ሆነዋል።
"በሀረር ከተማ የተቋቋመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል አቀናጅቶ የማቅረብ ሀገር አቀፍ መርሃ ግብር አካል ነው።
በሀረር የመሶብ ማዕከል 8 ተቋማት በ24 የአገልግሎት መስኮቶች 67 የተለያዩ የሕዝብ አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ ለተገልጋይ ያቀርባል።
ይኅው ሀገራዊ አፈፃፀም የመንግሥት አገልግሎትን ብቃት፣ ተደራሽነት እና የዜጎች እርካታ በማሻሻል፣ በተቋማት መካከከል የተበታተነ አገልግሎትን በመቀነስ፣ ኅብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት የሚያጠፋውን ጊዜ እና ገንዘብ መቀነስ አስችሏል።
በመላው ሀገራችን የመሶብ ሥነዘዴ፤ መንግሥት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የተቀናጀ የአገልግሎት አሰጣጥ ያለውን ጽኑ አቋም በሚያመላክት መንገድ እየተስፋፋ ይገኛል።
የተቀናጀ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የመንግሥት አገልግሎት አፈፃፀም ቁልፍ የክዋኔ ማመላከቻ እና አጠቃላይ የዜጎች ተጠቃሚነት ማጎልበቻ ሆነዋል።
👍4🔥1
ከመጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተሰጡ ሹመቶች
- ሌ/ጄኔራል አስራት ደኔሮ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
- ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
- አቶ ኤርዚቅ ኢሳ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
#PMOEthiopia
- ሌ/ጄኔራል አስራት ደኔሮ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
- ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
- አቶ ኤርዚቅ ኢሳ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
#PMOEthiopia
❤1