Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.2K subscribers
40.8K photos
333 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
“የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ታላቅነት ማሳያ ነው”

- በኢትዮ- ሶማሊያ ጦርነት የፓራኮማንዶ ብርጌድ አዛዥ
+++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የካራማራ ድል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሀገሩ ነፃነት ያለውን ፍቅርና ታላቅነት በተግባር ያሳየበት የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት የአንደኛ የፓራኮማንዶ ብርጌድ አዛዥ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም ገለጹ።

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ በወቅቱ የነበረው የጦር ሁኔታ ተመጣጣኝ ባልነበረበትና ሀገሪቱ በውስጥ ችግሮች ተወጥራ በነበረችበት ወቅት ወራሪውን የሶማሊያ ኃይል በአጭር ጊዜ ዝግጅት ድል ማድረግ መቻሉ ተአምራዊ ነበር።

ሶማሊያ ጅግጅጋ ለመድረስ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ብትገሰግስም፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ካራማራ ላይ ባደረገው ተጋድሎና ምሽግ በመያዝ የጠላትን ጉዞ መግታት መቻሉን አውስተዋል።

የክተት አዋጁን ተከትሎ ከ120 ሺህ በላይ ሕዝብ በ48 ሰዓታት ውስጥ ታጠቅ ጦር ሰፈር በመክተት ያሳየው ወገንተኝነት የድሉ መሠረት መሆኑን ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ገልጸዋል።

በወቅቱ ሐረርና ድሬዳዋን ከመከላከል ባለፈ፣ የወገን ጦር ባደረገው ከፍተኛ ጥቃት ጠላት ተሸንፎ እስከ ሐርጌሳ እንዲገባ መደረጉንና በኦጋዴን አካባቢዎች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ዳግም መውለብለቡን ተርከዋል።

ትውልዱ ከዚህ የታሪክ አጋጣሚ በመማር፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ሰላም ዘመናዊና በሚገባ የሠለጠነ የሰው ኃይል ያለው ሠራዊት የመገንባት አስፈላጊነትን ሊገነዘብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በበኃይሉ አበራ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ካራማራ #ኢትዮጵያ #የካራማራ_ድል #ሶማሊያ #ታሪክ #ተስፋዬ_ሀብተማሪያም #ሉዓላዊነት
👍61
#ፕሬስ_መረጃ_ማጣሪያ - በመለያ የምርት ቁጥር 620 የተመረቱ የፋይን (Fine) የታሸጉ የውኃ ምርቶች ባዕድ ነገር የታየባቸው በመሆናቸው ምርቶችን ማህበረሰቡ እንዳይጠቀም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳስበ።
https://www.facebook.com/share/p/14WPmnaX475

#የጤናጥንቃቄ #PublicHealth #FoodSafety #የውኃጥራት #HealthAlertEthiopia #ፋይንውኃ #FineWater #የታሸገውኃ #ጥራትቁጥጥር #EFDA #የምግብናመድኃኒትባለስልጣን #ConsumerProtection #Ethiopia
1
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።

🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።

ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።

📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
5🔥1
“ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል”

- አቶ ሙስጠፌ መሐመድ
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
+++++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል ሲሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በጂግጂጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን “ጉምሩክ ስለኢትዮጵያ” የውይይት መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት፤ ህገ-ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ ህጋዊ ነጋዴዎችን ከገበያ በማውጣት እና የሀገር ኢኮኖሚን በማቀጨጭ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።

ኮንትሮባንድ የንግድ ስርዓቱን ከማዛባት ባሻገር የማህበረሰብ ጤና፣ ሰላም እና ደህንነት ላይ እክል የሚፈጥር የሀገር እክል ነው ብለዋል።

የኮንትሮባንድ መረብ ውስብስብ እና በርካታ ተዋናዮች ያሉበት በመሆኑ በፀጥታ አካላት ብቻ በሚደረግ ጥረት እልባት ሊያገኝ አይችልም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይህንን የልማት ጠላት ለመከላከል እና ለማስወገድ ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ህጋዊ ነጋዴዎች የንግድ ህግን አክብረው እና ለታክስ ህግ ተገዥ ሆነው በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገሪቱ ገቢ እያስገኙ እንደሚገኙ አቶ ሙስጠፌ ገልጸዋል።

አክለውም፣ ክልሉ የሚሰራቸው የልማት ስራዎች ከግብር ከፋዩ በሚገኝ ገቢ የሚሰራ ነው፤ በዚህም ህጋዊ ነጋዴዎቻችን ሊኮሩ ይገባል ብለዋል።

ህጋዊ ነጋዴዎችን የንግድ ስራዎቻቸውን ለማስፋፋት ምቹ የንግድ ስነ-ምህዳር በመፍጠር እና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የክልሉ መንግስ እንደሚያበረታታቸውም አመልክተዋል።

በዮሐንስ መልካሙ (ጂግጂጋ)
8
የእመርታ ቤተ መጻሕፍት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመደመር መጻሕፍት ሽያጭ እና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በተገኘ በጀት የተገነባ ፕሮጀክት ነው።

ቤተ መጻሕፍቱ ከ1ሺ ካሬ ሜትር በላይ የቦታ ስፋት ላይ ያረፈ እና ዘመናዊ መሠረተ ልማት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል። ሶስት የወለል ብዛት የያዘው እመርታ ቤተ መጻሕፍት፤ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ተስማሚ የሆነውን የድሬን አየር እያገኙ እንዲገለገሉም የቴራስ ቦታ ተዘጋጅቶለታል።

‎ቤተ- መጻሕፍቱ የብሬል ማንበቢያ ቦታ፣ ለልዩ ፍላጎት ተጠቃሚዎች የተዘጋጀ የአይቲ ማዕከል፣ ከክፍል ውጭ የንባብ ቦታ፣ የግል እና የቡድን ማንበቢያ እና የጥናት ክፍሎች፣ እንዲሁም የኮንፈረንስ ክፍልን አካቷል።

በአጠቃላይ እመርታ ቤተ-መጻሕፍት በአንድ ጊዜ ለ1ሺህ ሰው አገልግሎት መስጠት እንዲችል ሆኖ የተገነባ ሲሆን በመጽሐፍ መደርመሪያው ላይ ብቻ 1ሚሊየን መጻሕፍትን የመያዝ አቅም አለው።

#PMOEthiopia
👍63